Header Include

Vertimas į amharų k. - Afrikos akademija

Išvertė Muchamed Zain Zahr Ad-Din. Išleido Afrikos akademija.

QR Code https://quran.islamcontent.com/lt/amharic_zain

إِذَا ٱلسَّمَآءُ ٱنشَقَّتۡ

1. ሰማይ በተቀደደች (በተሰነጠቀች) ጊዜ፤

1. ሰማይ በተቀደደች (በተሰነጠቀች) ጊዜ፤

وَأَذِنَتۡ لِرَبِّهَا وَحُقَّتۡ

2. የጌታዋንም ትዕዛዝ በሰማች ጊዜ፤ (ልትሰማ) ተገባትም፤

2. የጌታዋንም ትዕዛዝ በሰማች ጊዜ፤ (ልትሰማ) ተገባትም፤

وَإِذَا ٱلۡأَرۡضُ مُدَّتۡ

3. ምድርም በተለጠጠች ጊዜ፤

3. ምድርም በተለጠጠች ጊዜ፤

وَأَلۡقَتۡ مَا فِيهَا وَتَخَلَّتۡ

4. በውስጧ ያለውንም ሁሉ በጣለችና ባዶ በሆነች ጊዜ፤

4. በውስጧ ያለውንም ሁሉ በጣለችና ባዶ በሆነች ጊዜ፤

وَأَذِنَتۡ لِرَبِّهَا وَحُقَّتۡ

5. ለጌታዋም በሰማች ጊዜ፤ (ልትስማ) ተገባትም፤

5. ለጌታዋም በሰማች ጊዜ፤ (ልትስማ) ተገባትም፤

يَٰٓأَيُّهَا ٱلۡإِنسَٰنُ إِنَّكَ كَادِحٌ إِلَىٰ رَبِّكَ كَدۡحٗا فَمُلَٰقِيهِ

6. አንተ ሰው ሆይ! አንተ ጌታህን በሞት እስከምትገናኝ ድረስ ልፋትን ለፊ ነህ። ተገናኚዉም ነህ።

6. አንተ ሰው ሆይ! አንተ ጌታህን በሞት እስከምትገናኝ ድረስ ልፋትን ለፊ ነህ። ተገናኚዉም ነህ።

فَأَمَّا مَنۡ أُوتِيَ كِتَٰبَهُۥ بِيَمِينِهِۦ

7. ያ! መጽሐፉን በቀኝ እጅ የተሰጠውማ

7. ያ! መጽሐፉን በቀኝ እጅ የተሰጠውማ

فَسَوۡفَ يُحَاسَبُ حِسَابٗا يَسِيرٗا

8. በእርግጥ ቀላልን ምርመራ ይመረመራል።

8. በእርግጥ ቀላልን ምርመራ ይመረመራል።

وَيَنقَلِبُ إِلَىٰٓ أَهۡلِهِۦ مَسۡرُورٗا

9. ወደ ቤተሰቦቹም ተደሳች ሆኖ (በደስታ) ይመለሳል::

9. ወደ ቤተሰቦቹም ተደሳች ሆኖ (በደስታ) ይመለሳል::

وَأَمَّا مَنۡ أُوتِيَ كِتَٰبَهُۥ وَرَآءَ ظَهۡرِهِۦ

10. ያ ! መጽሐፉን በጀርባው በኩል የተሰጠው ግን

10. ያ ! መጽሐፉን በጀርባው በኩል የተሰጠው ግን

فَسَوۡفَ يَدۡعُواْ ثُبُورٗا

11. (ዋ! ጥፋቴ በማለት) ጥፋትን በእርግጥ ይጠራል::

11. (ዋ! ጥፋቴ በማለት) ጥፋትን በእርግጥ ይጠራል::

وَيَصۡلَىٰ سَعِيرًا

12. የተጋጋመች እሳትንም ይገባል::

12. የተጋጋመች እሳትንም ይገባል::

إِنَّهُۥ كَانَ فِيٓ أَهۡلِهِۦ مَسۡرُورًا

13. እርሱ በቤተሰቡ ውስጥ ተደሳች ነበርና፤

13. እርሱ በቤተሰቡ ውስጥ ተደሳች ነበርና፤

إِنَّهُۥ ظَنَّ أَن لَّن يَحُورَ

14. እርሱም ወደ አላህ እንደማይመለስ አሰበ።

14. እርሱም ወደ አላህ እንደማይመለስ አሰበ።

بَلَىٰٓۚ إِنَّ رَبَّهُۥ كَانَ بِهِۦ بَصِيرٗا

15. አይደለም (ይመለሳል)፤ ጌታው በእርሱ (መመለስ) አዋቂ ነው።

15. አይደለም (ይመለሳል)፤ ጌታው በእርሱ (መመለስ) አዋቂ ነው።

فَلَآ أُقۡسِمُ بِٱلشَّفَقِ

16. ስለሆነም በወጋገኑ እምላለሁ።

16. ስለሆነም በወጋገኑ እምላለሁ።

وَٱلَّيۡلِ وَمَا وَسَقَ

17. በሌሊቱና በሰበሰበዉም ሁሉ፤

17. በሌሊቱና በሰበሰበዉም ሁሉ፤

وَٱلۡقَمَرِ إِذَا ٱتَّسَقَ

18. በጨረቃውም በሞላ ጊዜ (እምላለሁ)።

18. በጨረቃውም በሞላ ጊዜ (እምላለሁ)።

لَتَرۡكَبُنَّ طَبَقًا عَن طَبَقٖ

19. ከአንድ እርከን ወደ ሌላ እርከን ትሸጋገራላችሁ።

19. ከአንድ እርከን ወደ ሌላ እርከን ትሸጋገራላችሁ።

فَمَا لَهُمۡ لَا يُؤۡمِنُونَ

20. የማያምኑት ለእነርሱ ምን አላቸው ( ምን ሆነው ነው)?

20. የማያምኑት ለእነርሱ ምን አላቸው ( ምን ሆነው ነው)?

وَإِذَا قُرِئَ عَلَيۡهِمُ ٱلۡقُرۡءَانُ لَا يَسۡجُدُونَۤ۩

21. በእነርሱ ላይ ቁርኣን በተነበበ ጊዜ የማይሰግዱትስ ለእነርሱ ምን አላቸውና ነው?

21. በእነርሱ ላይ ቁርኣን በተነበበ ጊዜ የማይሰግዱትስ ለእነርሱ ምን አላቸውና ነው?

بَلِ ٱلَّذِينَ كَفَرُواْ يُكَذِّبُونَ

22. በእርግጥ እነዚያ የካዱት ያስተባብላሉ።

22. በእርግጥ እነዚያ የካዱት ያስተባብላሉ።

وَٱللَّهُ أَعۡلَمُ بِمَا يُوعُونَ

23. አላህ በልቦቻቸው የሚቋጥሩትን ሁሉ አዋቂ ነው::

23. አላህ በልቦቻቸው የሚቋጥሩትን ሁሉ አዋቂ ነው::

فَبَشِّرۡهُم بِعَذَابٍ أَلِيمٍ

24. (መልዕክተኛችን ሙሐመድ ሆይ!) በአሳማሚ ቅጣት አብስራቸው።

24. (መልዕክተኛችን ሙሐመድ ሆይ!) በአሳማሚ ቅጣት አብስራቸው።

إِلَّا ٱلَّذِينَ ءَامَنُواْ وَعَمِلُواْ ٱلصَّٰلِحَٰتِ لَهُمۡ أَجۡرٌ غَيۡرُ مَمۡنُونِۭ

25.እነዚያ በአላህ አምነው መልካም ተግባራትን የሰሩት ሲቀሩ፤ ለእነርሱማ የማይቋረጥ ምንዳ አላቸው።

25.እነዚያ በአላህ አምነው መልካም ተግባራትን የሰሩት ሲቀሩ፤ ለእነርሱማ የማይቋረጥ ምንዳ አላቸው።
Footer Include