Amharic translation - Muhammad Sadiq
ߞߎ߬ߙߊ߬ߣߊ߫ ߛߊߣߌ߲ ߞߘߐߦߌߘߊ ߘߐߖߊ߬ߡߊ߲߬ߠߌ߲
Translated by Sh. Muhammed Sadiq and Muhammed Sani Habib and developed under the supervision of Rowwad Translation Center. The original translation is available for review, evaluation, and continuous development.
وَيۡلٞ لِّكُلِّ هُمَزَةٖ لُّمَزَةٍ
ለሃሜተኛ ለዘላፊ ሁሉ ወዮለት፡፡
ٱلَّذِي جَمَعَ مَالٗا وَعَدَّدَهُۥ
ለዚያ ገንዘብን የሰበሰበና የቆጣጠረው (ያደለበውም) ለኾነ ፤(ወዮለት)፡፡
يَحۡسَبُ أَنَّ مَالَهُۥٓ أَخۡلَدَهُۥ
ገንዘቡ የሚያዘወትረው መኾኑን ያስባል፡፡
كَلَّاۖ لَيُنۢبَذَنَّ فِي ٱلۡحُطَمَةِ
ይከልከል፤ በሰባሪይቱ (እሳት) ውስጥ በእርግጥ ይጣላል፡፡
وَمَآ أَدۡرَىٰكَ مَا ٱلۡحُطَمَةُ
ሰባሪይቱም ምን እንደ ኾነች ምን አሳወቀህ?
نَارُ ٱللَّهِ ٱلۡمُوقَدَةُ
የተነደደችው የአላህ እሳት ናት፡፡
ٱلَّتِي تَطَّلِعُ عَلَى ٱلۡأَفۡـِٔدَةِ
ያቺ በልቦች ላይ የምትዘልቅ የኾነችው፡፡
إِنَّهَا عَلَيۡهِم مُّؤۡصَدَةٞ
እርሷ በእርግጥ በእነርሱ ላይ የተዘጋጀች ናት፡፡
فِي عَمَدٖ مُّمَدَّدَةِۭ
በተዘረጋች አዕማድ ውስጥ (የተዘጋች ናት)፡፡
share_via