Amharic translation - Africa Academy
Translation of the Meanings of the Noble Qur'an
Translated by Muhammad Zain Zahruddin. Published by Africa Academy
وَٱلۡعَٰدِيَٰتِ ضَبۡحٗا
1. እያለከለኩ ሩዋጮች በሆኑ (ፈረሶች)፤
فَٱلۡمُورِيَٰتِ قَدۡحٗا
2. ምድርን በሸሆናቸው እያጋጩ የእሳት ብልጭታን አውጪዎች በሆኑትም (ፈረሶች)፤
فَٱلۡمُغِيرَٰتِ صُبۡحٗا
3. በማለዳ (በጧት) ወራሪዎች በሆኑትም ፈረሶች፤
فَأَثَرۡنَ بِهِۦ نَقۡعٗا
4. በእርሱም አቧራን በቀሰቀሱት፤
فَوَسَطۡنَ بِهِۦ جَمۡعًا
5.በፈረሰኞቻቸው በኩል (የጠላት) ስብስብ መሀልን በተጋፈጡትም (ፈረሶች) እምላለሁ።
إِنَّ ٱلۡإِنسَٰنَ لِرَبِّهِۦ لَكَنُودٞ
6. የሰው ልጅ ለጌታው ብርቱ ከሓዲ ነው::
وَإِنَّهُۥ عَلَىٰ ذَٰلِكَ لَشَهِيدٞ
7. እርሱም በዚያ ክህደቱ ላይ መስካሪ ነው::
وَإِنَّهُۥ لِحُبِّ ٱلۡخَيۡرِ لَشَدِيدٌ
8. እርሱም ገንዘብን በመውደድ ላይ በጣም ብርቱ ነው::
۞ أَفَلَا يَعۡلَمُ إِذَا بُعۡثِرَ مَا فِي ٱلۡقُبُورِ
9. የሰው ልጅ በመቃብሮች ዉስጥ ያሉት ሙታን ሁሉ በተቀሰቀሱ ጊዜ ምን እንደሚከሰት አያውቅምን?
وَحُصِّلَ مَا فِي ٱلصُّدُورِ
10. በልቦች ውስጥ ያለዉም ሁሉ በተገለጸ ጊዜ እንዴት እንደሚሆን አያውቅምን?
إِنَّ رَبَّهُم بِهِمۡ يَوۡمَئِذٖ لَّخَبِيرُۢ
11. ጌታቸው በዚያ ቀን በእነርሱ ነገር በእርግጥ ውስጠ አዋቂ ነው::
Share via