Header Include

阿姆哈拉语翻译。

古兰经阿姆哈拉文译解,穆罕默德·萨迪克和穆罕默德·塔尼·哈比卜翻译。由拉瓦德翻译中心负责校正,附上翻译原文以便发表意见、评价和持续改进。

QR Code https://quran.islamcontent.com/zh/amharic_sadiq

يَٰٓأَيُّهَا ٱلۡمُدَّثِّرُ

አንተ (ልብስህን) ደራቢው ሆይ!

አንተ (ልብስህን) ደራቢው ሆይ!

قُمۡ فَأَنذِرۡ

ተነሳ አስጠንቅቅም፡፡

ተነሳ አስጠንቅቅም፡፡

وَرَبَّكَ فَكَبِّرۡ

ጌታህንም አክብር፡፡

ጌታህንም አክብር፡፡

وَثِيَابَكَ فَطَهِّرۡ

ልብስህንም አጥራ፡፡

ልብስህንም አጥራ፡፡

وَٱلرُّجۡزَ فَٱهۡجُرۡ

ጣዖትንም ራቅ፡፡

ጣዖትንም ራቅ፡፡

وَلَا تَمۡنُن تَسۡتَكۡثِرُ

ማብዛትንም የምትፈልግ ኾነህ፤ (በረከትን) አትለግስ።

ማብዛትንም የምትፈልግ ኾነህ፤ (በረከትን) አትለግስ።

وَلِرَبِّكَ فَٱصۡبِرۡ

ለጌታህም (ትዕዛዝ) ታገሥ፡፡

ለጌታህም (ትዕዛዝ) ታገሥ፡፡

فَإِذَا نُقِرَ فِي ٱلنَّاقُورِ

በቀንዱም በተነፋ ጊዜ (ነገሩ ይበረታል)፡፡

በቀንዱም በተነፋ ጊዜ (ነገሩ ይበረታል)፡፡

فَذَٰلِكَ يَوۡمَئِذٖ يَوۡمٌ عَسِيرٌ

ይህም (ጊዜ) ያ ቀን አስቸጋሪ ቀን ነው፡፡

ይህም (ጊዜ) ያ ቀን አስቸጋሪ ቀን ነው፡፡

عَلَى ٱلۡكَٰفِرِينَ غَيۡرُ يَسِيرٖ

በከሓዲዎች ላይ ገር ያልኾነ ነው፡፡

በከሓዲዎች ላይ ገር ያልኾነ ነው፡፡

ذَرۡنِي وَمَنۡ خَلَقۡتُ وَحِيدٗا

አንድ ኾኖ ከፈጠርኩት ሰው ጋር ተዎኝ (እኔ እበቃሃለሁ)፡፡

አንድ ኾኖ ከፈጠርኩት ሰው ጋር ተዎኝ (እኔ እበቃሃለሁ)፡፡

وَجَعَلۡتُ لَهُۥ مَالٗا مَّمۡدُودٗا

ለእርሱም የተዘረጋን ገንዘብ (በያይነቱ) ያደረግሁለት፡፡

ለእርሱም የተዘረጋን ገንዘብ (በያይነቱ) ያደረግሁለት፡፡

وَبَنِينَ شُهُودٗا

(በያደባባዩ) ተገኝዎች የኾኑ ወንዶች ልጆችንም፡፡

(በያደባባዩ) ተገኝዎች የኾኑ ወንዶች ልጆችንም፡፡

وَمَهَّدتُّ لَهُۥ تَمۡهِيدٗا

ለእርሱም (ኑሮውን) መዘርጋትን የዘረጋሁለት (ከኾነ ሰው ገር ተዎኝ)፡፡

ለእርሱም (ኑሮውን) መዘርጋትን የዘረጋሁለት (ከኾነ ሰው ገር ተዎኝ)፡፡

ثُمَّ يَطۡمَعُ أَنۡ أَزِيدَ

ከዚያም ልጨምርለት ይከጅላል፡፡

ከዚያም ልጨምርለት ይከጅላል፡፡

كَلَّآۖ إِنَّهُۥ كَانَ لِأٓيَٰتِنَا عَنِيدٗا

ይከልከል፤ እርሱ ለአንቀጾቻችን በእርግጥ ተቃዋሚ ነበር፡፡

ይከልከል፤ እርሱ ለአንቀጾቻችን በእርግጥ ተቃዋሚ ነበር፡፡

سَأُرۡهِقُهُۥ صَعُودًا

በእርግጥ ችግርን አስገድደዋለሁ፡፡

በእርግጥ ችግርን አስገድደዋለሁ፡፡

إِنَّهُۥ فَكَّرَ وَقَدَّرَ

እርሱ (በቁርኣን ነገር) ሐሰበ፤ ገመተም፡፡

እርሱ (በቁርኣን ነገር) ሐሰበ፤ ገመተም፡፡

فَقُتِلَ كَيۡفَ قَدَّرَ

ተረገመም፤ እንዴት ገመተ!

ተረገመም፤ እንዴት ገመተ!

ثُمَّ قُتِلَ كَيۡفَ قَدَّرَ

ከዚያም (ከሞት በኋላ) ተረገመ፡፡ እንዴት ገመተ!

ከዚያም (ከሞት በኋላ) ተረገመ፡፡ እንዴት ገመተ!

ثُمَّ نَظَرَ

ከዚያም እንደ ገና (በቁርኣኑ ነገር) ተመለከተ፡፡

ከዚያም እንደ ገና (በቁርኣኑ ነገር) ተመለከተ፡፡

ثُمَّ عَبَسَ وَبَسَرَ

ከዚያም ፊቱን አጨፈገገ፤ አኮማተረም፡፡

ከዚያም ፊቱን አጨፈገገ፤ አኮማተረም፡፡

ثُمَّ أَدۡبَرَ وَٱسۡتَكۡبَرَ

ከዚያም (ከማመን) ዞረ፤ ኮራም፡፡

ከዚያም (ከማመን) ዞረ፤ ኮራም፡፡

فَقَالَ إِنۡ هَٰذَآ إِلَّا سِحۡرٞ يُؤۡثَرُ

አለም «ይህ (ከሌላ) የሚቀዳ ድግምት እንጅ ሌላ አይደለም፡፡

አለም «ይህ (ከሌላ) የሚቀዳ ድግምት እንጅ ሌላ አይደለም፡፡

إِنۡ هَٰذَآ إِلَّا قَوۡلُ ٱلۡبَشَرِ

«ይህ የሰው ቃል እንጅ ሌላ አይደለም፡፡»

«ይህ የሰው ቃል እንጅ ሌላ አይደለም፡፡»

سَأُصۡلِيهِ سَقَرَ

በሰቀር ውስጥ በእርግጥ አገባዋለሁ፡፡

በሰቀር ውስጥ በእርግጥ አገባዋለሁ፡፡

وَمَآ أَدۡرَىٰكَ مَا سَقَرُ

ሰቀር ምን እንደኾነች ምን አሳወቀህ?

ሰቀር ምን እንደኾነች ምን አሳወቀህ?

لَا تُبۡقِي وَلَا تَذَرُ

(ያገኘችውን ሁሉ) አታስቀርም አትተውምም፡፡

(ያገኘችውን ሁሉ) አታስቀርም አትተውምም፡፡

لَوَّاحَةٞ لِّلۡبَشَرِ

ቆዳን በጣም አክሳይ ናት፡፡

ቆዳን በጣም አክሳይ ናት፡፡

عَلَيۡهَا تِسۡعَةَ عَشَرَ

በእርሷም ላይ አሥራ ዘጠኝ (ዘበኞች) አሉባት፡፡

በእርሷም ላይ አሥራ ዘጠኝ (ዘበኞች) አሉባት፡፡

وَمَا جَعَلۡنَآ أَصۡحَٰبَ ٱلنَّارِ إِلَّا مَلَٰٓئِكَةٗۖ وَمَا جَعَلۡنَا عِدَّتَهُمۡ إِلَّا فِتۡنَةٗ لِّلَّذِينَ كَفَرُواْ لِيَسۡتَيۡقِنَ ٱلَّذِينَ أُوتُواْ ٱلۡكِتَٰبَ وَيَزۡدَادَ ٱلَّذِينَ ءَامَنُوٓاْ إِيمَٰنٗا وَلَا يَرۡتَابَ ٱلَّذِينَ أُوتُواْ ٱلۡكِتَٰبَ وَٱلۡمُؤۡمِنُونَ وَلِيَقُولَ ٱلَّذِينَ فِي قُلُوبِهِم مَّرَضٞ وَٱلۡكَٰفِرُونَ مَاذَآ أَرَادَ ٱللَّهُ بِهَٰذَا مَثَلٗاۚ كَذَٰلِكَ يُضِلُّ ٱللَّهُ مَن يَشَآءُ وَيَهۡدِي مَن يَشَآءُۚ وَمَا يَعۡلَمُ جُنُودَ رَبِّكَ إِلَّا هُوَۚ وَمَا هِيَ إِلَّا ذِكۡرَىٰ لِلۡبَشَرِ

የእሳትንም ዘበኞች መላእክት እንጅ ሌላ አላደረግንም፡፡ ቁጥራቸውንም ለእነዚያ ለካዱት መፈተኛ እንጅ አላደረግንም፡፡ እነዚያ መጽሐፍን የተሰጡት እንዲያረጋግጡ፣ እነዚያም ያመኑት እምነትን እንዲጨምሩ፣ እነዚያም መጽሐፍን የተሰጡትና ምእምናኖቹ እንዳይጠራጠሩ፣ እነዚያም በልቦቻቸው ውስጥ በሽታ ያለባቸው (መናፍቃን)፣ ከሓዲዎችም አላህ በዚህ (ቁጥር) ምን ምሳሌ ሽቷል? እንዲሉ (እንጅ አላደረግንም)፡፡ እንደዚሁ አላህ የሚሻውን ያጠምማል፡፡ የሚሻውንም ያቀናል፡፡ የጌታህንም ሰራዊት (ልክ) ከርሱ በቀር ማንም አያውቅም፡፡ እርሷም (የሰቀር እሳት) ለሰዎች መገሰጫ እንጅ ሌላ አይደለችም፡፡

የእሳትንም ዘበኞች መላእክት እንጅ ሌላ አላደረግንም፡፡ ቁጥራቸውንም ለእነዚያ ለካዱት መፈተኛ እንጅ አላደረግንም፡፡ እነዚያ መጽሐፍን የተሰጡት እንዲያረጋግጡ፣ እነዚያም ያመኑት እምነትን እንዲጨምሩ፣ እነዚያም መጽሐፍን የተሰጡትና ምእምናኖቹ እንዳይጠራጠሩ፣ እነዚያም በልቦቻቸው ውስጥ በሽታ ያለባቸው (መናፍቃን)፣ ከሓዲዎችም አላህ በዚህ (ቁጥር) ምን ምሳሌ ሽቷል? እንዲሉ (እንጅ አላደረግንም)፡፡ እንደዚሁ አላህ የሚሻውን ያጠምማል፡፡ የሚሻውንም ያቀናል፡፡ የጌታህንም ሰራዊት (ልክ) ከርሱ በቀር ማንም አያውቅም፡፡ እርሷም (የሰቀር እሳት) ለሰዎች መገሰጫ እንጅ ሌላ አይደለችም፡፡

كَلَّا وَٱلۡقَمَرِ

(ከክህደት) ይከልከሉ፡፡ በጨረቃ እምላለሁ፡፡

(ከክህደት) ይከልከሉ፡፡ በጨረቃ እምላለሁ፡፡

وَٱلَّيۡلِ إِذۡ أَدۡبَرَ

በሌሊቱም በኼደ ጊዜ፡፡

በሌሊቱም በኼደ ጊዜ፡፡

وَٱلصُّبۡحِ إِذَآ أَسۡفَرَ

በንጋቱም ባበራ ጊዜ፡፡

በንጋቱም ባበራ ጊዜ፡፡

إِنَّهَا لَإِحۡدَى ٱلۡكُبَرِ

እርሷ (ሰቀር) ከታላላቆቹ (አደጋዎች) አንዷ ናት፡፡

እርሷ (ሰቀር) ከታላላቆቹ (አደጋዎች) አንዷ ናት፡፡

نَذِيرٗا لِّلۡبَشَرِ

ለሰዎች አስፈራሪ ስትኾን፡፡

ለሰዎች አስፈራሪ ስትኾን፡፡

لِمَن شَآءَ مِنكُمۡ أَن يَتَقَدَّمَ أَوۡ يَتَأَخَّرَ

ከእናንተ (ወደ በጎ ነገር) መቅደምን ወይም ወደ ኋላ መቅረትን ለሻ ሰው (አስፈራሪ ስትኾኑ)፡፡

ከእናንተ (ወደ በጎ ነገር) መቅደምን ወይም ወደ ኋላ መቅረትን ለሻ ሰው (አስፈራሪ ስትኾኑ)፡፡

كُلُّ نَفۡسِۭ بِمَا كَسَبَتۡ رَهِينَةٌ

ነፍስ ሁሉ በሠራችው ሥራ ተያዥ ናት፡፡

ነፍስ ሁሉ በሠራችው ሥራ ተያዥ ናት፡፡

إِلَّآ أَصۡحَٰبَ ٱلۡيَمِينِ

የቀኝ ባለቤቶች ብቻ ሲቀሩ፡፡

የቀኝ ባለቤቶች ብቻ ሲቀሩ፡፡

فِي جَنَّٰتٖ يَتَسَآءَلُونَ

(እነርሱስ) በገነቶች ውስጥ ይጠያየቃሉ፡፡

(እነርሱስ) በገነቶች ውስጥ ይጠያየቃሉ፡፡

عَنِ ٱلۡمُجۡرِمِينَ

ከአመጸኞቹ ኹነታ፡፡

ከአመጸኞቹ ኹነታ፡፡

مَا سَلَكَكُمۡ فِي سَقَرَ

(ይሏቸዋልም) «በሰቀር ውስጥ ምን አገባችሁ?»

(ይሏቸዋልም) «በሰቀር ውስጥ ምን አገባችሁ?»

قَالُواْ لَمۡ نَكُ مِنَ ٱلۡمُصَلِّينَ

(እነርሱም) ይላሉ «ከሰጋጆቹ አልነበርንም፡፡

(እነርሱም) ይላሉ «ከሰጋጆቹ አልነበርንም፡፡

وَلَمۡ نَكُ نُطۡعِمُ ٱلۡمِسۡكِينَ

«ለድኾችም የምናበላ አልነበርንም፡፡

«ለድኾችም የምናበላ አልነበርንም፡፡

وَكُنَّا نَخُوضُ مَعَ ٱلۡخَآئِضِينَ

«ከዘባራቂዎቹም ጋር እንዘባርቅ ነበርን፡፡

«ከዘባራቂዎቹም ጋር እንዘባርቅ ነበርን፡፡

وَكُنَّا نُكَذِّبُ بِيَوۡمِ ٱلدِّينِ

«በፍርዱ ቀንም እናስተባብል ነበርን፡፡

«በፍርዱ ቀንም እናስተባብል ነበርን፡፡

حَتَّىٰٓ أَتَىٰنَا ٱلۡيَقِينُ

«እርግጠኛው (ሞት) እስከ መጣን ድረስ፡፡»

«እርግጠኛው (ሞት) እስከ መጣን ድረስ፡፡»

فَمَا تَنفَعُهُمۡ شَفَٰعَةُ ٱلشَّٰفِعِينَ

የአማላጆችም ምልጃ አትጠቅማቸውም፡፡

የአማላጆችም ምልጃ አትጠቅማቸውም፡፡

فَمَا لَهُمۡ عَنِ ٱلتَّذۡكِرَةِ مُعۡرِضِينَ

ከግሣጼዬም (ከቁርኣን) የሚያፈገፍጉት ለእነርሱ ምን አልላቸው?

ከግሣጼዬም (ከቁርኣን) የሚያፈገፍጉት ለእነርሱ ምን አልላቸው?

كَأَنَّهُمۡ حُمُرٞ مُّسۡتَنفِرَةٞ

እነርሱ ልክ ደንባሪዎች የሜዳ አህዮች ይመስላሉ፡፡

እነርሱ ልክ ደንባሪዎች የሜዳ አህዮች ይመስላሉ፡፡

فَرَّتۡ مِن قَسۡوَرَةِۭ

ከዐንበሳ የሸሹ፡፡

ከዐንበሳ የሸሹ፡፡

بَلۡ يُرِيدُ كُلُّ ٱمۡرِيٕٖ مِّنۡهُمۡ أَن يُؤۡتَىٰ صُحُفٗا مُّنَشَّرَةٗ

ይልቁንም ከእነርሱ እያንዳንዱ ሰው ሁሉ የተዘረጉ ጽሑፎችን እንዲስሰጥ ይፈልጋል፡፡

ይልቁንም ከእነርሱ እያንዳንዱ ሰው ሁሉ የተዘረጉ ጽሑፎችን እንዲስሰጥ ይፈልጋል፡፡

كَلَّاۖ بَل لَّا يَخَافُونَ ٱلۡأٓخِرَةَ

ይከልከሉ፡፡ ይልቁንም የመጨረሻይቱን ዓለም (ቅጣት) አይፈሩም፡፡

ይከልከሉ፡፡ ይልቁንም የመጨረሻይቱን ዓለም (ቅጣት) አይፈሩም፡፡

كَلَّآ إِنَّهُۥ تَذۡكِرَةٞ

ይከልከሉ፡፡ እርሱ (ቁርኣን) መገሠጫ ነው፡፡

ይከልከሉ፡፡ እርሱ (ቁርኣን) መገሠጫ ነው፡፡

فَمَن شَآءَ ذَكَرَهُۥ

ስለዚህ የሻ ሰው ይገሰጽበታል፡፡

ስለዚህ የሻ ሰው ይገሰጽበታል፡፡

وَمَا يَذۡكُرُونَ إِلَّآ أَن يَشَآءَ ٱللَّهُۚ هُوَ أَهۡلُ ٱلتَّقۡوَىٰ وَأَهۡلُ ٱلۡمَغۡفِرَةِ

አላህም ካልሻ በስተቀር አይገሠጹም፡፡ እርሱ (አላህ) የመፈራት ባለቤት የምሕረትም ባለቤት ነው፡፡

አላህም ካልሻ በስተቀር አይገሠጹም፡፡ እርሱ (አላህ) የመፈራት ባለቤት የምሕረትም ባለቤት ነው፡፡
Footer Include