Fassarar Amhariyanci - Muhammad Sadiƙ
Sheikh Muhammad Sadiƙ da Muhammad Sani Habib suka fassarata. An sabunta ta ƙarƙashin kulawar Cibiyar fassara ta Ruwad, an bada damar karanta fassarar ta asali dan manufar bayyanar da ra'ayi da daidaitata da kuma ci gaba mai ɗorewa.
وَٱلشَّمۡسِ وَضُحَىٰهَا
በፀሐይና በብርሃኗ እምላለሁ፡፡
وَٱلۡقَمَرِ إِذَا تَلَىٰهَا
በጨረቃም በተከተላት ጊዜ፤
وَٱلنَّهَارِ إِذَا جَلَّىٰهَا
በቀኑም (ፀሐይን) በገለጻት ጊዜ፤
وَٱلَّيۡلِ إِذَا يَغۡشَىٰهَا
በሌሊቱም በሸፈናት ጊዜ፤
وَٱلسَّمَآءِ وَمَا بَنَىٰهَا
በሰማይቱም በገነባትም (ጌታ)፤
وَٱلۡأَرۡضِ وَمَا طَحَىٰهَا
በምድሪቱም በዘረጋትም፤
وَنَفۡسٖ وَمَا سَوَّىٰهَا
በነፍስም ባስተካከላትም፤
فَأَلۡهَمَهَا فُجُورَهَا وَتَقۡوَىٰهَا
አመጽዋንና ፍርሃትዋንም ባሳወቃት (አምላክ እምላለሁ)፡፡
قَدۡ أَفۡلَحَ مَن زَكَّىٰهَا
(ከኀጢኣት) ያጠራት ሰው ፍላጎቱን በእርግጥ አገኘ፡፡
وَقَدۡ خَابَ مَن دَسَّىٰهَا
(በኀጢኣት) የሸፈናትም ሰው በእውነት አፈረ፡፡
كَذَّبَتۡ ثَمُودُ بِطَغۡوَىٰهَآ
ሠሙድ ወሰን በማለፍዋ አስተባበለች፡፡
إِذِ ٱنۢبَعَثَ أَشۡقَىٰهَا
ጠማማዋ በተንቀሳቀሰ ጊዜ፡፡
فَقَالَ لَهُمۡ رَسُولُ ٱللَّهِ نَاقَةَ ٱللَّهِ وَسُقۡيَٰهَا
ለእነርሱም የአላህ መልክተኛ (ሷሊህ) «የአላህን ግመል የመጠጥ ተራዋንም (ተጠንቀቁ)» አላቸው፡፡
فَكَذَّبُوهُ فَعَقَرُوهَا فَدَمۡدَمَ عَلَيۡهِمۡ رَبُّهُم بِذَنۢبِهِمۡ فَسَوَّىٰهَا
አስተባበሉትም፡፡ (ቋንጃዋን) ወጓትም፡፡ በኀጢኣታቸውም ምክንያት ጌታቸው (ቅጣትን) በእነርሱ ላይ ደመደመባቸው፤ አስተካከላትም፡፡
وَلَا يَخَافُ عُقۡبَٰهَا
ፍጻሜዋንም (የምታስከትለውን) አይፈራም፡፡
مشاركة عبر