अम्हरी अनुवाद : अफ्रिका एकेडेमी ।
अनुवाद : मुहम्मद ज़ैन ज़हरुद्दिन । अफ्रिका एकेडेमीबाट प्रकाशित ।
وَٱلسَّمَآءِ وَٱلطَّارِقِ
1. በሰማዩ እና ሌሊት በሚመጣውም እምላለሁ።
وَمَآ أَدۡرَىٰكَ مَا ٱلطَّارِقُ
2. (መልዕክተኛችን ሙሐመድ ሆይ!) የሌሊት መጪው ምን እንደሆነ ምን አሳወቀህ?
ٱلنَّجۡمُ ٱلثَّاقِبُ
3. ጨለማውን ሰንጣቂ ኮከብ ነው::
إِن كُلُّ نَفۡسٖ لَّمَّا عَلَيۡهَا حَافِظٞ
4. ነፍስ ሁሉ በእርሷ ላይ ጠባቂ ያለባት እንጂ ሌላ አይደለችም::
فَلۡيَنظُرِ ٱلۡإِنسَٰنُ مِمَّ خُلِقَ
5. የሰው ልጅ ከምን እንደተፈጠረ ይመልከት፤
خُلِقَ مِن مَّآءٖ دَافِقٖ
6. ከተስፈንጣሪ ውሃ (የዘር ፈሳሽ) ተፈጠረ::
يَخۡرُجُ مِنۢ بَيۡنِ ٱلصُّلۡبِ وَٱلتَّرَآئِبِ
7. ከጀርባና ከእርግብግቢቶች መካከል የሚወጣ ከሆነ የዘር ፈሳሽ ውሃ (ተፈጠረ)።
إِنَّهُۥ عَلَىٰ رَجۡعِهِۦ لَقَادِرٞ
8. አላህ እርሱን በመመለሱ ላይ በእርግጥ ቻይ ነው::
يَوۡمَ تُبۡلَى ٱلسَّرَآئِرُ
9. ሚስጥሮች በሚገለጹበት ቀን፤
فَمَا لَهُۥ مِن قُوَّةٖ وَلَا نَاصِرٖ
10. (ለሰው) ምንም ኃይልና ረዳት አይኖረዉም::
وَٱلسَّمَآءِ ذَاتِ ٱلرَّجۡعِ
11. የመመለስ ባለቤት (ዝናባማ) በሆነችው ሰማይ እምላለሁ::
وَٱلۡأَرۡضِ ذَاتِ ٱلصَّدۡعِ
12. (በበቃይ) የመሰንጠቅ ባለቤት በሆነችው ምድርም እምላለሁ::
إِنَّهُۥ لَقَوۡلٞ فَصۡلٞ
13. እርሱ (ቁርኣን)፤ (እውነትን ከውሸት) የሚለይ (የአላህ) ቃል ነው።
وَمَا هُوَ بِٱلۡهَزۡلِ
14. እርሱም ቀልድ አይደለም።
إِنَّهُمۡ يَكِيدُونَ كَيۡدٗا
15. እነርሱ በእርግጥ ተንኮልን ያሴራሉ (ይሸርባሉ)::
وَأَكِيدُ كَيۡدٗا
16. እኔ ተንኮልንም እመልሳለሁ (አመክናለሁ)::
فَمَهِّلِ ٱلۡكَٰفِرِينَ أَمۡهِلۡهُمۡ رُوَيۡدَۢا
17. (መልዕክተኛችን ሙሐመድ ሆይ!) ከሓዲያንን ቀን ሰጣቸው:: ጥቂትን ጊዜ አቆያቸው (ታገሳቸው)::
مشاركة عبر