TRADUZIONE AMARICA - Muhammed Sadiq
Traduzione dei significati del Nobile Corano
Traduzione a cura di Shaikh Muhammad Sadeq e Muhammad Ath-Thany Habib, curata dal Pioneer Translation Center. La traduzione è disponibile per consultazione, con l’obiettivo di raccogliere osservazioni, valutazioni e favorire un miglioramento continuo
ٱلۡقَارِعَةُ
ቆርቋሪይቱ (ጩኸት)፤
مَا ٱلۡقَارِعَةُ
ምን አስደናቂ ቆርቋሪ ናት!
وَمَآ أَدۡرَىٰكَ مَا ٱلۡقَارِعَةُ
ቆርቋሪይቱም ምን እንደኾነች ምን አሳወቀህ?
يَوۡمَ يَكُونُ ٱلنَّاسُ كَٱلۡفَرَاشِ ٱلۡمَبۡثُوثِ
ሰዎች እንደ ተበታተነ ቢራቢሮ (ወይም ኩብኩባ) በሚኾኑበት ቀን፤
وَتَكُونُ ٱلۡجِبَالُ كَٱلۡعِهۡنِ ٱلۡمَنفُوشِ
ጋራዎችም እንደ ተነደፈ ሱፍ በሚኾኑበት (ቀን ልቦችን በድንጋጤ ትቆረቁራለች፡፡)
فَأَمَّا مَن ثَقُلَتۡ مَوَٰزِينُهُۥ
ሚዛኖቹ የከበዱለት ሰውማ፤
فَهُوَ فِي عِيشَةٖ رَّاضِيَةٖ
እርሱ በምትወደድ ኑሮ ውስጥ ይኾናል፡፡
وَأَمَّا مَنۡ خَفَّتۡ مَوَٰزِينُهُۥ
ሚዛኖቹም የቀለሉበት ሰውማ፤
فَأُمُّهُۥ هَاوِيَةٞ
መኖሪያው ሃዊያህ ናት
وَمَآ أَدۡرَىٰكَ مَا هِيَهۡ
እርሷም ምን እንደ ኾነች ምን አሳወቀህ?
نَارٌ حَامِيَةُۢ
(እርሷ) በጣም ተኳሳ እሳት ናት፡፡
share_via