La traduction amharique - Muhammad Sâdiq

Traduction des sens du Noble Coran

Traduit par Cheikh Muhammad Sâdiq et Muhammad Ath-Thânî Habîb. Développement achevé sous la supervision du Centre Rawwâd At-Tarjamah (Les Pionniers de la Traduction), avec accès à la traduction originale dans le but de la réception des suggestions des lecteurs, d'évaluation et de développement continu.

QR Code https://quran.islamcontent.com/fr/amharic_sadiq

إِذَا ٱلسَّمَآءُ ٱنشَقَّتۡ

ሰማይ በተቀደደች ጊዜ፤

ሰማይ በተቀደደች ጊዜ፤

وَأَذِنَتۡ لِرَبِّهَا وَحُقَّتۡ

ለጌታዋም (ትዕዛዝ) በሰማች ጊዜ፤ (ልትሰማ) ተገባትም፤

ለጌታዋም (ትዕዛዝ) በሰማች ጊዜ፤ (ልትሰማ) ተገባትም፤

وَإِذَا ٱلۡأَرۡضُ مُدَّتۡ

ምድርም በተለጠጠች ጊዜ፤

ምድርም በተለጠጠች ጊዜ፤

وَأَلۡقَتۡ مَا فِيهَا وَتَخَلَّتۡ

በውስጧ ያለውንም ሁሉ በጣለችና ባዶ በኾነች ጊዜ፤

በውስጧ ያለውንም ሁሉ በጣለችና ባዶ በኾነች ጊዜ፤

وَأَذِنَتۡ لِرَبِّهَا وَحُقَّتۡ

ለጌታዋም በሰማች ጊዜ፤ (መስማት) ተገባትም፤ (ሰው ሁሉ ሥራውን ይገናኛል)፡፡

ለጌታዋም በሰማች ጊዜ፤ (መስማት) ተገባትም፤ (ሰው ሁሉ ሥራውን ይገናኛል)፡፡

يَٰٓأَيُّهَا ٱلۡإِنسَٰنُ إِنَّكَ كَادِحٌ إِلَىٰ رَبِّكَ كَدۡحٗا فَمُلَٰقِيهِ

አንተ ሰው ሆይ! አንተ ጌታህን (በሞት) እስከምትገናኝ ድረስ ልፋትን ለፊ ነህ፤ ተገናኚውም ነህ፡፡

አንተ ሰው ሆይ! አንተ ጌታህን (በሞት) እስከምትገናኝ ድረስ ልፋትን ለፊ ነህ፤ ተገናኚውም ነህ፡፡

فَأَمَّا مَنۡ أُوتِيَ كِتَٰبَهُۥ بِيَمِينِهِۦ

መጽሐፉን በቀኙ የተሰጠ ሰውማ፤

መጽሐፉን በቀኙ የተሰጠ ሰውማ፤

فَسَوۡفَ يُحَاسَبُ حِسَابٗا يَسِيرٗا

በእርግጥ ቀላልን ምርመራ ይመረመራል፡፡

በእርግጥ ቀላልን ምርመራ ይመረመራል፡፡

وَيَنقَلِبُ إِلَىٰٓ أَهۡلِهِۦ مَسۡرُورٗا

ወደ ቤተሰቦቹም ተደሳች ኾኖ ይመለሳል፡፡

ወደ ቤተሰቦቹም ተደሳች ኾኖ ይመለሳል፡፡

وَأَمَّا مَنۡ أُوتِيَ كِتَٰبَهُۥ وَرَآءَ ظَهۡرِهِۦ

መጽሐፉን በጀርባው ኋላ የተሰጠ ሰውማ፤

መጽሐፉን በጀርባው ኋላ የተሰጠ ሰውማ፤

فَسَوۡفَ يَدۡعُواْ ثُبُورٗا

(ዋ! ጥፋቴ በማለት) ጥፋትን በእርግጥ ይጠራል፡፡

(ዋ! ጥፋቴ በማለት) ጥፋትን በእርግጥ ይጠራል፡፡

وَيَصۡلَىٰ سَعِيرًا

የተጋጋመች እሳትንም ይገባል፡፡

የተጋጋመች እሳትንም ይገባል፡፡

إِنَّهُۥ كَانَ فِيٓ أَهۡلِهِۦ مَسۡرُورًا

እርሱ በቤተሰቡ ውስጥ ተደሳች ነበርና፡፡

እርሱ በቤተሰቡ ውስጥ ተደሳች ነበርና፡፡

إِنَّهُۥ ظَنَّ أَن لَّن يَحُورَ

እርሱ (ወደ አላህ) የማይመለስ መኾኑን አስቧልና፡፡

እርሱ (ወደ አላህ) የማይመለስ መኾኑን አስቧልና፡፡

بَلَىٰٓۚ إِنَّ رَبَّهُۥ كَانَ بِهِۦ بَصِيرٗا

አይደለም (ይመለሳል)፡፡ ጌታው በእርሱ (መመለስ) ዐዋቂ ነበር፤ (ነውም)፡፡

አይደለም (ይመለሳል)፡፡ ጌታው በእርሱ (መመለስ) ዐዋቂ ነበር፤ (ነውም)፡፡

فَلَآ أُقۡسِمُ بِٱلشَّفَقِ

(አትካዱ)፤ በወጋገኑ እምላለሁ፡፡

(አትካዱ)፤ በወጋገኑ እምላለሁ፡፡

وَٱلَّيۡلِ وَمَا وَسَقَ

በሌሊቱም በሰበሰውም ሁሉ፤

በሌሊቱም በሰበሰውም ሁሉ፤

وَٱلۡقَمَرِ إِذَا ٱتَّسَقَ

በጨረቃውም በሞላ ጊዜ (እምላለሁ)፡፡

በጨረቃውም በሞላ ጊዜ (እምላለሁ)፡፡

لَتَرۡكَبُنَّ طَبَقًا عَن طَبَقٖ

ከኹነታ በኋላ ወደ ሌላ ኹነታ ትለዋወጣላችሁ፡፡

ከኹነታ በኋላ ወደ ሌላ ኹነታ ትለዋወጣላችሁ፡፡

فَمَا لَهُمۡ لَا يُؤۡمِنُونَ

የማያምኑት ለእነርሱ ምን አላቸው?

የማያምኑት ለእነርሱ ምን አላቸው?

وَإِذَا قُرِئَ عَلَيۡهِمُ ٱلۡقُرۡءَانُ لَا يَسۡجُدُونَۤ۩

በእነርሱም ላይ ቁርኣን በተነበበ ጊዜ የማይሰግዱት፤ (ምንአላቸው?) [1]

[1] እዚህ አንድ የትላዋ ሱጁድ ይደረጋል።
በእነርሱም ላይ ቁርኣን በተነበበ ጊዜ የማይሰግዱት፤ (ምንአላቸው?) [1]

بَلِ ٱلَّذِينَ كَفَرُواْ يُكَذِّبُونَ

በእርግጡ እነዚያ የካዱት (በትንሣኤ) ያስተባብላሉ፡፡

በእርግጡ እነዚያ የካዱት (በትንሣኤ) ያስተባብላሉ፡፡

وَٱللَّهُ أَعۡلَمُ بِمَا يُوعُونَ

አላህም (በልቦቻቸው) የሚቆጥሩትን ዐዋቂ ነው፡፡

አላህም (በልቦቻቸው) የሚቆጥሩትን ዐዋቂ ነው፡፡

فَبَشِّرۡهُم بِعَذَابٍ أَلِيمٍ

በአሳማሚ ቅጣትም አብስራቸው፡፡

በአሳማሚ ቅጣትም አብስራቸው፡፡

إِلَّا ٱلَّذِينَ ءَامَنُواْ وَعَمِلُواْ ٱلصَّٰلِحَٰتِ لَهُمۡ أَجۡرٌ غَيۡرُ مَمۡنُونِۭ

ግን እነዚያ ያመኑና መልካሞችን የሠሩ ለእነርሱ የማይቆረጥ ምንዳ አልላቸው፡፡

ግን እነዚያ ያመኑና መልካሞችን የሠሩ ለእነርሱ የማይቆረጥ ምንዳ አልላቸው፡፡