La traduction amharique - Muhammad Sâdiq
Traduction des sens du Noble Coran
Traduit par Cheikh Muhammad Sâdiq et Muhammad Ath-Thânî Habîb. Développement achevé sous la supervision du Centre Rawwâd At-Tarjamah (Les Pionniers de la Traduction), avec accès à la traduction originale dans le but de la réception des suggestions des lecteurs, d'évaluation et de développement continu.
ٱلۡقَارِعَةُ
ቆርቋሪይቱ (ጩኸት)፤
مَا ٱلۡقَارِعَةُ
ምን አስደናቂ ቆርቋሪ ናት!
وَمَآ أَدۡرَىٰكَ مَا ٱلۡقَارِعَةُ
ቆርቋሪይቱም ምን እንደኾነች ምን አሳወቀህ?
يَوۡمَ يَكُونُ ٱلنَّاسُ كَٱلۡفَرَاشِ ٱلۡمَبۡثُوثِ
ሰዎች እንደ ተበታተነ ቢራቢሮ (ወይም ኩብኩባ) በሚኾኑበት ቀን፤
وَتَكُونُ ٱلۡجِبَالُ كَٱلۡعِهۡنِ ٱلۡمَنفُوشِ
ጋራዎችም እንደ ተነደፈ ሱፍ በሚኾኑበት (ቀን ልቦችን በድንጋጤ ትቆረቁራለች፡፡)
فَأَمَّا مَن ثَقُلَتۡ مَوَٰزِينُهُۥ
ሚዛኖቹ የከበዱለት ሰውማ፤
فَهُوَ فِي عِيشَةٖ رَّاضِيَةٖ
እርሱ በምትወደድ ኑሮ ውስጥ ይኾናል፡፡
وَأَمَّا مَنۡ خَفَّتۡ مَوَٰزِينُهُۥ
ሚዛኖቹም የቀለሉበት ሰውማ፤
فَأُمُّهُۥ هَاوِيَةٞ
መኖሪያው ሃዊያህ ናት
وَمَآ أَدۡرَىٰكَ مَا هِيَهۡ
እርሷም ምን እንደ ኾነች ምን አሳወቀህ?
نَارٌ حَامِيَةُۢ
(እርሷ) በጣም ተኳሳ እሳት ናት፡፡
share_via