La traduction amharique - Muhammad Sâdiq

Traduction des sens du Noble Coran

Traduit par Cheikh Muhammad Sâdiq et Muhammad Ath-Thânî Habîb. Développement achevé sous la supervision du Centre Rawwâd At-Tarjamah (Les Pionniers de la Traduction), avec accès à la traduction originale dans le but de la réception des suggestions des lecteurs, d'évaluation et de développement continu.

QR Code https://quran.islamcontent.com/fr/amharic_sadiq

وَٱلَّيۡلِ إِذَا يَغۡشَىٰ

በሌሊቱ እምላለሁ (በጨለማው) በሚሸፍን ጊዜ፡፡

በሌሊቱ እምላለሁ (በጨለማው) በሚሸፍን ጊዜ፡፡

وَٱلنَّهَارِ إِذَا تَجَلَّىٰ

በቀኑም፤ በተገለጸ ጊዜ፡፡

በቀኑም፤ በተገለጸ ጊዜ፡፡

وَمَا خَلَقَ ٱلذَّكَرَ وَٱلۡأُنثَىٰٓ

ወንድንና ሴትን በፈጠረውም (አምላክ እምላለሁ)፡፡

ወንድንና ሴትን በፈጠረውም (አምላክ እምላለሁ)፡፡

إِنَّ سَعۡيَكُمۡ لَشَتَّىٰ

ሥራችሁ በእርግጥ የተለያየ ነው፡፡

ሥራችሁ በእርግጥ የተለያየ ነው፡፡

فَأَمَّا مَنۡ أَعۡطَىٰ وَٱتَّقَىٰ

የሰጠ ሰውማ ጌታውን የፈራም፡፡

የሰጠ ሰውማ ጌታውን የፈራም፡፡

وَصَدَّقَ بِٱلۡحُسۡنَىٰ

በመልካሚቱም (እምነት) ያረጋገጠ፤

በመልካሚቱም (እምነት) ያረጋገጠ፤

فَسَنُيَسِّرُهُۥ لِلۡيُسۡرَىٰ

ለገሪቱ ሥራ እናዘጋጀዋለን፡፡

ለገሪቱ ሥራ እናዘጋጀዋለን፡፡

وَأَمَّا مَنۢ بَخِلَ وَٱسۡتَغۡنَىٰ

የሰሰተ ሰውማ የተብቃቃም፤ (በራሱ የተመካ)፤

የሰሰተ ሰውማ የተብቃቃም፤ (በራሱ የተመካ)፤

وَكَذَّبَ بِٱلۡحُسۡنَىٰ

በመልካሚቱ (እምነት) ያሰተባበለም፤

በመልካሚቱ (እምነት) ያሰተባበለም፤

فَسَنُيَسِّرُهُۥ لِلۡعُسۡرَىٰ

ለክፉይቱ ሥራ እናዘጋጀዋለን፡፡

ለክፉይቱ ሥራ እናዘጋጀዋለን፡፡

وَمَا يُغۡنِي عَنۡهُ مَالُهُۥٓ إِذَا تَرَدَّىٰٓ

በወደቀም ጊዜ ገንዘቡ ከእርሱ ምንም አይጠቅመውም፡፡

በወደቀም ጊዜ ገንዘቡ ከእርሱ ምንም አይጠቅመውም፡፡

إِنَّ عَلَيۡنَا لَلۡهُدَىٰ

ቅኑን መንገድ መግለጽ በእኛ ላይ አለብን፡፡

ቅኑን መንገድ መግለጽ በእኛ ላይ አለብን፡፡

وَإِنَّ لَنَا لَلۡأٓخِرَةَ وَٱلۡأُولَىٰ

መጨረሻይቱም መጀመሪያይቱም ዓለም የእኛ ናቸው፡፡

መጨረሻይቱም መጀመሪያይቱም ዓለም የእኛ ናቸው፡፡

فَأَنذَرۡتُكُمۡ نَارٗا تَلَظَّىٰ

የምትንቀለቀልንም እሳት አስጠነቀቅኳችሁ (በላቸው)፡፡

የምትንቀለቀልንም እሳት አስጠነቀቅኳችሁ (በላቸው)፡፡

لَا يَصۡلَىٰهَآ إِلَّا ٱلۡأَشۡقَى

ከጠማማ በቀር ሌላ የማይገባት የኾነችን፡፡

ከጠማማ በቀር ሌላ የማይገባት የኾነችን፡፡

ٱلَّذِي كَذَّبَ وَتَوَلَّىٰ

ያ ያስተባበለና ከትዕዛዝ የሸሸው፡፡

ያ ያስተባበለና ከትዕዛዝ የሸሸው፡፡

وَسَيُجَنَّبُهَا ٱلۡأَتۡقَى

አላህን በጣም ፈሪውም በእርግጥ ይርቃታል፡፡

አላህን በጣም ፈሪውም በእርግጥ ይርቃታል፡፡

ٱلَّذِي يُؤۡتِي مَالَهُۥ يَتَزَكَّىٰ

ያ የሚጥራራ ኾኖ ገንዘቡን (ለድኾች) የሚሰጠው፡፡

ያ የሚጥራራ ኾኖ ገንዘቡን (ለድኾች) የሚሰጠው፡፡

وَمَا لِأَحَدٍ عِندَهُۥ مِن نِّعۡمَةٖ تُجۡزَىٰٓ

ለአንድም ሰው እርሱ ዘንድ የምትመለስ ውለታ የለችም፡፡

ለአንድም ሰው እርሱ ዘንድ የምትመለስ ውለታ የለችም፡፡

إِلَّا ٱبۡتِغَآءَ وَجۡهِ رَبِّهِ ٱلۡأَعۡلَىٰ

ግን የታላቅ ጌታውን ውዴታ ለመፈለግ (ይህንን ሠራ)፡፡

ግን የታላቅ ጌታውን ውዴታ ለመፈለግ (ይህንን ሠራ)፡፡

وَلَسَوۡفَ يَرۡضَىٰ

ወደፊትም በእርግጥ ይደሰታል፡፡

ወደፊትም በእርግጥ ይደሰታል፡፡