阿姆哈拉语翻译。
古兰经阿姆哈拉文译解,穆罕默德·萨迪克和穆罕默德·塔尼·哈比卜翻译。由拉瓦德翻译中心负责校正,附上翻译原文以便发表意见、评价和持续改进。
عَبَسَ وَتَوَلَّىٰٓ
ፊቱን አጨፈገገ፤ ዞረም፡፡
أَن جَآءَهُ ٱلۡأَعۡمَىٰ
ዕውሩ ስለ መጣው፡፡
وَمَا يُدۡرِيكَ لَعَلَّهُۥ يَزَّكَّىٰٓ
ምን ያሳውቅሃል? (ከኀጢአቶቹ) ሊጥራራ ይከጀላል፡፡
أَوۡ يَذَّكَّرُ فَتَنفَعَهُ ٱلذِّكۡرَىٰٓ
ወይም ሊገሠጽ ግሠጼይቱም ልትጠቅመው (ይከጀላል)፡፡
أَمَّا مَنِ ٱسۡتَغۡنَىٰ
የተብቃቃው ሰውማ፤
فَأَنتَ لَهُۥ تَصَدَّىٰ
አንተ ለእርሱ (ለእምነቱ በመጓጓት) በፈገግታ ትቀበለዋለህ፡፡
وَمَا عَلَيۡكَ أَلَّا يَزَّكَّىٰ
ባይጥራራ (ባያምን) ባንተ ላይ ምንም የሌለብህ ስትኾን፡፡
وَأَمَّا مَن جَآءَكَ يَسۡعَىٰ
እየገሰገሰ የመጣህ ሰውማ፤
وَهُوَ يَخۡشَىٰ
እርሱ (አላህን) የሚፈራ ሲኾን፤
فَأَنتَ عَنۡهُ تَلَهَّىٰ
አንተ ከእርሱ ትዝዘናጋለህ፡፡
كَلَّآ إِنَّهَا تَذۡكِرَةٞ
ተከልከል፡፡ እርሷ ማስገንዘቢያ ናት፡፡
فَمَن شَآءَ ذَكَرَهُۥ
የሻም ሰው (ቁርኣኑን) ያስታውሰዋል፡፡
فِي صُحُفٖ مُّكَرَّمَةٖ
በተከበሩ ጽሑፎች ውስጥ ነው፡፡
مَّرۡفُوعَةٖ مُّطَهَّرَةِۭ
ከፍ በተደረገች ንጹሕ በተደረገች (ጽሑፍ ውስጥ ነው)፡፡
بِأَيۡدِي سَفَرَةٖ
በጸሐፊዎቹ (መላእክት) እጆች (ንጹሕ የተደረገች)፡፡
كِرَامِۭ بَرَرَةٖ
የተከበሩና ታዛዦች በኾኑት (ጸሐፊዎች እጆች)፡፡
قُتِلَ ٱلۡإِنسَٰنُ مَآ أَكۡفَرَهُۥ
ሰው ተረገመ፤ ምን ከሓዲ አደረገው?
مِنۡ أَيِّ شَيۡءٍ خَلَقَهُۥ
(ጌታው) በምን ነገር ፈጠረው? (አያስብምን?)
مِن نُّطۡفَةٍ خَلَقَهُۥ فَقَدَّرَهُۥ
ከፍትወት ጠብታ ፈጠረው፤ መጠነውም፡፡
ثُمَّ ٱلسَّبِيلَ يَسَّرَهُۥ
ከዚያም (መውጫ) መንገዱን አገራው፡፡
ثُمَّ أَمَاتَهُۥ فَأَقۡبَرَهُۥ
ከዚያም ገደለው፤ እንዲቀበርም አደረገው፡፡
ثُمَّ إِذَا شَآءَ أَنشَرَهُۥ
ከዚያም (ማንሳቱን) በሻ ጊዜ ያስነሳዋል፡፡
كَلَّا لَمَّا يَقۡضِ مَآ أَمَرَهُۥ
በእውነት ያንን (ጌታው) ያዘዘውን ገና አልፈጸመም፡፡
فَلۡيَنظُرِ ٱلۡإِنسَٰنُ إِلَىٰ طَعَامِهِۦٓ
ሰውም ወደ ምግቡ ይመልከት፡፡
أَنَّا صَبَبۡنَا ٱلۡمَآءَ صَبّٗا
እኛ ውሃን ማንቧቧትን ያንቧቧን መኾናችንን፡፡
ثُمَّ شَقَقۡنَا ٱلۡأَرۡضَ شَقّٗا
ከዚያም ምድርን (በደካማ ቡቃያ) መሰንጠቅን የሰነጠቅን፤
فَأَنۢبَتۡنَا فِيهَا حَبّٗا
በውስጧም እኽልን ያበቀልን፤
وَعِنَبٗا وَقَضۡبٗا
ወይንንም፤ እርጥብ (ያበቀልን)፤
وَزَيۡتُونٗا وَنَخۡلٗا
የዘይት ወይራንም ዘንባባንም፤
وَحَدَآئِقَ غُلۡبٗا
ጭፍቆች አትክልቶችንም፤
وَفَٰكِهَةٗ وَأَبّٗا
ፍራፍሬንም ገለባንም፤ (ያበቀልን መኾናችንን ይመልከት)፡፡
مَّتَٰعٗا لَّكُمۡ وَلِأَنۡعَٰمِكُمۡ
ለእናንተም ለእንስሶቻችሁም መጠቀሚያ ይኾን ዘንድ (ይህን ሠራን)፡፡
فَإِذَا جَآءَتِ ٱلصَّآخَّةُ
አደንቋሪይቱም (መከራ) በመጣች ጊዜ፤
يَوۡمَ يَفِرُّ ٱلۡمَرۡءُ مِنۡ أَخِيهِ
ሰው ከወንድሙ በሚሸሽበት ቀን፤
وَأُمِّهِۦ وَأَبِيهِ
ከናቱም ካባቱም፤
وَصَٰحِبَتِهِۦ وَبَنِيهِ
ከሚስቱም ከልጁም፤
لِكُلِّ ٱمۡرِيٕٖ مِّنۡهُمۡ يَوۡمَئِذٖ شَأۡنٞ يُغۡنِيهِ
ከእነርሱ ለየሰው ሁሉ በዚያ ቀን (ከሌላው) የሚያብቃቃው ኹነታ አልለው፡፡
وُجُوهٞ يَوۡمَئِذٖ مُّسۡفِرَةٞ
ፊቶች በዚያ ቀን አብሪዎች ናቸው፤
ضَاحِكَةٞ مُّسۡتَبۡشِرَةٞ
ሳቂዎችም ተደሳቾችም ናቸው፡፡
وَوُجُوهٞ يَوۡمَئِذٍ عَلَيۡهَا غَبَرَةٞ
ፊቶችም በዚያ ቀን በላያቸው ላይ ትቢያ አልለባቸው፤
تَرۡهَقُهَا قَتَرَةٌ
ጥቁረት ትሸፍናቸዋለች፤
أُوْلَٰٓئِكَ هُمُ ٱلۡكَفَرَةُ ٱلۡفَجَرَةُ
እነዚያ እነሱ ከሓዲዎቹ አመጸኞቹ ናቸው፡፡
مشاركة عبر