Header Include

امهري ژباړه

په اماریک ژبه کې د قرآن کریم د معنی ژباړه، د شیخ محمد صادق او محمد الثاني لخوا شوې ده دا ژباړه د مرکز رواد الترجمة تر څارنې لاندې اصلاح شوې او اصلي ژباړه د نظر څرګندولو، ارزونې او دوامداره پرمختګ لپاره شتون لري.

QR Code https://quran.islamcontent.com/ps/amharic_sadiq

وَٱلۡعَٰدِيَٰتِ ضَبۡحٗا

እያለከለኩ ሩዋጮች በኾኑት (ፈረሶች) እምላለሁ፡፡

እያለከለኩ ሩዋጮች በኾኑት (ፈረሶች) እምላለሁ፡፡

فَٱلۡمُورِيَٰتِ قَدۡحٗا

(በሰኮናቸው) እያጋጩ እሳትን አውጪዎች በኾኑትም፤

(በሰኮናቸው) እያጋጩ እሳትን አውጪዎች በኾኑትም፤

فَٱلۡمُغِيرَٰتِ صُبۡحٗا

በማለዳ ወራሪዎች በኾኑትም፤

በማለዳ ወራሪዎች በኾኑትም፤

فَأَثَرۡنَ بِهِۦ نَقۡعٗا

በእርሱ አቧራን በቀሰቀሱትም፤

በእርሱ አቧራን በቀሰቀሱትም፤

فَوَسَطۡنَ بِهِۦ جَمۡعًا

በ(ጠላት) ክቢ መካከል በእርሱ (በጧት) በተጋፈጡትም እምላለሁ፡፡

በ(ጠላት) ክቢ መካከል በእርሱ (በጧት) በተጋፈጡትም እምላለሁ፡፡

إِنَّ ٱلۡإِنسَٰنَ لِرَبِّهِۦ لَكَنُودٞ

ሰው ለጌታው ብርቱ ከሓዲ ነው፡፡

ሰው ለጌታው ብርቱ ከሓዲ ነው፡፡

وَإِنَّهُۥ عَلَىٰ ذَٰلِكَ لَشَهِيدٞ

እርሱም በዚህ ላይ መስካሪ ነው፡፡

እርሱም በዚህ ላይ መስካሪ ነው፡፡

وَإِنَّهُۥ لِحُبِّ ٱلۡخَيۡرِ لَشَدِيدٌ

እርሱም ገንዘብን ለመውደድ በጣም ብርቱ ነው፡፡

እርሱም ገንዘብን ለመውደድ በጣም ብርቱ ነው፡፡

۞ أَفَلَا يَعۡلَمُ إِذَا بُعۡثِرَ مَا فِي ٱلۡقُبُورِ

(ሰው) አያውቅምን? በመቃብሮች ያሉት (ሙታን) በተቀሰቀሱ ጊዜ፤

(ሰው) አያውቅምን? በመቃብሮች ያሉት (ሙታን) በተቀሰቀሱ ጊዜ፤

وَحُصِّلَ مَا فِي ٱلصُّدُورِ

በልቦች ውስጥ ያለውም ሁሉ በተገለጸ ጊዜ (እንዴት እንደሚኾን)፡፡

በልቦች ውስጥ ያለውም ሁሉ በተገለጸ ጊዜ (እንዴት እንደሚኾን)፡፡

إِنَّ رَبَّهُم بِهِمۡ يَوۡمَئِذٖ لَّخَبِيرُۢ

ጌታቸው በዚያ ቀን በእነርሱ (ነገር) በእርግጥ ውስጠ አዋቂ ነው፡፡

ጌታቸው በዚያ ቀን በእነርሱ (ነገር) በእርግጥ ውስጠ አዋቂ ነው፡፡
Footer Include