アムハラ語対訳 - アフリカ・アカデミー
聖クルアーンの意味の翻訳
محمد زين زهر الدين訳。アフリカアカデミー発行。
وَٱلسَّمَآءِ وَٱلطَّارِقِ
1. በሰማዩ እና ሌሊት በሚመጣውም እምላለሁ።
وَمَآ أَدۡرَىٰكَ مَا ٱلطَّارِقُ
2. (መልዕክተኛችን ሙሐመድ ሆይ!) የሌሊት መጪው ምን እንደሆነ ምን አሳወቀህ?
ٱلنَّجۡمُ ٱلثَّاقِبُ
3. ጨለማውን ሰንጣቂ ኮከብ ነው::
إِن كُلُّ نَفۡسٖ لَّمَّا عَلَيۡهَا حَافِظٞ
4. ነፍስ ሁሉ በእርሷ ላይ ጠባቂ ያለባት እንጂ ሌላ አይደለችም::
فَلۡيَنظُرِ ٱلۡإِنسَٰنُ مِمَّ خُلِقَ
5. የሰው ልጅ ከምን እንደተፈጠረ ይመልከት፤
خُلِقَ مِن مَّآءٖ دَافِقٖ
6. ከተስፈንጣሪ ውሃ (የዘር ፈሳሽ) ተፈጠረ::
يَخۡرُجُ مِنۢ بَيۡنِ ٱلصُّلۡبِ وَٱلتَّرَآئِبِ
7. ከጀርባና ከእርግብግቢቶች መካከል የሚወጣ ከሆነ የዘር ፈሳሽ ውሃ (ተፈጠረ)።
إِنَّهُۥ عَلَىٰ رَجۡعِهِۦ لَقَادِرٞ
8. አላህ እርሱን በመመለሱ ላይ በእርግጥ ቻይ ነው::
يَوۡمَ تُبۡلَى ٱلسَّرَآئِرُ
9. ሚስጥሮች በሚገለጹበት ቀን፤
فَمَا لَهُۥ مِن قُوَّةٖ وَلَا نَاصِرٖ
10. (ለሰው) ምንም ኃይልና ረዳት አይኖረዉም::
وَٱلسَّمَآءِ ذَاتِ ٱلرَّجۡعِ
11. የመመለስ ባለቤት (ዝናባማ) በሆነችው ሰማይ እምላለሁ::
وَٱلۡأَرۡضِ ذَاتِ ٱلصَّدۡعِ
12. (በበቃይ) የመሰንጠቅ ባለቤት በሆነችው ምድርም እምላለሁ::
إِنَّهُۥ لَقَوۡلٞ فَصۡلٞ
13. እርሱ (ቁርኣን)፤ (እውነትን ከውሸት) የሚለይ (የአላህ) ቃል ነው።
وَمَا هُوَ بِٱلۡهَزۡلِ
14. እርሱም ቀልድ አይደለም።
إِنَّهُمۡ يَكِيدُونَ كَيۡدٗا
15. እነርሱ በእርግጥ ተንኮልን ያሴራሉ (ይሸርባሉ)::
وَأَكِيدُ كَيۡدٗا
16. እኔ ተንኮልንም እመልሳለሁ (አመክናለሁ)::
فَمَهِّلِ ٱلۡكَٰفِرِينَ أَمۡهِلۡهُمۡ رُوَيۡدَۢا
17. (መልዕክተኛችን ሙሐመድ ሆይ!) ከሓዲያንን ቀን ሰጣቸው:: ጥቂትን ጊዜ አቆያቸው (ታገሳቸው)::
share_via