Header Include

阿姆哈拉语翻译。

古兰经阿姆哈拉文译解,穆罕默德·萨迪克和穆罕默德·塔尼·哈比卜翻译。由拉瓦德翻译中心负责校正,附上翻译原文以便发表意见、评价和持续改进。

QR Code https://quran.islamcontent.com/zh/amharic_sadiq

ٱلۡحَآقَّةُ

እውነትን አረጋጋጪቱ (ትንሣኤ)፡፡

እውነትን አረጋጋጪቱ (ትንሣኤ)፡፡

مَا ٱلۡحَآقَّةُ

አረጋጋጪቱም (እርሷ) ምንድን ናት!

አረጋጋጪቱም (እርሷ) ምንድን ናት!

وَمَآ أَدۡرَىٰكَ مَا ٱلۡحَآقَّةُ

አረጋጋጪቱም ምን እንደኾነች ምን አሳወቀህ?

አረጋጋጪቱም ምን እንደኾነች ምን አሳወቀህ?

كَذَّبَتۡ ثَمُودُ وَعَادُۢ بِٱلۡقَارِعَةِ

ሰሙድና ዓድ በቆርቋሪይቱ (ትንሣኤ) አስተባበሉ፡፡

ሰሙድና ዓድ በቆርቋሪይቱ (ትንሣኤ) አስተባበሉ፡፡

فَأَمَّا ثَمُودُ فَأُهۡلِكُواْ بِٱلطَّاغِيَةِ

ሠሙድማ ወሰን በሌላት ጩኸት ተጠፋ፤ (ተወደሙ)፡፡

ሠሙድማ ወሰን በሌላት ጩኸት ተጠፋ፤ (ተወደሙ)፡፡

وَأَمَّا عَادٞ فَأُهۡلِكُواْ بِرِيحٖ صَرۡصَرٍ عَاتِيَةٖ

ዓድማ በኀይል በምትንሻሻ ብርቱ ነፋስ ተጠፉ፡፡

ዓድማ በኀይል በምትንሻሻ ብርቱ ነፋስ ተጠፉ፡፡

سَخَّرَهَا عَلَيۡهِمۡ سَبۡعَ لَيَالٖ وَثَمَٰنِيَةَ أَيَّامٍ حُسُومٗاۖ فَتَرَى ٱلۡقَوۡمَ فِيهَا صَرۡعَىٰ كَأَنَّهُمۡ أَعۡجَازُ نَخۡلٍ خَاوِيَةٖ

ተከታታይ በኾኑ ሰባት ሌሊቶችና ስምንት መዓልቶች ውስጥ በእነርሱ ላይ ለቀቃት፡፡ ሕዝቦቹንም፤ በውስጧ የተጣሉ ኾነው ልክ ክፍት የኾኑ የዘንባባ ግንዶች መስለው ታያቸዋለህ፡፡

ተከታታይ በኾኑ ሰባት ሌሊቶችና ስምንት መዓልቶች ውስጥ በእነርሱ ላይ ለቀቃት፡፡ ሕዝቦቹንም፤ በውስጧ የተጣሉ ኾነው ልክ ክፍት የኾኑ የዘንባባ ግንዶች መስለው ታያቸዋለህ፡፡

فَهَلۡ تَرَىٰ لَهُم مِّنۢ بَاقِيَةٖ

ለእነርሱም ቀሪን ታያለህን?

ለእነርሱም ቀሪን ታያለህን?

وَجَآءَ فِرۡعَوۡنُ وَمَن قَبۡلَهُۥ وَٱلۡمُؤۡتَفِكَٰتُ بِٱلۡخَاطِئَةِ

ፈርዖን ከበፊቱ የነበሩትም ሰዎች ተገልባጮቹም (ከተሞች) በኀጢአት (ሥራዎች) መጡ፡፡

ፈርዖን ከበፊቱ የነበሩትም ሰዎች ተገልባጮቹም (ከተሞች) በኀጢአት (ሥራዎች) መጡ፡፡

فَعَصَوۡاْ رَسُولَ رَبِّهِمۡ فَأَخَذَهُمۡ أَخۡذَةٗ رَّابِيَةً

የጌታቸውንም መልእክተኛ ትዕዛዝ ጣሱ፡፡ የበረታችንም አያያዝ ያዛቸው፡፡

የጌታቸውንም መልእክተኛ ትዕዛዝ ጣሱ፡፡ የበረታችንም አያያዝ ያዛቸው፡፡

إِنَّا لَمَّا طَغَا ٱلۡمَآءُ حَمَلۡنَٰكُمۡ فِي ٱلۡجَارِيَةِ

እኛ ውሃው ባየለ ጊዜ በተንሻላይቱ ታንኳ ውስጥ ጫንናችሁ፡፡

እኛ ውሃው ባየለ ጊዜ በተንሻላይቱ ታንኳ ውስጥ ጫንናችሁ፡፡

لِنَجۡعَلَهَا لَكُمۡ تَذۡكِرَةٗ وَتَعِيَهَآ أُذُنٞ وَٰعِيَةٞ

ለእናንተ መገሰጫ ልናደርጋት አጥኒ የኾነችም ጆሮ ታጠናት ዘንድ፡፡

ለእናንተ መገሰጫ ልናደርጋት አጥኒ የኾነችም ጆሮ ታጠናት ዘንድ፡፡

فَإِذَا نُفِخَ فِي ٱلصُّورِ نَفۡخَةٞ وَٰحِدَةٞ

በቀንዱም አንዲት መንነፋት በተነፋች ጊዜ፡፡

በቀንዱም አንዲት መንነፋት በተነፋች ጊዜ፡፡

وَحُمِلَتِ ٱلۡأَرۡضُ وَٱلۡجِبَالُ فَدُكَّتَا دَكَّةٗ وَٰحِدَةٗ

ምድርና ጋራዎችም (ከስፍራቸው) በተነሱና አንዲትን መሰባበር በተሰባበሩ ጊዜ፡፡

ምድርና ጋራዎችም (ከስፍራቸው) በተነሱና አንዲትን መሰባበር በተሰባበሩ ጊዜ፡፡

فَيَوۡمَئِذٖ وَقَعَتِ ٱلۡوَاقِعَةُ

በዚያ ቀን ኋኝቱ (ትንሣኤ) ትኾናለች፡፡

በዚያ ቀን ኋኝቱ (ትንሣኤ) ትኾናለች፡፡

وَٱنشَقَّتِ ٱلسَّمَآءُ فَهِيَ يَوۡمَئِذٖ وَاهِيَةٞ

ሰማይም ትቀደዳለች፡፡ ስለዚህ እርሷ በዚያ ቀን ደካማ ናት፡፡

ሰማይም ትቀደዳለች፡፡ ስለዚህ እርሷ በዚያ ቀን ደካማ ናት፡፡

وَٱلۡمَلَكُ عَلَىٰٓ أَرۡجَآئِهَاۚ وَيَحۡمِلُ عَرۡشَ رَبِّكَ فَوۡقَهُمۡ يَوۡمَئِذٖ ثَمَٰنِيَةٞ

መላእክትም በየጫፎችዋ ላይ ይኾናሉ፡፡ የጌታህንም ዐርሽ በዚያ ቀን ስምንት መላእክት ከበላያቸው ይሸከማሉ፡፡

መላእክትም በየጫፎችዋ ላይ ይኾናሉ፡፡ የጌታህንም ዐርሽ በዚያ ቀን ስምንት መላእክት ከበላያቸው ይሸከማሉ፡፡

يَوۡمَئِذٖ تُعۡرَضُونَ لَا تَخۡفَىٰ مِنكُمۡ خَافِيَةٞ

በዚያ ቀን ከእናንተ ተደባቂ (ነገሮች) የማይደበቁ ሲኾኑ ትቅቀረባላችሁ፡፡

በዚያ ቀን ከእናንተ ተደባቂ (ነገሮች) የማይደበቁ ሲኾኑ ትቅቀረባላችሁ፡፡

فَأَمَّا مَنۡ أُوتِيَ كِتَٰبَهُۥ بِيَمِينِهِۦ فَيَقُولُ هَآؤُمُ ٱقۡرَءُواْ كِتَٰبِيَهۡ

መጽሐፉን በቀኙ የተሰጠ ሰውማ (ለጓደኞቹ) «እንኩ፤ መጽሐፌን አንብቡ» ይላል፡፡

መጽሐፉን በቀኙ የተሰጠ ሰውማ (ለጓደኞቹ) «እንኩ፤ መጽሐፌን አንብቡ» ይላል፡፡

إِنِّي ظَنَنتُ أَنِّي مُلَٰقٍ حِسَابِيَهۡ

«እኔ ምርመራየን የምገናኝ መኾኔን አረጋገጥኩ፤» (ተዘጋጀሁም ይላል)፡፡

«እኔ ምርመራየን የምገናኝ መኾኔን አረጋገጥኩ፤» (ተዘጋጀሁም ይላል)፡፡

فَهُوَ فِي عِيشَةٖ رَّاضِيَةٖ

እርሱም በተወደደች ኑሮ ውሰጥ ይኾናል፡፡

እርሱም በተወደደች ኑሮ ውሰጥ ይኾናል፡፡

فِي جَنَّةٍ عَالِيَةٖ

በከፍተኛይቱ ገነት ውስጥ፡፡

በከፍተኛይቱ ገነት ውስጥ፡፡

قُطُوفُهَا دَانِيَةٞ

ፍሬዎችዋ ቅርቦች የኾኑ፡፡

ፍሬዎችዋ ቅርቦች የኾኑ፡፡

كُلُواْ وَٱشۡرَبُواْ هَنِيٓـَٔۢا بِمَآ أَسۡلَفۡتُمۡ فِي ٱلۡأَيَّامِ ٱلۡخَالِيَةِ

በአለፉት ቀናት ውስጥ (በምድረ ዓለም) ባስቀደማችሁት ምክንያት ብሉ፤ ጠጡም፤ (ይባላሉ)፡፡

በአለፉት ቀናት ውስጥ (በምድረ ዓለም) ባስቀደማችሁት ምክንያት ብሉ፤ ጠጡም፤ (ይባላሉ)፡፡

وَأَمَّا مَنۡ أُوتِيَ كِتَٰبَهُۥ بِشِمَالِهِۦ فَيَقُولُ يَٰلَيۡتَنِي لَمۡ أُوتَ كِتَٰبِيَهۡ

መጽሐፉንም በግራው የተሰጠማ «ዋ ጥፋቴ! ምነው መጽሐፌን ባልተሰጠሁ» ይላል፡፡

መጽሐፉንም በግራው የተሰጠማ «ዋ ጥፋቴ! ምነው መጽሐፌን ባልተሰጠሁ» ይላል፡፡

وَلَمۡ أَدۡرِ مَا حِسَابِيَهۡ

«ምርመራየንም ምን እንደኾነ ባላወቅኩ፡፡

«ምርመራየንም ምን እንደኾነ ባላወቅኩ፡፡

يَٰلَيۡتَهَا كَانَتِ ٱلۡقَاضِيَةَ

«እርሷ (ሞት ሕይወቴን) ምነው ፈጻሚ በኾነች፡፡

«እርሷ (ሞት ሕይወቴን) ምነው ፈጻሚ በኾነች፡፡

مَآ أَغۡنَىٰ عَنِّي مَالِيَهۡۜ

«ገንዘቤ ከእኔ ምንንም አላብቃቃኝ፤ (አልጠቀመኝም)፡፡

«ገንዘቤ ከእኔ ምንንም አላብቃቃኝ፤ (አልጠቀመኝም)፡፡

هَلَكَ عَنِّي سُلۡطَٰنِيَهۡ

«ኀይሌ ከእኔ ላይ ጠፋ» (ይላል)፡፡

«ኀይሌ ከእኔ ላይ ጠፋ» (ይላል)፡፡

خُذُوهُ فَغُلُّوهُ

«ያዙት፤ እሰሩትም፡፡

«ያዙት፤ እሰሩትም፡፡

ثُمَّ ٱلۡجَحِيمَ صَلُّوهُ

«ከዚያም በእሳት ውሰጥ አግቡት፡፡

«ከዚያም በእሳት ውሰጥ አግቡት፡፡

ثُمَّ فِي سِلۡسِلَةٖ ذَرۡعُهَا سَبۡعُونَ ذِرَاعٗا فَٱسۡلُكُوهُ

«ከዚያም ርዝመቷ ሰባ ክንድ በኾነች ሰንሰለት ውስጥ አግቡት፡፡»

«ከዚያም ርዝመቷ ሰባ ክንድ በኾነች ሰንሰለት ውስጥ አግቡት፡፡»

إِنَّهُۥ كَانَ لَا يُؤۡمِنُ بِٱللَّهِ ٱلۡعَظِيمِ

እርሱ ታላቅ በኾነው አላህ አያምንም ነበርና፡፡

እርሱ ታላቅ በኾነው አላህ አያምንም ነበርና፡፡

وَلَا يَحُضُّ عَلَىٰ طَعَامِ ٱلۡمِسۡكِينِ

ድኾችንም በማብላት ላይ አያግባባም ነበርና፡፡

ድኾችንም በማብላት ላይ አያግባባም ነበርና፡፡

فَلَيۡسَ لَهُ ٱلۡيَوۡمَ هَٰهُنَا حَمِيمٞ

ለእርሱም ዛሬ እዚህ ዘመድ የለውም፡፡

ለእርሱም ዛሬ እዚህ ዘመድ የለውም፡፡

وَلَا طَعَامٌ إِلَّا مِنۡ غِسۡلِينٖ

ምግብም ከእሳት ሰዎች ቁስል እጣቢ (እዥ) በስተቀር የለውም፡፡

ምግብም ከእሳት ሰዎች ቁስል እጣቢ (እዥ) በስተቀር የለውም፡፡

لَّا يَأۡكُلُهُۥٓ إِلَّا ٱلۡخَٰطِـُٔونَ

ኀጢኣተኞች እንጅ ሌላ አይበላውም፤ (ይባላል)፡፡

ኀጢኣተኞች እንጅ ሌላ አይበላውም፤ (ይባላል)፡፡

فَلَآ أُقۡسِمُ بِمَا تُبۡصِرُونَ

በምታዩትም ነገር እምላለሁ፡፡

በምታዩትም ነገር እምላለሁ፡፡

وَمَا لَا تُبۡصِرُونَ

በማታዩትም ነገር፡፡

በማታዩትም ነገር፡፡

إِنَّهُۥ لَقَوۡلُ رَسُولٖ كَرِيمٖ

እርሱ (ቁርኣን) የተከበረ መልክተኛ ቃል ነው፡፡

እርሱ (ቁርኣን) የተከበረ መልክተኛ ቃል ነው፡፡

وَمَا هُوَ بِقَوۡلِ شَاعِرٖۚ قَلِيلٗا مَّا تُؤۡمِنُونَ

እርሱም የባለቅኔ ቃል (ግጥም) አይደለም፡፡ ጥቂትን ብቻ ታምናላችሁ፡፡

እርሱም የባለቅኔ ቃል (ግጥም) አይደለም፡፡ ጥቂትን ብቻ ታምናላችሁ፡፡

وَلَا بِقَوۡلِ كَاهِنٖۚ قَلِيلٗا مَّا تَذَكَّرُونَ

የጠንቋይም ቃል አይደለም፡፡ ጥቂትን ብቻ ታስታውሳላችሁ፡፡

የጠንቋይም ቃል አይደለም፡፡ ጥቂትን ብቻ ታስታውሳላችሁ፡፡

تَنزِيلٞ مِّن رَّبِّ ٱلۡعَٰلَمِينَ

ከዓለማት ጌታ የተወረደ ነው፡፡

ከዓለማት ጌታ የተወረደ ነው፡፡

وَلَوۡ تَقَوَّلَ عَلَيۡنَا بَعۡضَ ٱلۡأَقَاوِيلِ

በእኛ ላይም ከፊልን ቃላት (ያላልነውን) በቀጠፈ ኖሮ፤

በእኛ ላይም ከፊልን ቃላት (ያላልነውን) በቀጠፈ ኖሮ፤

لَأَخَذۡنَا مِنۡهُ بِٱلۡيَمِينِ

በቀኝ በያዝነው ነበር፡፡

በቀኝ በያዝነው ነበር፡፡

ثُمَّ لَقَطَعۡنَا مِنۡهُ ٱلۡوَتِينَ

ከዚያም ከእርሱ የልቡን ሥር (የተንጠለጠለበትን ጅማት) በቆረጥን ነበር፡፡

ከዚያም ከእርሱ የልቡን ሥር (የተንጠለጠለበትን ጅማት) በቆረጥን ነበር፡፡

فَمَا مِنكُم مِّنۡ أَحَدٍ عَنۡهُ حَٰجِزِينَ

ከእናንተም ውስጥ ከእርሱ ላይ ከልካዮች ምንም አይኖሩም፡፡

ከእናንተም ውስጥ ከእርሱ ላይ ከልካዮች ምንም አይኖሩም፡፡

وَإِنَّهُۥ لَتَذۡكِرَةٞ لِّلۡمُتَّقِينَ

እርሱም (ቁርኣን) ለጥንቁቆቹ መገሠጫ ነው፡፡

እርሱም (ቁርኣን) ለጥንቁቆቹ መገሠጫ ነው፡፡

وَإِنَّا لَنَعۡلَمُ أَنَّ مِنكُم مُّكَذِّبِينَ

እኛም ከእናንተ ውስጥ አስተባባዮች መኖራቸውን በእርግጥ እናውቃለን፡፡

እኛም ከእናንተ ውስጥ አስተባባዮች መኖራቸውን በእርግጥ እናውቃለን፡፡

وَإِنَّهُۥ لَحَسۡرَةٌ عَلَى ٱلۡكَٰفِرِينَ

እርሱም (ቁርኣን) በከሓዲዎቹ ላይ ጸጸት ነው፡፡

እርሱም (ቁርኣን) በከሓዲዎቹ ላይ ጸጸት ነው፡፡

وَإِنَّهُۥ لَحَقُّ ٱلۡيَقِينِ

እርሱም የተረጋገጠ እውነት ነው፡፡

እርሱም የተረጋገጠ እውነት ነው፡፡

فَسَبِّحۡ بِٱسۡمِ رَبِّكَ ٱلۡعَظِيمِ

የታላቁን ጌታህንም ስም አወድስ፡፡

የታላቁን ጌታህንም ስም አወድስ፡፡
Footer Include