Traducción al amárico - Academia de África
Traducción de los significados del Sagrado Corán
Traducida por Muhammad Zain Zahr Ad-Din. Publicada por la Academia de África.
ٱلۡقَارِعَةُ
1. ቆርቋሪይቱ (ጩኸት)፤
مَا ٱلۡقَارِعَةُ
2. ቆርቋሪይቱ (ጩኸት) ምንድን ናት!
وَمَآ أَدۡرَىٰكَ مَا ٱلۡقَارِعَةُ
3. (መልዕክተኛችን ሙሐመድ ሆይ!) ቆርቋሪይቱ ምን እንደሆነች ምን አሳወቀህ?
يَوۡمَ يَكُونُ ٱلنَّاسُ كَٱلۡفَرَاشِ ٱلۡمَبۡثُوثِ
4. ሰዎች እንደተበታተነ ቢራቢሮ (ኩብኩባ) የሚሆኑበት ቀን፤
وَتَكُونُ ٱلۡجِبَالُ كَٱلۡعِهۡنِ ٱلۡمَنفُوشِ
5. ጋራዎችም እንደ ተነደፈ ሱፍ የሚሆኑበት (አስደንጋጭ ቀን) ናት።
فَأَمَّا مَن ثَقُلَتۡ مَوَٰزِينُهُۥ
6. በዚያ ዕለት ያ ሚዛኖቹ የከበዱለት ሰውማ
فَهُوَ فِي عِيشَةٖ رَّاضِيَةٖ
7. እርሱ ኑሮው በአሰደሳቿ ጀነት ውስጥ ይሆናል።
وَأَمَّا مَنۡ خَفَّتۡ مَوَٰزِينُهُۥ
8. ያ ሚዛኖቹ የቀለሉበት ሰው ደግሞ
فَأُمُّهُۥ هَاوِيَةٞ
9. መኖሪያው ሃዊያህ (የምትባል የገሀነም እሳት) ናት።
وَمَآ أَدۡرَىٰكَ مَا هِيَهۡ
10. (መልዕክተኛችን ሙሐመድ ሆይ!) እርሷ ምን እንደሆነች ምን አሳወቀህ?
نَارٌ حَامِيَةُۢ
11. (እርሷ) በጣም ተኳሳ እሳት ናት::
share_via