ߊߡߎߤߊߙߌߞߊ߲ ߘߟߊߡߌ߬ߘߊ - ߡߎ߬ߤ߭ߊߡߡߊߘߎ߫ ߛ߫ߊ߯ߘߌߞ߫ߎ߫ ߓߟߏ߫
ߗߍ߬ߡߐ߯ ߡߎ߬ߤ߭ߊߡߡߊߘߎ߫ ߛ߫ߊ߯ߘߌߞߎ߫ ߣߌ߫ ߡߎ߬ߤ߭ߊߡߡߊߘߎ߫ ߝߌߟߊߣߊ߲ ߤ߭ߊ߬ߓߌ߯ߓߎ߫ ߟߊ߫ ߘߟߊߡߌߘߊ ߟߋ߬. ߊ߬ ߛߊߞߍ߫ ߘߊ߫ ߙߎ߬ߥߊ߯ߘߎ߫ ߘߟߊߡߌߘߊ ߝߊ߲ߓߊ ߟߊ߫ ߞߎ߲߬ߠߊ߬ߛߌ߰ߟߌ ߟߋ߫ ߞߐ߬ߣߐߡߊ߬߸ ߘߟߊߡߌߘߊ ߓߊߖߏߣߊ ߦߋ߫ ߓߟߏߞߘߐ߫ ߖߌ߲ߞߌ߲߫ ߞߊߡߵߊ߬ ߡߊ߬ ߡߙߌߣߊ߲ߦߌߘߊ ߘߐ߫ ߊ߬ ߞߊ߲߬߸ ߊ߬ ߣߴߊ߬ ߡߐ߬ߟߐ߲߬ߦߊ ߣߴߊ߬ ߟߊߥߙߎߞߌ ߘߊߓߊ߲ߠߌ߲.
وَٱلَّيۡلِ إِذَا يَغۡشَىٰ
በሌሊቱ እምላለሁ (በጨለማው) በሚሸፍን ጊዜ፡፡
وَٱلنَّهَارِ إِذَا تَجَلَّىٰ
በቀኑም፤ በተገለጸ ጊዜ፡፡
وَمَا خَلَقَ ٱلذَّكَرَ وَٱلۡأُنثَىٰٓ
ወንድንና ሴትን በፈጠረውም (አምላክ እምላለሁ)፡፡
إِنَّ سَعۡيَكُمۡ لَشَتَّىٰ
ሥራችሁ በእርግጥ የተለያየ ነው፡፡
فَأَمَّا مَنۡ أَعۡطَىٰ وَٱتَّقَىٰ
የሰጠ ሰውማ ጌታውን የፈራም፡፡
وَصَدَّقَ بِٱلۡحُسۡنَىٰ
በመልካሚቱም (እምነት) ያረጋገጠ፤
فَسَنُيَسِّرُهُۥ لِلۡيُسۡرَىٰ
ለገሪቱ ሥራ እናዘጋጀዋለን፡፡
وَأَمَّا مَنۢ بَخِلَ وَٱسۡتَغۡنَىٰ
የሰሰተ ሰውማ የተብቃቃም፤ (በራሱ የተመካ)፤
وَكَذَّبَ بِٱلۡحُسۡنَىٰ
በመልካሚቱ (እምነት) ያሰተባበለም፤
فَسَنُيَسِّرُهُۥ لِلۡعُسۡرَىٰ
ለክፉይቱ ሥራ እናዘጋጀዋለን፡፡
وَمَا يُغۡنِي عَنۡهُ مَالُهُۥٓ إِذَا تَرَدَّىٰٓ
በወደቀም ጊዜ ገንዘቡ ከእርሱ ምንም አይጠቅመውም፡፡
إِنَّ عَلَيۡنَا لَلۡهُدَىٰ
ቅኑን መንገድ መግለጽ በእኛ ላይ አለብን፡፡
وَإِنَّ لَنَا لَلۡأٓخِرَةَ وَٱلۡأُولَىٰ
መጨረሻይቱም መጀመሪያይቱም ዓለም የእኛ ናቸው፡፡
فَأَنذَرۡتُكُمۡ نَارٗا تَلَظَّىٰ
የምትንቀለቀልንም እሳት አስጠነቀቅኳችሁ (በላቸው)፡፡
لَا يَصۡلَىٰهَآ إِلَّا ٱلۡأَشۡقَى
ከጠማማ በቀር ሌላ የማይገባት የኾነችን፡፡
ٱلَّذِي كَذَّبَ وَتَوَلَّىٰ
ያ ያስተባበለና ከትዕዛዝ የሸሸው፡፡
وَسَيُجَنَّبُهَا ٱلۡأَتۡقَى
አላህን በጣም ፈሪውም በእርግጥ ይርቃታል፡፡
ٱلَّذِي يُؤۡتِي مَالَهُۥ يَتَزَكَّىٰ
ያ የሚጥራራ ኾኖ ገንዘቡን (ለድኾች) የሚሰጠው፡፡
وَمَا لِأَحَدٍ عِندَهُۥ مِن نِّعۡمَةٖ تُجۡزَىٰٓ
ለአንድም ሰው እርሱ ዘንድ የምትመለስ ውለታ የለችም፡፡
إِلَّا ٱبۡتِغَآءَ وَجۡهِ رَبِّهِ ٱلۡأَعۡلَىٰ
ግን የታላቅ ጌታውን ውዴታ ለመፈለግ (ይህንን ሠራ)፡፡
وَلَسَوۡفَ يَرۡضَىٰ
ወደፊትም በእርግጥ ይደሰታል፡፡
مشاركة عبر