Header Include

امهري ژباړه

په اماریک ژبه کې د قرآن کریم د معنی ژباړه، د شیخ محمد صادق او محمد الثاني لخوا شوې ده دا ژباړه د مرکز رواد الترجمة تر څارنې لاندې اصلاح شوې او اصلي ژباړه د نظر څرګندولو، ارزونې او دوامداره پرمختګ لپاره شتون لري.

QR Code https://quran.islamcontent.com/ps/amharic_sadiq

عَمَّ يَتَسَآءَلُونَ

ከምን ነገር ይጠያየቃሉ?

ከምን ነገር ይጠያየቃሉ?

عَنِ ٱلنَّبَإِ ٱلۡعَظِيمِ

ከታላቁ ዜና (ከቁርኣን ይጠያየቃሉ)፡፡

ከታላቁ ዜና (ከቁርኣን ይጠያየቃሉ)፡፡

ٱلَّذِي هُمۡ فِيهِ مُخۡتَلِفُونَ

ከዚያ እነርሱ በእርሱ የተለያዩበት ከኾነው፡፡

ከዚያ እነርሱ በእርሱ የተለያዩበት ከኾነው፡፡

كَلَّا سَيَعۡلَمُونَ

ይከልከሉ፤ ወደፊት (የሚደርስበቸውን) በእርግጥ ያውቃሉ፡፡

ይከልከሉ፤ ወደፊት (የሚደርስበቸውን) በእርግጥ ያውቃሉ፡፡

ثُمَّ كَلَّا سَيَعۡلَمُونَ

ከዚያም ይከልከሉ፤ ወደፊት ያውቃሉ፡፡

ከዚያም ይከልከሉ፤ ወደፊት ያውቃሉ፡፡

أَلَمۡ نَجۡعَلِ ٱلۡأَرۡضَ مِهَٰدٗا

ምድርን ምንጣፍ አላደረግንምን?

ምድርን ምንጣፍ አላደረግንምን?

وَٱلۡجِبَالَ أَوۡتَادٗا

ጋራዎችንም ችካሎች አላደረግንምን?

ጋራዎችንም ችካሎች አላደረግንምን?

وَخَلَقۡنَٰكُمۡ أَزۡوَٰجٗا

ብዙ ዓይነቶችም አድርገን ፈጠርናችሁ፡፡

ብዙ ዓይነቶችም አድርገን ፈጠርናችሁ፡፡

وَجَعَلۡنَا نَوۡمَكُمۡ سُبَاتٗا

እንቅልፋችሁንም ዕረፍት አደረግን፡፡

እንቅልፋችሁንም ዕረፍት አደረግን፡፡

وَجَعَلۡنَا ٱلَّيۡلَ لِبَاسٗا

ሌሊቱንም ልባስ አደረግን፡፡

ሌሊቱንም ልባስ አደረግን፡፡

وَجَعَلۡنَا ٱلنَّهَارَ مَعَاشٗا

ቀኑንም (ለኑሮ) መስሪያ አደረግን፡፡

ቀኑንም (ለኑሮ) መስሪያ አደረግን፡፡

وَبَنَيۡنَا فَوۡقَكُمۡ سَبۡعٗا شِدَادٗا

ከበላያችሁም ሰባትን ብርቱዎች (ሰማያት) ገነባን፡፡

ከበላያችሁም ሰባትን ብርቱዎች (ሰማያት) ገነባን፡፡

وَجَعَلۡنَا سِرَاجٗا وَهَّاجٗا

አንጸባራቂ ብርሃንንም አደረግን፡፡

አንጸባራቂ ብርሃንንም አደረግን፡፡

وَأَنزَلۡنَا مِنَ ٱلۡمُعۡصِرَٰتِ مَآءٗ ثَجَّاجٗا

ከአረገዙት ደመናዎችም ተንቧቢ ውሃን አወረድን፡፡

ከአረገዙት ደመናዎችም ተንቧቢ ውሃን አወረድን፡፡

لِّنُخۡرِجَ بِهِۦ حَبّٗا وَنَبَاتٗا

በእርሱ እኽልንና ቅጠላ ቅጠልን እናወጣ ዘንድ (አወረድን)፡፡

በእርሱ እኽልንና ቅጠላ ቅጠልን እናወጣ ዘንድ (አወረድን)፡፡

وَجَنَّٰتٍ أَلۡفَافًا

የተቆላለፉ አትክልቶችንም፡፡

የተቆላለፉ አትክልቶችንም፡፡

إِنَّ يَوۡمَ ٱلۡفَصۡلِ كَانَ مِيقَٰتٗا

የመለያው ቀን የተወሰነ ጊዜ ነው፡፡

የመለያው ቀን የተወሰነ ጊዜ ነው፡፡

يَوۡمَ يُنفَخُ فِي ٱلصُّورِ فَتَأۡتُونَ أَفۡوَاجٗا

በቀንዱ በሚነፋና የተለያዩ ጭፍሮች ኾናችሁ በምትመጡ ቀን ነው፡፡

በቀንዱ በሚነፋና የተለያዩ ጭፍሮች ኾናችሁ በምትመጡ ቀን ነው፡፡

وَفُتِحَتِ ٱلسَّمَآءُ فَكَانَتۡ أَبۡوَٰبٗا

ሰማይም በምትከፈትና (ባለ) ደጃፎችም በምትኾንበት፡፡

ሰማይም በምትከፈትና (ባለ) ደጃፎችም በምትኾንበት፡፡

وَسُيِّرَتِ ٱلۡجِبَالُ فَكَانَتۡ سَرَابًا

ጋራዎችም በሚነዱበት (እንደ) ሲሪብዱም በሚኾኑበት (ቀን) ነው፡፡

ጋራዎችም በሚነዱበት (እንደ) ሲሪብዱም በሚኾኑበት (ቀን) ነው፡፡

إِنَّ جَهَنَّمَ كَانَتۡ مِرۡصَادٗا

ገሀነም መጠባበቂያ (ስፍራ) ናት፡፡

ገሀነም መጠባበቂያ (ስፍራ) ናት፡፡

لِّلطَّٰغِينَ مَـَٔابٗا

ለሕግ ተላላፊዎች መመለሻ ስትኾን፡፡

ለሕግ ተላላፊዎች መመለሻ ስትኾን፡፡

لَّٰبِثِينَ فِيهَآ أَحۡقَابٗا

በውስጧ ብዙን ዘመናት ነዋሪዎች ሲኾኑ፤

በውስጧ ብዙን ዘመናት ነዋሪዎች ሲኾኑ፤

لَّا يَذُوقُونَ فِيهَا بَرۡدٗا وَلَا شَرَابًا

በውስጧ ቅዝቃዜንም መጠጥንም አይቀምሱም፡፡

በውስጧ ቅዝቃዜንም መጠጥንም አይቀምሱም፡፡

إِلَّا حَمِيمٗا وَغَسَّاقٗا

ግን ሙቅ ውሃንና እዥን (ይቀምሳሉ)፡፡

ግን ሙቅ ውሃንና እዥን (ይቀምሳሉ)፡፡

جَزَآءٗ وِفَاقًا

ተስማሚን ምንዳ ይምመነዳሉ፡፡

ተስማሚን ምንዳ ይምመነዳሉ፡፡

إِنَّهُمۡ كَانُواْ لَا يَرۡجُونَ حِسَابٗا

እነርሱ ምርመራን የማይፈሩ ነበሩና፡፡

እነርሱ ምርመራን የማይፈሩ ነበሩና፡፡

وَكَذَّبُواْ بِـَٔايَٰتِنَا كِذَّابٗا

በአንቀጾቻችንም ማስተባበልን አስተባበሉና፡፡

በአንቀጾቻችንም ማስተባበልን አስተባበሉና፡፡

وَكُلَّ شَيۡءٍ أَحۡصَيۡنَٰهُ كِتَٰبٗا

ነገሩንም ሁሉ የተጻፈ ሲኾን አጠቃለልነው፡፡

ነገሩንም ሁሉ የተጻፈ ሲኾን አጠቃለልነው፡፡

فَذُوقُواْ فَلَن نَّزِيدَكُمۡ إِلَّا عَذَابًا

ቅመሱም ቅጣትንም እንጅ (ሌላን) አንጨምራችሁም (ይባላሉ)፡፡

ቅመሱም ቅጣትንም እንጅ (ሌላን) አንጨምራችሁም (ይባላሉ)፡፡

إِنَّ لِلۡمُتَّقِينَ مَفَازًا

ለጥንቁቆቹ መዳኛ ስፍራ አልላቸው፡፡

ለጥንቁቆቹ መዳኛ ስፍራ አልላቸው፡፡

حَدَآئِقَ وَأَعۡنَٰبٗا

አትክልቶችና ወይኖችም፡፡

አትክልቶችና ወይኖችም፡፡

وَكَوَاعِبَ أَتۡرَابٗا

እኩያዎች የኾኑ ጡተ ጉቻማዎችም፡፡

እኩያዎች የኾኑ ጡተ ጉቻማዎችም፡፡

وَكَأۡسٗا دِهَاقٗا

የተሞሉ ብርጭቆዎችም፡፡

የተሞሉ ብርጭቆዎችም፡፡

لَّا يَسۡمَعُونَ فِيهَا لَغۡوٗا وَلَا كِذَّٰبٗا

በውስጧ ትርፍ ቃልንም ማስዋሸትንም አይሰሙም፡፡

በውስጧ ትርፍ ቃልንም ማስዋሸትንም አይሰሙም፡፡

جَزَآءٗ مِّن رَّبِّكَ عَطَآءً حِسَابٗا

ከጌታህ የኾነን ምንዳ በቂ ስጦታን (ተሰጡ)፡፡

ከጌታህ የኾነን ምንዳ በቂ ስጦታን (ተሰጡ)፡፡

رَّبِّ ٱلسَّمَٰوَٰتِ وَٱلۡأَرۡضِ وَمَا بَيۡنَهُمَا ٱلرَّحۡمَٰنِۖ لَا يَمۡلِكُونَ مِنۡهُ خِطَابٗا

የሰማያትና የምድር በመካከላቸውም ያለው ሁሉ ጌታ በጣም አዛኝ ከኾነው (ተመነዱ)፡፡ ከእርሱ ጋር መነጋገርን አይችሉም፡፡

የሰማያትና የምድር በመካከላቸውም ያለው ሁሉ ጌታ በጣም አዛኝ ከኾነው (ተመነዱ)፡፡ ከእርሱ ጋር መነጋገርን አይችሉም፡፡

يَوۡمَ يَقُومُ ٱلرُّوحُ وَٱلۡمَلَٰٓئِكَةُ صَفّٗاۖ لَّا يَتَكَلَّمُونَ إِلَّا مَنۡ أَذِنَ لَهُ ٱلرَّحۡمَٰنُ وَقَالَ صَوَابٗا

መንፈሱ (ጂብሪል) መላእክቶቹም የተሰለፉ ኾነው በሚቆሙ ቀን አል-ረሕማን ለእርሱ የፈቀደለትና ትክክለኛን ቃል ያለ ሰው ቢኾን እንጅ (መነጋገርን አይችሉም)፡፡

መንፈሱ (ጂብሪል) መላእክቶቹም የተሰለፉ ኾነው በሚቆሙ ቀን አል-ረሕማን ለእርሱ የፈቀደለትና ትክክለኛን ቃል ያለ ሰው ቢኾን እንጅ (መነጋገርን አይችሉም)፡፡

ذَٰلِكَ ٱلۡيَوۡمُ ٱلۡحَقُّۖ فَمَن شَآءَ ٱتَّخَذَ إِلَىٰ رَبِّهِۦ مَـَٔابًا

ይህ የተረጋገጠው ቀን ነው፡፡ የሻም ሰው ወደ ጌታው መመለስን ይይዛል፡፡

ይህ የተረጋገጠው ቀን ነው፡፡ የሻም ሰው ወደ ጌታው መመለስን ይይዛል፡፡

إِنَّآ أَنذَرۡنَٰكُمۡ عَذَابٗا قَرِيبٗا يَوۡمَ يَنظُرُ ٱلۡمَرۡءُ مَا قَدَّمَتۡ يَدَاهُ وَيَقُولُ ٱلۡكَافِرُ يَٰلَيۡتَنِي كُنتُ تُرَٰبَۢا

እኛ ሰው ሁሉ እጆቹ ያስቀደሙትን በሚያይበትና ከሓዲውም ዋ ምኞቴ! ምንነው ዐፈር በኾንኩ በሚልበት ቀን ቅርብ የኾነን ቅጣት አስጠነቀቅናችሁ፡፡

እኛ ሰው ሁሉ እጆቹ ያስቀደሙትን በሚያይበትና ከሓዲውም ዋ ምኞቴ! ምንነው ዐፈር በኾንኩ በሚልበት ቀን ቅርብ የኾነን ቅጣት አስጠነቀቅናችሁ፡፡
Footer Include