Header Include

Amharic translation - Africa Academy

Translated by Muhammad Zain Zahruddin. Published by Africa Academy

QR Code https://quran.islamcontent.com/rn/amharic_zain

إِذَا وَقَعَتِ ٱلۡوَاقِعَةُ

1. ተጨባጪቱ (ቂያማ) እውን በሆነች ጊዜ፤

1. ተጨባጪቱ (ቂያማ) እውን በሆነች ጊዜ፤

لَيۡسَ لِوَقۡعَتِهَا كَاذِبَةٌ

2. (ቂያማ) እውን ለመሆኗ አንዲትም አስተባባይ ነፍስ የለችም።

2. (ቂያማ) እውን ለመሆኗ አንዲትም አስተባባይ ነፍስ የለችም።

خَافِضَةٞ رَّافِعَةٌ

3. እርሷ (ገሚሱን) ዝቅ አድራጊና (ገሚሱን) ደግሞ ከፍ አድራጊ ናት::

3. እርሷ (ገሚሱን) ዝቅ አድራጊና (ገሚሱን) ደግሞ ከፍ አድራጊ ናት::

إِذَا رُجَّتِ ٱلۡأَرۡضُ رَجّٗا

4. ምድር መናወጥን በተናወጠች ጊዜ::

4. ምድር መናወጥን በተናወጠች ጊዜ::

وَبُسَّتِ ٱلۡجِبَالُ بَسّٗا

5. ተራራዎች (እንደተፈጨ ዱቄት) መፈርፈርን በተፈረፈሩ ጊዜ።

5. ተራራዎች (እንደተፈጨ ዱቄት) መፈርፈርን በተፈረፈሩ ጊዜ።

فَكَانَتۡ هَبَآءٗ مُّنۢبَثّٗا

6. የተበተነ ብናኝ በሆኑም ጊዜ::

6. የተበተነ ብናኝ በሆኑም ጊዜ::

وَكُنتُمۡ أَزۡوَٰجٗا ثَلَٰثَةٗ

7. እናንተ (ሰዎች) ሶስት ዓይነቶችም በሆናችሁ ጊዜ (ገሚሱን ዝቅ እና ገሚሱን ከፍ ታደርጋለች)::

7. እናንተ (ሰዎች) ሶስት ዓይነቶችም በሆናችሁ ጊዜ (ገሚሱን ዝቅ እና ገሚሱን ከፍ ታደርጋለች)::

فَأَصۡحَٰبُ ٱلۡمَيۡمَنَةِ مَآ أَصۡحَٰبُ ٱلۡمَيۡمَنَةِ

8. እናም በዚያ ቀን የቀኝ ጓዶች ለመሆን የበቁ ሁሉ ምን (የተከበሩ) የቀኝ ጓዶች ናቸው::

8. እናም በዚያ ቀን የቀኝ ጓዶች ለመሆን የበቁ ሁሉ ምን (የተከበሩ) የቀኝ ጓዶች ናቸው::

وَأَصۡحَٰبُ ٱلۡمَشۡـَٔمَةِ مَآ أَصۡحَٰبُ ٱلۡمَشۡـَٔمَةِ

9. የግራ ጓዶች ምን (የተዋረዱ) የግራ ጓዶች ናቸው::

9. የግራ ጓዶች ምን (የተዋረዱ) የግራ ጓዶች ናቸው::

وَٱلسَّٰبِقُونَ ٱلسَّٰبِقُونَ

10. እነዚያ (ለበጎ ስራ) ቀዳሚዎች የሆኑ ሁሉ (ለገነትም) ቀዳሚዎች ናቸው::

10. እነዚያ (ለበጎ ስራ) ቀዳሚዎች የሆኑ ሁሉ (ለገነትም) ቀዳሚዎች ናቸው::

أُوْلَٰٓئِكَ ٱلۡمُقَرَّبُونَ

11. እነዚያ (በአላህ ዘንድም) ባለሟሎች ናቸው

11. እነዚያ (በአላህ ዘንድም) ባለሟሎች ናቸው

فِي جَنَّٰتِ ٱلنَّعِيمِ

12. በመደሰቻ ገነቶች ውስጥ ሲሆኑ

12. በመደሰቻ ገነቶች ውስጥ ሲሆኑ

ثُلَّةٞ مِّنَ ٱلۡأَوَّلِينَ

13. (የዚህ እድል ባለ ቤቶች) ከፊተኞቹ ብዙ ቡድኖች ናቸው::

13. (የዚህ እድል ባለ ቤቶች) ከፊተኞቹ ብዙ ቡድኖች ናቸው::

وَقَلِيلٞ مِّنَ ٱلۡأٓخِرِينَ

14. ከኋለኞቹ ግን ጥቂቶች ናቸው::

14. ከኋለኞቹ ግን ጥቂቶች ናቸው::

عَلَىٰ سُرُرٖ مَّوۡضُونَةٖ

15. በተሸሞኑ አልጋዎች ላይ ይሆናሉ::

15. በተሸሞኑ አልጋዎች ላይ ይሆናሉ::

مُّتَّكِـِٔينَ عَلَيۡهَا مُتَقَٰبِلِينَ

16. በእርሷ ላይ የተመቻቹና ፊት ለፊት የተቅጣጩ ሲሆኑ።

16. በእርሷ ላይ የተመቻቹና ፊት ለፊት የተቅጣጩ ሲሆኑ።

يَطُوفُ عَلَيۡهِمۡ وِلۡدَٰنٞ مُّخَلَّدُونَ

17. እነርሱን (ለማገለገል) በእነርሱ ዙሪያ ሁልጊዜ የማያረጁ ወጣት ልጆች ይዘዋወራሉ።

17. እነርሱን (ለማገለገል) በእነርሱ ዙሪያ ሁልጊዜ የማያረጁ ወጣት ልጆች ይዘዋወራሉ።

بِأَكۡوَابٖ وَأَبَارِيقَ وَكَأۡسٖ مِّن مَّعِينٖ

18. ከ(ጠጅ) ምንጭ በብርጨቆዎች፣ በኩስኩስቶችና (እብሪቆች) በጽዋም በእነርሱ ዙሪያ እንዲዞሩ ይደረጋሉ።

18. ከ(ጠጅ) ምንጭ በብርጨቆዎች፣ በኩስኩስቶችና (እብሪቆች) በጽዋም በእነርሱ ዙሪያ እንዲዞሩ ይደረጋሉ።

لَّا يُصَدَّعُونَ عَنۡهَا وَلَا يُنزِفُونَ

19. ከእርሷ የራስ ምታት እንኳን አያገኛቸዉም:: አይሰክሩምም::

19. ከእርሷ የራስ ምታት እንኳን አያገኛቸዉም:: አይሰክሩምም::

وَفَٰكِهَةٖ مِّمَّا يَتَخَيَّرُونَ

20. ከእሸቶች ከሚመርጡት ዓይነት

20. ከእሸቶች ከሚመርጡት ዓይነት

وَلَحۡمِ طَيۡرٖ مِّمَّا يَشۡتَهُونَ

21. ከሚፈልጉት የበራሪ ስጋ ይዘው ይዞሩላቸዋል::

21. ከሚፈልጉት የበራሪ ስጋ ይዘው ይዞሩላቸዋል::

وَحُورٌ عِينٞ

22. ዓይናማዎች የሆኑ ነጫጭ ቆንጆ ሴቶችም አሏቸው::

22. ዓይናማዎች የሆኑ ነጫጭ ቆንጆ ሴቶችም አሏቸው::

كَأَمۡثَٰلِ ٱللُّؤۡلُوِٕ ٱلۡمَكۡنُونِ

23. ልክ እንደተሸፈነ ሉል የሚመስሉ::

23. ልክ እንደተሸፈነ ሉል የሚመስሉ::

جَزَآءَۢ بِمَا كَانُواْ يَعۡمَلُونَ

24. ለዚያ ይሰሩት በነበሩት መልካም ተግባር ምክንያት ዋጋ ይሆን ዘንድ ይህንን አደረግንላቸው።

24. ለዚያ ይሰሩት በነበሩት መልካም ተግባር ምክንያት ዋጋ ይሆን ዘንድ ይህንን አደረግንላቸው።

لَا يَسۡمَعُونَ فِيهَا لَغۡوٗا وَلَا تَأۡثِيمًا

25. በውስጧ ውድቅ ንግግርንና መወንጀልንም አይሰሙም።

25. በውስጧ ውድቅ ንግግርንና መወንጀልንም አይሰሙም።

إِلَّا قِيلٗا سَلَٰمٗا سَلَٰمٗا

26. ሰላም ሰላም መባባልን ግን ይሰማሉ::

26. ሰላም ሰላም መባባልን ግን ይሰማሉ::

وَأَصۡحَٰبُ ٱلۡيَمِينِ مَآ أَصۡحَٰبُ ٱلۡيَمِينِ

27. የቀኝ ጓዶች ምንኛ የከበሩ የቀኝ ጓዶች ናቸው::

27. የቀኝ ጓዶች ምንኛ የከበሩ የቀኝ ጓዶች ናቸው::

فِي سِدۡرٖ مَّخۡضُودٖ

28. በተቀፈቀፈ (እሾህ በሌለው) ቁርቁራ ውስጥ ናቸው::

28. በተቀፈቀፈ (እሾህ በሌለው) ቁርቁራ ውስጥ ናቸው::

وَطَلۡحٖ مَّنضُودٖ

29. ፍሬው በተነባበረ ሙዝ ዛፍም ውስጥ ናቸው።

29. ፍሬው በተነባበረ ሙዝ ዛፍም ውስጥ ናቸው።

وَظِلّٖ مَّمۡدُودٖ

30. በተዘረጋ ጥላ ስርም ናቸው::

30. በተዘረጋ ጥላ ስርም ናቸው::

وَمَآءٖ مَّسۡكُوبٖ

31. በሚንቧቡ ውሃ አጠገብም ናቸው::

31. በሚንቧቡ ውሃ አጠገብም ናቸው::

وَفَٰكِهَةٖ كَثِيرَةٖ

32. በብዙ ዓይነት ፍራፍሬዎችም ውስጥ ናቸው።

32. በብዙ ዓይነት ፍራፍሬዎችም ውስጥ ናቸው።

لَّا مَقۡطُوعَةٖ وَلَا مَمۡنُوعَةٖ

33. ምንጊዜም የማትቋረጥ የማትከለከልም የሆነች፤

33. ምንጊዜም የማትቋረጥ የማትከለከልም የሆነች፤

وَفُرُشٖ مَّرۡفُوعَةٍ

34. ከፍ በተደረጉ ምንጣፎች ላይም ናቸው።

34. ከፍ በተደረጉ ምንጣፎች ላይም ናቸው።

إِنَّآ أَنشَأۡنَٰهُنَّ إِنشَآءٗ

35. እኛ (የገነት ሴቶችን) አዲስ ፍጥረት አድርገን ፈጠርናቸው::

35. እኛ (የገነት ሴቶችን) አዲስ ፍጥረት አድርገን ፈጠርናቸው::

فَجَعَلۡنَٰهُنَّ أَبۡكَارًا

36. እናም ደናግሎችም አደረግናቸው::

36. እናም ደናግሎችም አደረግናቸው::

عُرُبًا أَتۡرَابٗا

37. ለባሎቻቸው ተሽሞርሟሪዎችና እኩያዎች አደረግናቸው::

37. ለባሎቻቸው ተሽሞርሟሪዎችና እኩያዎች አደረግናቸው::

لِّأَصۡحَٰبِ ٱلۡيَمِينِ

38. ለቀኝ ጓዶች አዘጋጀናቸው::

38. ለቀኝ ጓዶች አዘጋጀናቸው::

ثُلَّةٞ مِّنَ ٱلۡأَوَّلِينَ

39. ከፊተኞቹ ብዙ ቡድኖች ናቸው::

39. ከፊተኞቹ ብዙ ቡድኖች ናቸው::

وَثُلَّةٞ مِّنَ ٱلۡأٓخِرِينَ

40. ከኋለኞቹም ብዙ ቡድኖች ናቸው::

40. ከኋለኞቹም ብዙ ቡድኖች ናቸው::

وَأَصۡحَٰبُ ٱلشِّمَالِ مَآ أَصۡحَٰبُ ٱلشِّمَالِ

41. የግራ ጓዶችም ምንኛ የተዋረዱ የግራ ጓዶች ናቸው::

41. የግራ ጓዶችም ምንኛ የተዋረዱ የግራ ጓዶች ናቸው::

فِي سَمُومٖ وَحَمِيمٖ

42. በመርዛም ንፋስና በጣም በፈላ ውሃም ውስጥ ናቸው::

42. በመርዛም ንፋስና በጣም በፈላ ውሃም ውስጥ ናቸው::

وَظِلّٖ مِّن يَحۡمُومٖ

43. ከጥቁር ጭስም በሆነ ጥላ ውስጥ

43. ከጥቁር ጭስም በሆነ ጥላ ውስጥ

لَّا بَارِدٖ وَلَا كَرِيمٍ

44. ቀዝቃዛም መልካምም ያልሆነ

44. ቀዝቃዛም መልካምም ያልሆነ

إِنَّهُمۡ كَانُواْ قَبۡلَ ذَٰلِكَ مُتۡرَفِينَ

45. እነርሱ ከዚህ በፊት የነብያትን አስተምህሮት ወደ ጎን የተው የዱንያ ቅምጥሎች ነበሩና::

45. እነርሱ ከዚህ በፊት የነብያትን አስተምህሮት ወደ ጎን የተው የዱንያ ቅምጥሎች ነበሩና::

وَكَانُواْ يُصِرُّونَ عَلَى ٱلۡحِنثِ ٱلۡعَظِيمِ

46. በከባድ ኃጢአትም ላይ ይዘወትሩ ነበሩና::

46. በከባድ ኃጢአትም ላይ ይዘወትሩ ነበሩና::

وَكَانُواْ يَقُولُونَ أَئِذَا مِتۡنَا وَكُنَّا تُرَابٗا وَعِظَٰمًا أَءِنَّا لَمَبۡعُوثُونَ

47. (እንዲህ) ይሉ ነበርም፡ "ሞተን አፈር፣ አጥንቶችም በሆን ጊዜ እኛ የምንቀሰቀስ ነን?

47. (እንዲህ) ይሉ ነበርም፡ "ሞተን አፈር፣ አጥንቶችም በሆን ጊዜ እኛ የምንቀሰቀስ ነን?

أَوَءَابَآؤُنَا ٱلۡأَوَّلُونَ

48. "የፊተኞቹ አባቶቻችንንም (ይቀሰቀሳሉን)?" (ይሉ ነበር)

48. "የፊተኞቹ አባቶቻችንንም (ይቀሰቀሳሉን)?" (ይሉ ነበር)

قُلۡ إِنَّ ٱلۡأَوَّلِينَ وَٱلۡأٓخِرِينَ

49. (መልዕክተኛችን ሙሐመድ ሆይ!) "ፊተኞቹም ሆኑ ኋለኞቹ

49. (መልዕክተኛችን ሙሐመድ ሆይ!) "ፊተኞቹም ሆኑ ኋለኞቹ

لَمَجۡمُوعُونَ إِلَىٰ مِيقَٰتِ يَوۡمٖ مَّعۡلُومٖ

50. "በተወሰነ ቀን ቀጠሮ በእርግጥ ተሰብሳቢዎች ናቸው" በላቸው::

50. "በተወሰነ ቀን ቀጠሮ በእርግጥ ተሰብሳቢዎች ናቸው" በላቸው::

ثُمَّ إِنَّكُمۡ أَيُّهَا ٱلضَّآلُّونَ ٱلۡمُكَذِّبُونَ

51. ከዚያም እናንተ ጠማሞችና አስተባባዩች ሆይ!

51. ከዚያም እናንተ ጠማሞችና አስተባባዩች ሆይ!

لَأٓكِلُونَ مِن شَجَرٖ مِّن زَقُّومٖ

52. ከዘቁም ዛፍ በእርግጥ በይዎች ናችሁ::

52. ከዘቁም ዛፍ በእርግጥ በይዎች ናችሁ::

فَمَالِـُٔونَ مِنۡهَا ٱلۡبُطُونَ

53. ከእርሷም ሆዶቻችሁን ሞይዎች ናችሁ::

53. ከእርሷም ሆዶቻችሁን ሞይዎች ናችሁ::

فَشَٰرِبُونَ عَلَيۡهِ مِنَ ٱلۡحَمِيمِ

54. በእርሱ ላይም ከፈላ ውሃ ጠጪዎች ናችው::

54. በእርሱ ላይም ከፈላ ውሃ ጠጪዎች ናችው::

فَشَٰرِبُونَ شُرۡبَ ٱلۡهِيمِ

55. የተጠሙንም ግመሎች አጠጣጥ ብጤ ጠጪዎች ናቸው::

55. የተጠሙንም ግመሎች አጠጣጥ ብጤ ጠጪዎች ናቸው::

هَٰذَا نُزُلُهُمۡ يَوۡمَ ٱلدِّينِ

56. ይህ የፍርዱ ቀን መስተንግዷቸው ነው::

56. ይህ የፍርዱ ቀን መስተንግዷቸው ነው::

نَحۡنُ خَلَقۡنَٰكُمۡ فَلَوۡلَا تُصَدِّقُونَ

57. (ሰዎች ሆይ!) እኛ ፈጠርናችሁ አታምኑምን?

57. (ሰዎች ሆይ!) እኛ ፈጠርናችሁ አታምኑምን?

أَفَرَءَيۡتُم مَّا تُمۡنُونَ

58. በሴቶች ማህጸኖች የምታፈሱትን (የምትረጩትን ፍትወት) አያችሁን?

58. በሴቶች ማህጸኖች የምታፈሱትን (የምትረጩትን ፍትወት) አያችሁን?

ءَأَنتُمۡ تَخۡلُقُونَهُۥٓ أَمۡ نَحۡنُ ٱلۡخَٰلِقُونَ

59. እናንተ ትፈጥሩታላችሁን! ወይስ እኛ ነን ፈጣሪዎቹ?

59. እናንተ ትፈጥሩታላችሁን! ወይስ እኛ ነን ፈጣሪዎቹ?

نَحۡنُ قَدَّرۡنَا بَيۡنَكُمُ ٱلۡمَوۡتَ وَمَا نَحۡنُ بِمَسۡبُوقِينَ

60. እኛ ሞትን (ጊዜውን) በመካከላችሁ ወሰንን እኛም ተሸናፊዎች አይደለንም::

60. እኛ ሞትን (ጊዜውን) በመካከላችሁ ወሰንን እኛም ተሸናፊዎች አይደለንም::

عَلَىٰٓ أَن نُّبَدِّلَ أَمۡثَٰلَكُمۡ وَنُنشِئَكُمۡ فِي مَا لَا تَعۡلَمُونَ

61. ብጤዎቻችሁን በመለወጥና በዚያ በማታውቁትም ቅርጽ እናንተኑ በመፍጠር ላይ (አንሸነፍም)።

61. ብጤዎቻችሁን በመለወጥና በዚያ በማታውቁትም ቅርጽ እናንተኑ በመፍጠር ላይ (አንሸነፍም)።

وَلَقَدۡ عَلِمۡتُمُ ٱلنَّشۡأَةَ ٱلۡأُولَىٰ فَلَوۡلَا تَذَكَّرُونَ

62. የፊተኛይቱን አፈጣጠር በእርግጥ አውቃችኋል አትገነዘቡምን?

62. የፊተኛይቱን አፈጣጠር በእርግጥ አውቃችኋል አትገነዘቡምን?

أَفَرَءَيۡتُم مَّا تَحۡرُثُونَ

63. የምትዘሩትን (አዝርአት) አያችሁን

63. የምትዘሩትን (አዝርአት) አያችሁን

ءَأَنتُمۡ تَزۡرَعُونَهُۥٓ أَمۡ نَحۡنُ ٱلزَّٰرِعُونَ

64. እናንተ ታበቅሉታላችሁን? ወይስ እኛ አብቃዮቹ ነን?

64. እናንተ ታበቅሉታላችሁን? ወይስ እኛ አብቃዮቹ ነን?

لَوۡ نَشَآءُ لَجَعَلۡنَٰهُ حُطَٰمٗا فَظَلۡتُمۡ تَفَكَّهُونَ

65. ብንሻ ኖሮ ደረቅ ስብርብር ባረደግነው እና የምትደነቁም በሆናችሁ ነበር::

65. ብንሻ ኖሮ ደረቅ ስብርብር ባረደግነው እና የምትደነቁም በሆናችሁ ነበር::

إِنَّا لَمُغۡرَمُونَ

66. "እኛ በእዳ ተያዥዎች ነን::

66. "እኛ በእዳ ተያዥዎች ነን::

بَلۡ نَحۡنُ مَحۡرُومُونَ

67. "በእርግጥም እኛ (ከመጠቀም) የተከለክልን ነን" ትሉ ነበር።

67. "በእርግጥም እኛ (ከመጠቀም) የተከለክልን ነን" ትሉ ነበር።

أَفَرَءَيۡتُمُ ٱلۡمَآءَ ٱلَّذِي تَشۡرَبُونَ

68. ያንን ምትጠጡትን ውሃ አያችሁን?

68. ያንን ምትጠጡትን ውሃ አያችሁን?

ءَأَنتُمۡ أَنزَلۡتُمُوهُ مِنَ ٱلۡمُزۡنِ أَمۡ نَحۡنُ ٱلۡمُنزِلُونَ

69. እናንተ ከደመናው አወረዳችሁትን? ወይስ እኛ አውራጆቹ ነን?

69. እናንተ ከደመናው አወረዳችሁትን? ወይስ እኛ አውራጆቹ ነን?

لَوۡ نَشَآءُ جَعَلۡنَٰهُ أُجَاجٗا فَلَوۡلَا تَشۡكُرُونَ

70. ብንፈልግ ኖሮ መርጋጋ ባደረግነው ነበር:: አታመሰግኑምን?

70. ብንፈልግ ኖሮ መርጋጋ ባደረግነው ነበር:: አታመሰግኑምን?

أَفَرَءَيۡتُمُ ٱلنَّارَ ٱلَّتِي تُورُونَ

71. ያችንም የምትሰብቋትን እሳት አያችሁን?

71. ያችንም የምትሰብቋትን እሳት አያችሁን?

ءَأَنتُمۡ أَنشَأۡتُمۡ شَجَرَتَهَآ أَمۡ نَحۡنُ ٱلۡمُنشِـُٔونَ

72. እናንተ ዛፏን ፈጠራችሁን? ወይስ እኛ ፈጣሪዎቹ ነን?

72. እናንተ ዛፏን ፈጠራችሁን? ወይስ እኛ ፈጣሪዎቹ ነን?

نَحۡنُ جَعَلۡنَٰهَا تَذۡكِرَةٗ وَمَتَٰعٗا لِّلۡمُقۡوِينَ

73. እኛ ለገሀነም ማስታወሻ ለመንገደኞችም መጠቀሚያ አደረግናት::

73. እኛ ለገሀነም ማስታወሻ ለመንገደኞችም መጠቀሚያ አደረግናት::

فَسَبِّحۡ بِٱسۡمِ رَبِّكَ ٱلۡعَظِيمِ

74. የታላቁን ጌታህንም ስም አጥራው::

74. የታላቁን ጌታህንም ስም አጥራው::

۞ فَلَآ أُقۡسِمُ بِمَوَٰقِعِ ٱلنُّجُومِ

75. በከዋክብትም መጥለቂያዎች እምላለሁ::

75. በከዋክብትም መጥለቂያዎች እምላለሁ::

وَإِنَّهُۥ لَقَسَمٞ لَّوۡ تَعۡلَمُونَ عَظِيمٌ

76. እርሱም ብታውቁ ታላቅ መሀላ ነው::

76. እርሱም ብታውቁ ታላቅ መሀላ ነው::

إِنَّهُۥ لَقُرۡءَانٞ كَرِيمٞ

77. እርሱ የተከበረ ቁርኣን ነው::

77. እርሱ የተከበረ ቁርኣን ነው::

فِي كِتَٰبٖ مَّكۡنُونٖ

78. በተጠበቀ መጽሐፍ ውስጥም ነው::

78. በተጠበቀ መጽሐፍ ውስጥም ነው::

لَّا يَمَسُّهُۥٓ إِلَّا ٱلۡمُطَهَّرُونَ

79. የተጥራሩት እንጂ ሌላ አይነካዉም::

79. የተጥራሩት እንጂ ሌላ አይነካዉም::

تَنزِيلٞ مِّن رَّبِّ ٱلۡعَٰلَمِينَ

80. ከዓለማት ጌታ የተወረደ ነው::

80. ከዓለማት ጌታ የተወረደ ነው::

أَفَبِهَٰذَا ٱلۡحَدِيثِ أَنتُم مُّدۡهِنُونَ

81. በዚህ ንግግር እናንተ ቸልተኞች ናችሁን?

81. በዚህ ንግግር እናንተ ቸልተኞች ናችሁን?

وَتَجۡعَلُونَ رِزۡقَكُمۡ أَنَّكُمۡ تُكَذِّبُونَ

82. ሲሳያችሁንም (ዝናብን) እናንተ የምታስተባበሉት ታደርጋላችሁን?

82. ሲሳያችሁንም (ዝናብን) እናንተ የምታስተባበሉት ታደርጋላችሁን?

فَلَوۡلَآ إِذَا بَلَغَتِ ٱلۡحُلۡقُومَ

83. ነፍስ ጉሮሮንም በደረሰች ጊዜ::

83. ነፍስ ጉሮሮንም በደረሰች ጊዜ::

وَأَنتُمۡ حِينَئِذٖ تَنظُرُونَ

84. እናንተ ያን ጊዜ የምታዩ ስትሆኑ፤

84. እናንተ ያን ጊዜ የምታዩ ስትሆኑ፤

وَنَحۡنُ أَقۡرَبُ إِلَيۡهِ مِنكُمۡ وَلَٰكِن لَّا تُبۡصِرُونَ

85. እኛም ግን እናንተ አታዩም እንጂ ከናንተ ይልቅ ወደ እርሱ የቀረብን ነን::

85. እኛም ግን እናንተ አታዩም እንጂ ከናንተ ይልቅ ወደ እርሱ የቀረብን ነን::

فَلَوۡلَآ إِن كُنتُمۡ غَيۡرَ مَدِينِينَ

86. የማትዳኙም ከሆናችሁ

86. የማትዳኙም ከሆናችሁ

تَرۡجِعُونَهَآ إِن كُنتُمۡ صَٰدِقِينَ

87. እውነተኞች እንደሆናችሁ ነፍሲቱን ወደ አካል ለምን አትመልሷትም?

87. እውነተኞች እንደሆናችሁ ነፍሲቱን ወደ አካል ለምን አትመልሷትም?

فَأَمَّآ إِن كَانَ مِنَ ٱلۡمُقَرَّبِينَ

88. እናም ሟቹ ከባለሟሎቹ ከሆነም፤

88. እናም ሟቹ ከባለሟሎቹ ከሆነም፤

فَرَوۡحٞ وَرَيۡحَانٞ وَجَنَّتُ نَعِيمٖ

89. ለእርሱ እረፍት መልካም ሲሳይና የመጠቀሚያ ገነት አለው::

89. ለእርሱ እረፍት መልካም ሲሳይና የመጠቀሚያ ገነት አለው::

وَأَمَّآ إِن كَانَ مِنۡ أَصۡحَٰبِ ٱلۡيَمِينِ

90. ሟቹ ከቀኝ ጓዶችም ከሆነ

90. ሟቹ ከቀኝ ጓዶችም ከሆነ

فَسَلَٰمٞ لَّكَ مِنۡ أَصۡحَٰبِ ٱلۡيَمِينِ

91."ከቀኝ ጓዶች ስለሆንክ ላንተ ሰላም ነው የሚገባህ" ይባላል።

91."ከቀኝ ጓዶች ስለሆንክ ላንተ ሰላም ነው የሚገባህ" ይባላል።

وَأَمَّآ إِن كَانَ مِنَ ٱلۡمُكَذِّبِينَ ٱلضَّآلِّينَ

92. ሟች ከእነዚያ ከሚያስተባብሉት ጠማማዎች ከሆነ ደግሞ

92. ሟች ከእነዚያ ከሚያስተባብሉት ጠማማዎች ከሆነ ደግሞ

فَنُزُلٞ مِّنۡ حَمِيمٖ

93. ከፈላ ውሃ የሆነ መስተንግዶ አለለት::

93. ከፈላ ውሃ የሆነ መስተንግዶ አለለት::

وَتَصۡلِيَةُ جَحِيمٍ

94. በገሀነም መቃጠልም አለለት::

94. በገሀነም መቃጠልም አለለት::

إِنَّ هَٰذَا لَهُوَ حَقُّ ٱلۡيَقِينِ

95. ይህ እርሱ እርግጠኛው እውነት ነው::

95. ይህ እርሱ እርግጠኛው እውነት ነው::

فَسَبِّحۡ بِٱسۡمِ رَبِّكَ ٱلۡعَظِيمِ

96. (መልዕክተኛችን ሙሐመድ ሆይ!) የታላቁ ጌታህን ስም አጥራው::

96. (መልዕክተኛችን ሙሐመድ ሆይ!) የታላቁ ጌታህን ስም አጥራው::
Footer Include