Header Include

ترجمه ى امهاری

ترجمهٔ معانی قرآن کریم به زبان امهری. ترجمهٔ شیخ محمدصادق و محمد الثانی حبیب. مراجعه و تصحیح زیر نظر مرکز ترجمهٔ رواد. ترجمهٔ اصلی به هدف اظهار نظر و ارزش‌گذاری و بهبود مستمر در معرض نظر خوانندگان قرار دارد

QR Code https://quran.islamcontent.com/fa/amharic_sadiq

وَٱلنَّجۡمِ إِذَا هَوَىٰ

በኮከብ እምላለሁ በወደቀ (በገባ) ጊዜ፡፡

በኮከብ እምላለሁ በወደቀ (በገባ) ጊዜ፡፡

مَا ضَلَّ صَاحِبُكُمۡ وَمَا غَوَىٰ

ባልደረባችሁ (ነቢያችን ሙሐመድ) አልተሳሳተም፤ አልጠመመምም፡፡

ባልደረባችሁ (ነቢያችን ሙሐመድ) አልተሳሳተም፤ አልጠመመምም፡፡

وَمَا يَنطِقُ عَنِ ٱلۡهَوَىٰٓ

ከልብ ወለድም አይናገርም፡፡

ከልብ ወለድም አይናገርም፡፡

إِنۡ هُوَ إِلَّا وَحۡيٞ يُوحَىٰ

እርሱ (ንግግሩ) የሚወርረድ ራእይ እንጅ ሌላ አይደለም፡፡

እርሱ (ንግግሩ) የሚወርረድ ራእይ እንጅ ሌላ አይደለም፡፡

عَلَّمَهُۥ شَدِيدُ ٱلۡقُوَىٰ

ኀይሎቹ ብርቱው አስተማረው፡፡

ኀይሎቹ ብርቱው አስተማረው፡፡

ذُو مِرَّةٖ فَٱسۡتَوَىٰ

የዕውቀት ባለቤት የኾነው (አስተማረው፤ በተፈጥሮ ቅርጹ ኾኖ በአየር ላይ) ተደላደለም፡፡

የዕውቀት ባለቤት የኾነው (አስተማረው፤ በተፈጥሮ ቅርጹ ኾኖ በአየር ላይ) ተደላደለም፡፡

وَهُوَ بِٱلۡأُفُقِ ٱلۡأَعۡلَىٰ

እርሱ በላይኛው አድማስ ኾኖ፡፡

እርሱ በላይኛው አድማስ ኾኖ፡፡

ثُمَّ دَنَا فَتَدَلَّىٰ

ከዚያም ቀረበ፤ ወረደም፡፡

ከዚያም ቀረበ፤ ወረደም፡፡

فَكَانَ قَابَ قَوۡسَيۡنِ أَوۡ أَدۡنَىٰ

(ከእርሱ) የሁለት ደጋኖች ጫፍ ያህል ወይም (ከዚህ) ይበልጥ የቀረበ ኾነም፡፡

(ከእርሱ) የሁለት ደጋኖች ጫፍ ያህል ወይም (ከዚህ) ይበልጥ የቀረበ ኾነም፡፡

فَأَوۡحَىٰٓ إِلَىٰ عَبۡدِهِۦ مَآ أَوۡحَىٰ

ወደ ባሪያውም (አላህ) ያወረደውን አወረደ፡፡

ወደ ባሪያውም (አላህ) ያወረደውን አወረደ፡፡

مَا كَذَبَ ٱلۡفُؤَادُ مَا رَأَىٰٓ

(ነቢዩም በዓይኑ) ያየውን ልቡ አልዋሸም፡፡

(ነቢዩም በዓይኑ) ያየውን ልቡ አልዋሸም፡፡

أَفَتُمَٰرُونَهُۥ عَلَىٰ مَا يَرَىٰ

ታዲያ በሚያየው ላይ ትከራከሩታላችሁን?

ታዲያ በሚያየው ላይ ትከራከሩታላችሁን?

وَلَقَدۡ رَءَاهُ نَزۡلَةً أُخۡرَىٰ

በሌላይቱም መውረድ ጊዜ በእርግጥ አይቶታል፡፡

በሌላይቱም መውረድ ጊዜ በእርግጥ አይቶታል፡፡

عِندَ سِدۡرَةِ ٱلۡمُنتَهَىٰ

በመጨረሻይቱ ቁርቁራ አጠገብ፤

በመጨረሻይቱ ቁርቁራ አጠገብ፤

عِندَهَا جَنَّةُ ٱلۡمَأۡوَىٰٓ

እርሷ ዘንድ መኖሪያይቱ ገነት ያለች ስትኾን፡፡

እርሷ ዘንድ መኖሪያይቱ ገነት ያለች ስትኾን፡፡

إِذۡ يَغۡشَى ٱلسِّدۡرَةَ مَا يَغۡشَىٰ

ቁርቁራይቱን የሚሸፍን ነገር በሚሸፍናት ጊዜ (አየው)፡፡

ቁርቁራይቱን የሚሸፍን ነገር በሚሸፍናት ጊዜ (አየው)፡፡

مَا زَاغَ ٱلۡبَصَرُ وَمَا طَغَىٰ

ዓይኑ (ካየው) አልተዘነበለም፡፡ ወሰንም አላለፈም፡፡

ዓይኑ (ካየው) አልተዘነበለም፡፡ ወሰንም አላለፈም፡፡

لَقَدۡ رَأَىٰ مِنۡ ءَايَٰتِ رَبِّهِ ٱلۡكُبۡرَىٰٓ

ከጌታው ታምራቶች ታላላቆቹን በእርግጥ አየ፡፡

ከጌታው ታምራቶች ታላላቆቹን በእርግጥ አየ፡፡

أَفَرَءَيۡتُمُ ٱللَّٰتَ وَٱلۡعُزَّىٰ

አል-ላትንና አል-ዑዛን አያችሁን?

አል-ላትንና አል-ዑዛን አያችሁን?

وَمَنَوٰةَ ٱلثَّالِثَةَ ٱلۡأُخۡرَىٰٓ

ሦስተኛይቱንም አነስተኛዋን መናትን (አያችሁን? የምትግገዟቸው ኃይል አላቸውን?) (የላቸውም)።

ሦስተኛይቱንም አነስተኛዋን መናትን (አያችሁን? የምትግገዟቸው ኃይል አላቸውን?) (የላቸውም)።

أَلَكُمُ ٱلذَّكَرُ وَلَهُ ٱلۡأُنثَىٰ

ለእናንተ ወንድ ለእርሱም ሴት (ልጅ) ይኖራልን?

ለእናንተ ወንድ ለእርሱም ሴት (ልጅ) ይኖራልን?

تِلۡكَ إِذٗا قِسۡمَةٞ ضِيزَىٰٓ

ይህቺ ያን ጊዜ አድላዊ ክፍፍል ናት፡፡

ይህቺ ያን ጊዜ አድላዊ ክፍፍል ናት፡፡

إِنۡ هِيَ إِلَّآ أَسۡمَآءٞ سَمَّيۡتُمُوهَآ أَنتُمۡ وَءَابَآؤُكُم مَّآ أَنزَلَ ٱللَّهُ بِهَا مِن سُلۡطَٰنٍۚ إِن يَتَّبِعُونَ إِلَّا ٱلظَّنَّ وَمَا تَهۡوَى ٱلۡأَنفُسُۖ وَلَقَدۡ جَآءَهُم مِّن رَّبِّهِمُ ٱلۡهُدَىٰٓ

እነርሱ እናንተና አባቶቻችሁ (አማልክት ብላችሁ) የጠራችኋቸው ስሞች ብቻ እንጅ ምንም አይደሉም፡፡ አላህ በእርሷ (መግገዛት) ምንም ማስረጃ አላወረደም፡፡ ከጌታቸውም መምሪያ የመጣላቸው ሲኾኑ ጥርጣሬንና ነፍሶች የሚዘነበሉበትን እንጅ ሌላ አይከተሉም፡፡

እነርሱ እናንተና አባቶቻችሁ (አማልክት ብላችሁ) የጠራችኋቸው ስሞች ብቻ እንጅ ምንም አይደሉም፡፡ አላህ በእርሷ (መግገዛት) ምንም ማስረጃ አላወረደም፡፡ ከጌታቸውም መምሪያ የመጣላቸው ሲኾኑ ጥርጣሬንና ነፍሶች የሚዘነበሉበትን እንጅ ሌላ አይከተሉም፡፡

أَمۡ لِلۡإِنسَٰنِ مَا تَمَنَّىٰ

ለሰው የተመኘው ሁሉ አለውን?

ለሰው የተመኘው ሁሉ አለውን?

فَلِلَّهِ ٱلۡأٓخِرَةُ وَٱلۡأُولَىٰ

መጨረሻይቱም መጀመሪያይቱም (ዓለም) የአላህ ብቻ ናቸው፡፡

መጨረሻይቱም መጀመሪያይቱም (ዓለም) የአላህ ብቻ ናቸው፡፡

۞ وَكَم مِّن مَّلَكٖ فِي ٱلسَّمَٰوَٰتِ لَا تُغۡنِي شَفَٰعَتُهُمۡ شَيۡـًٔا إِلَّا مِنۢ بَعۡدِ أَن يَأۡذَنَ ٱللَّهُ لِمَن يَشَآءُ وَيَرۡضَىٰٓ

በሰማያት ውስጥ ካለ መልአክም ብዙዎች (ሊማለዱለት) ለሚሻውና ለሚወደው ሰው ከፈቀደ በኋላ ቢኾን እንጅ ምልጃቸው ምንም አትጠቅምም፡፡

በሰማያት ውስጥ ካለ መልአክም ብዙዎች (ሊማለዱለት) ለሚሻውና ለሚወደው ሰው ከፈቀደ በኋላ ቢኾን እንጅ ምልጃቸው ምንም አትጠቅምም፡፡

إِنَّ ٱلَّذِينَ لَا يُؤۡمِنُونَ بِٱلۡأٓخِرَةِ لَيُسَمُّونَ ٱلۡمَلَٰٓئِكَةَ تَسۡمِيَةَ ٱلۡأُنثَىٰ

እነዚያ በመጨረሻይቱ ዓለም የማያምኑት መላእክትን በሴት አጠራር ይጠራሉ፡፡

እነዚያ በመጨረሻይቱ ዓለም የማያምኑት መላእክትን በሴት አጠራር ይጠራሉ፡፡

وَمَا لَهُم بِهِۦ مِنۡ عِلۡمٍۖ إِن يَتَّبِعُونَ إِلَّا ٱلظَّنَّۖ وَإِنَّ ٱلظَّنَّ لَا يُغۡنِي مِنَ ٱلۡحَقِّ شَيۡـٔٗا

ለእነርሱም በእርሱ ምንም ዕውቀት የላቸውም፡፡ ጥርጣሬን እንጅ ሌላን አይከተሉም፡፡ ጥርጣሬም ከእውነት ምንም አያብቃቃም፡፡

ለእነርሱም በእርሱ ምንም ዕውቀት የላቸውም፡፡ ጥርጣሬን እንጅ ሌላን አይከተሉም፡፡ ጥርጣሬም ከእውነት ምንም አያብቃቃም፡፡

فَأَعۡرِضۡ عَن مَّن تَوَلَّىٰ عَن ذِكۡرِنَا وَلَمۡ يُرِدۡ إِلَّا ٱلۡحَيَوٰةَ ٱلدُّنۡيَا

ከግሣጼያችንም (ከቁርኣን) ከሸሸና አነስተኛይቱን ሕይወት እንጅ ሌላን ከማይሻ ሰው ዙር (ተወው)፡፡

ከግሣጼያችንም (ከቁርኣን) ከሸሸና አነስተኛይቱን ሕይወት እንጅ ሌላን ከማይሻ ሰው ዙር (ተወው)፡፡

ذَٰلِكَ مَبۡلَغُهُم مِّنَ ٱلۡعِلۡمِۚ إِنَّ رَبَّكَ هُوَ أَعۡلَمُ بِمَن ضَلَّ عَن سَبِيلِهِۦ وَهُوَ أَعۡلَمُ بِمَنِ ٱهۡتَدَىٰ

ይህ (አነስተኛይቱን ሕይወት መምረጥ) ከዕውቀት ድካቸው ነው፡፡ ጌታህ እርሱ ከመንገዱ የተሳሳተውን በእርግጥ ዐዋቂ ነው፡፡ እርሱም የቀናውን ሰው ዐዋቂ ነው፡፡

ይህ (አነስተኛይቱን ሕይወት መምረጥ) ከዕውቀት ድካቸው ነው፡፡ ጌታህ እርሱ ከመንገዱ የተሳሳተውን በእርግጥ ዐዋቂ ነው፡፡ እርሱም የቀናውን ሰው ዐዋቂ ነው፡፡

وَلِلَّهِ مَا فِي ٱلسَّمَٰوَٰتِ وَمَا فِي ٱلۡأَرۡضِ لِيَجۡزِيَ ٱلَّذِينَ أَسَٰٓـُٔواْ بِمَا عَمِلُواْ وَيَجۡزِيَ ٱلَّذِينَ أَحۡسَنُواْ بِٱلۡحُسۡنَى

በሰማያት ያለውና በምድር ያለው ሁሉ የአላህ ነው፡፡ እነዚያን ያጠፉትን በሠሩት ሊመነዳ (ሊቀጣ) እነዚያን ያሳመሩትንም በመልካሚቱ (ገነት) ሊመነዳ (ነው)፡፡

በሰማያት ያለውና በምድር ያለው ሁሉ የአላህ ነው፡፡ እነዚያን ያጠፉትን በሠሩት ሊመነዳ (ሊቀጣ) እነዚያን ያሳመሩትንም በመልካሚቱ (ገነት) ሊመነዳ (ነው)፡፡

ٱلَّذِينَ يَجۡتَنِبُونَ كَبَٰٓئِرَ ٱلۡإِثۡمِ وَٱلۡفَوَٰحِشَ إِلَّا ٱللَّمَمَۚ إِنَّ رَبَّكَ وَٰسِعُ ٱلۡمَغۡفِرَةِۚ هُوَ أَعۡلَمُ بِكُمۡ إِذۡ أَنشَأَكُم مِّنَ ٱلۡأَرۡضِ وَإِذۡ أَنتُمۡ أَجِنَّةٞ فِي بُطُونِ أُمَّهَٰتِكُمۡۖ فَلَا تُزَكُّوٓاْ أَنفُسَكُمۡۖ هُوَ أَعۡلَمُ بِمَنِ ٱتَّقَىٰٓ

(እነርሱ) እነዚያ የኃጢኣትን ታላለቆችና አስጸያፊዎቹን የሚርቁ ናቸው፡፡ ግን ትናንሾቹ (የሚማሩ) ናቸው፡፡ ጌታህ ምሕረተ ሰፊ ነውና፡፡ ከምድር በፈጠራችሁ ጊዜ እናንተም በእናቶቻችሁ ሆዶች ውስጥ ሽሎች በኾናችሁ ጊዜ እርሱ በናንተ (ኹነታ) ዐዋቂ ነው፡፡ ነፍሶቻችሁንም አታወድሱ እርሱ የሚፈራውን ሰው ዐዋቂ ነው፡፡

(እነርሱ) እነዚያ የኃጢኣትን ታላለቆችና አስጸያፊዎቹን የሚርቁ ናቸው፡፡ ግን ትናንሾቹ (የሚማሩ) ናቸው፡፡ ጌታህ ምሕረተ ሰፊ ነውና፡፡ ከምድር በፈጠራችሁ ጊዜ እናንተም በእናቶቻችሁ ሆዶች ውስጥ ሽሎች በኾናችሁ ጊዜ እርሱ በናንተ (ኹነታ) ዐዋቂ ነው፡፡ ነፍሶቻችሁንም አታወድሱ እርሱ የሚፈራውን ሰው ዐዋቂ ነው፡፡

أَفَرَءَيۡتَ ٱلَّذِي تَوَلَّىٰ

ያንን (ከእምነት) የዞረውን አየህን?

ያንን (ከእምነት) የዞረውን አየህን?

وَأَعۡطَىٰ قَلِيلٗا وَأَكۡدَىٰٓ

ጥቂትን የሰጠውንና ያቋረጠውንም (አየህን?)

ጥቂትን የሰጠውንና ያቋረጠውንም (አየህን?)

أَعِندَهُۥ عِلۡمُ ٱلۡغَيۡبِ فَهُوَ يَرَىٰٓ

የሩቁ ምስጢር ዕውቀት እርሱ ዘንድ አልለን? ስለዚህ እርሱ ያያልን?

የሩቁ ምስጢር ዕውቀት እርሱ ዘንድ አልለን? ስለዚህ እርሱ ያያልን?

أَمۡ لَمۡ يُنَبَّأۡ بِمَا فِي صُحُفِ مُوسَىٰ

ይልቁንም በዚያ በሙሳ ጽሑፎች ውስጥ ባለው ነገር አልተነገረምን?

ይልቁንም በዚያ በሙሳ ጽሑፎች ውስጥ ባለው ነገር አልተነገረምን?

وَإِبۡرَٰهِيمَ ٱلَّذِي وَفَّىٰٓ

በዚያም (የታዘዘውን) በፈጸመው በኢብራሂም (ጽሑፎች ውስጥ ባለው አልተነገረምን?)

በዚያም (የታዘዘውን) በፈጸመው በኢብራሂም (ጽሑፎች ውስጥ ባለው አልተነገረምን?)

أَلَّا تَزِرُ وَازِرَةٞ وِزۡرَ أُخۡرَىٰ

(እርሱም ኃጢያት) ተሸካሚ ነፍስ የሌላይቱን ነፍስ ኃጢኣት አትሸከምም፡፡

(እርሱም ኃጢያት) ተሸካሚ ነፍስ የሌላይቱን ነፍስ ኃጢኣት አትሸከምም፡፡

وَأَن لَّيۡسَ لِلۡإِنسَٰنِ إِلَّا مَا سَعَىٰ

ለሰውም ሁሉ የሠራው እንጅ ሌላ የለውም፡፡

ለሰውም ሁሉ የሠራው እንጅ ሌላ የለውም፡፡

وَأَنَّ سَعۡيَهُۥ سَوۡفَ يُرَىٰ

ሥራውም ሁሉ ወደ ፊት ይታያል፡፡

ሥራውም ሁሉ ወደ ፊት ይታያል፡፡

ثُمَّ يُجۡزَىٰهُ ٱلۡجَزَآءَ ٱلۡأَوۡفَىٰ

ከዚያም ሙሉውን ምንዳ ይመነዳዋል፡፡

ከዚያም ሙሉውን ምንዳ ይመነዳዋል፡፡

وَأَنَّ إِلَىٰ رَبِّكَ ٱلۡمُنتَهَىٰ

መጨረሻውም ወደ ጌታህ ብቻ ነው፡፡

መጨረሻውም ወደ ጌታህ ብቻ ነው፡፡

وَأَنَّهُۥ هُوَ أَضۡحَكَ وَأَبۡكَىٰ

እነሆ እርሱም አስሳቀ፣ አስለቀሰም፡፡

እነሆ እርሱም አስሳቀ፣ አስለቀሰም፡፡

وَأَنَّهُۥ هُوَ أَمَاتَ وَأَحۡيَا

እነሆ እርሱም ገደለ፣ አስነሳም፡፡

እነሆ እርሱም ገደለ፣ አስነሳም፡፡

وَأَنَّهُۥ خَلَقَ ٱلزَّوۡجَيۡنِ ٱلذَّكَرَ وَٱلۡأُنثَىٰ

እርሱም ሁለቱን ዓይነቶች ወንድንና ሴትን ፈጠረ፡፡

እርሱም ሁለቱን ዓይነቶች ወንድንና ሴትን ፈጠረ፡፡

مِن نُّطۡفَةٍ إِذَا تُمۡنَىٰ

ከፍትወት ጠብታ (በማህጸን ውስጥ) በምትፈሰስ ጊዜ፡፡

ከፍትወት ጠብታ (በማህጸን ውስጥ) በምትፈሰስ ጊዜ፡፡

وَأَنَّ عَلَيۡهِ ٱلنَّشۡأَةَ ٱلۡأُخۡرَىٰ

የኋለኛይቱም ማስነሳት በእርሱ ላይ ነው፡፡

የኋለኛይቱም ማስነሳት በእርሱ ላይ ነው፡፡

وَأَنَّهُۥ هُوَ أَغۡنَىٰ وَأَقۡنَىٰ

እነሆ እርሱም አከበረ፣ ጥሪተኛም አደረገ፡፡

እነሆ እርሱም አከበረ፣ ጥሪተኛም አደረገ፡፡

وَأَنَّهُۥ هُوَ رَبُّ ٱلشِّعۡرَىٰ

እነሆ እርሱም የሺዕራ ጌታ ነው፡፡

እነሆ እርሱም የሺዕራ ጌታ ነው፡፡

وَأَنَّهُۥٓ أَهۡلَكَ عَادًا ٱلۡأُولَىٰ

እነሆ እርሱም የፊተኛይቱን ዓድ አጥፍቷል፡፡

እነሆ እርሱም የፊተኛይቱን ዓድ አጥፍቷል፡፡

وَثَمُودَاْ فَمَآ أَبۡقَىٰ

ሰሙድንም (አጥፍቷል)፤ አላስቀረምም፡፡

ሰሙድንም (አጥፍቷል)፤ አላስቀረምም፡፡

وَقَوۡمَ نُوحٖ مِّن قَبۡلُۖ إِنَّهُمۡ كَانُواْ هُمۡ أَظۡلَمَ وَأَطۡغَىٰ

በፊትም የኑሕን ሕዝቦች (አጥፍቷል)፡፡ እነርሱ በጣም በደለኞችና እጅግ የጠመሙ እነርሱ ነበሩና፡፡

በፊትም የኑሕን ሕዝቦች (አጥፍቷል)፡፡ እነርሱ በጣም በደለኞችና እጅግ የጠመሙ እነርሱ ነበሩና፡፡

وَٱلۡمُؤۡتَفِكَةَ أَهۡوَىٰ

የተገለበጠችውንም ከተማ ደፋ፡፡

የተገለበጠችውንም ከተማ ደፋ፡፡

فَغَشَّىٰهَا مَا غَشَّىٰ

ያለበሳትንም አለበሳት፡፡

ያለበሳትንም አለበሳት፡፡

فَبِأَيِّ ءَالَآءِ رَبِّكَ تَتَمَارَىٰ

ከጌታህም ጸጋዎች በየትኛው ትጠራጠራለህ?

ከጌታህም ጸጋዎች በየትኛው ትጠራጠራለህ?

هَٰذَا نَذِيرٞ مِّنَ ٱلنُّذُرِ ٱلۡأُولَىٰٓ

ይህ ከፊተኞቹ አስፈራሪዎች (ጎሳ) የኾነ አስፈራሪ ነው፡፡

ይህ ከፊተኞቹ አስፈራሪዎች (ጎሳ) የኾነ አስፈራሪ ነው፡፡

أَزِفَتِ ٱلۡأٓزِفَةُ

ቀራቢይቱ (ኅልፈተ ዓለም) ቀረበች፡፡

ቀራቢይቱ (ኅልፈተ ዓለም) ቀረበች፡፡

لَيۡسَ لَهَا مِن دُونِ ٱللَّهِ كَاشِفَةٌ

ለእርሷ ከአላህ ሌላ ገላጭ የላትም፡፡

ለእርሷ ከአላህ ሌላ ገላጭ የላትም፡፡

أَفَمِنۡ هَٰذَا ٱلۡحَدِيثِ تَعۡجَبُونَ

ከዚህ ንግግር ትደነቃላችሁን?

ከዚህ ንግግር ትደነቃላችሁን?

وَتَضۡحَكُونَ وَلَا تَبۡكُونَ

ትስቃላችሁምን? አታለቅሱምን?

ትስቃላችሁምን? አታለቅሱምን?

وَأَنتُمۡ سَٰمِدُونَ

እናንተም ዘንጊዎች ናችሁ፡፡

እናንተም ዘንጊዎች ናችሁ፡፡

فَٱسۡجُدُواْۤ لِلَّهِۤ وَٱعۡبُدُواْ۩

ለአላህም ስገዱ ተገዙትም፡፡ {1}

{1} ኢዝህ አንድ የንባብ ሱጁድ (ሱጁዱትላዋ) ይደረጋል።
ለአላህም ስገዱ ተገዙትም፡፡ {1}
Footer Include