La traduction amharique - Muhammad Sâdiq
Traduction des sens du Noble Coran
Traduit par Cheikh Muhammad Sâdiq et Muhammad Ath-Thânî Habîb. Développement achevé sous la supervision du Centre Rawwâd At-Tarjamah (Les Pionniers de la Traduction), avec accès à la traduction originale dans le but de la réception des suggestions des lecteurs, d'évaluation et de développement continu.
سَبِّحِ ٱسۡمَ رَبِّكَ ٱلۡأَعۡلَى
ከሁሉ በላይ የኾነውን ጌታህን ስም አሞግሥ፡፡
ٱلَّذِي خَلَقَ فَسَوَّىٰ
የዚያን (ሁሉን ነገር) የፈጠረውን ያስተካከለውንም፡፡
وَٱلَّذِي قَدَّرَ فَهَدَىٰ
የዚያንም የወሰነውን፡፡ (ለተፈጠረለት ነገር) የመራውንም፡፡
وَٱلَّذِيٓ أَخۡرَجَ ٱلۡمَرۡعَىٰ
የዚያንም ግጦሽን (ለምለም አድርጎ) ያወጣውን፡፡
فَجَعَلَهُۥ غُثَآءً أَحۡوَىٰ
(ከዚያ) ደረቅ ጥቁር ያደረገውንም (አምላክ ስም አሞግስ)፡፡
سَنُقۡرِئُكَ فَلَا تَنسَىٰٓ
(ቁርኣንን) በእርግጥ እናስነብብሃለን፤ አትረሳምም፡፡
إِلَّا مَا شَآءَ ٱللَّهُۚ إِنَّهُۥ يَعۡلَمُ ٱلۡجَهۡرَ وَمَا يَخۡفَىٰ
አላህ ከሻው ነገር በስተቀር፡፡ እርሱ ግልጹን የሚሸሸገውንም ሁሉ ያውቃልና፡፡
وَنُيَسِّرُكَ لِلۡيُسۡرَىٰ
ለገሪቱም (ሕግጋት) እንገጥምሃለን፡፡
فَذَكِّرۡ إِن نَّفَعَتِ ٱلذِّكۡرَىٰ
ግሣጼይቱ ብትጠቅም (ሰዎችን) ገሥጽም፡፡
سَيَذَّكَّرُ مَن يَخۡشَىٰ
(አላህን) የሚፈራ ሰው በእርግጥ ይገሠጻል፡፡
وَيَتَجَنَّبُهَا ٱلۡأَشۡقَى
መናጢውም ይርቃታል፡፡
ٱلَّذِي يَصۡلَى ٱلنَّارَ ٱلۡكُبۡرَىٰ
ያ ታላቂቱን እሳት የሚገባው፡፡
ثُمَّ لَا يَمُوتُ فِيهَا وَلَا يَحۡيَىٰ
ከዚያም በእርሷ ውስጥ አይሞትም ሕያውም አይኾንም፡፡
قَدۡ أَفۡلَحَ مَن تَزَكَّىٰ
የተጥራራ ሰው በእርግጥ ዳነ፡፡
وَذَكَرَ ٱسۡمَ رَبِّهِۦ فَصَلَّىٰ
የጌታውንም ስም ያወሳና የሰገደ፡፡
بَلۡ تُؤۡثِرُونَ ٱلۡحَيَوٰةَ ٱلدُّنۡيَا
ይልቁንም ቅርቢቱን ሕይወት ትመርጣላችሁ፡፡
وَٱلۡأٓخِرَةُ خَيۡرٞ وَأَبۡقَىٰٓ
መጨረሻይቱ (ሕይወት) በላጭ ሁል ጊዜ ዘውታሪም ስትኾን፡፡
إِنَّ هَٰذَا لَفِي ٱلصُّحُفِ ٱلۡأُولَىٰ
ይህ በፊተኞቹ መጻሕፍት ውስጥ ያልለ ነው፡፡
صُحُفِ إِبۡرَٰهِيمَ وَمُوسَىٰ
በኢብራሂምና በሙሳ ጽሑፎች ውስጥ፡፡
share_via