La traduction amharique - Académie d'Afrique
Traduction des sens du Noble Coran
La traduction par Muhammad Zayn Zahr Al-Dîn. Publiée par l'Académie d'Afrique.
ٱقۡرَأۡ بِٱسۡمِ رَبِّكَ ٱلَّذِي خَلَقَ
1. (መልዕክተኛችን ሙሐመድ ሆይ!) በዚያ (ሁሉንም ነገር) በፈጠረ ጌታህ ስም (ጀምርና) አንብብ! [1]
خَلَقَ ٱلۡإِنسَٰنَ مِنۡ عَلَقٍ
2. ሰውን ከረጋ ደም በፈጠረው (ጌታህ ስም)::
ٱقۡرَأۡ وَرَبُّكَ ٱلۡأَكۡرَمُ
3. (መልዕክተኛችን ሙሐመድ ሆይ!) አንብብ! ጌታህም በጣም ቸር ነው::
ٱلَّذِي عَلَّمَ بِٱلۡقَلَمِ
4. ያ በብዕር ያስተማረ (ጌታ)፤
عَلَّمَ ٱلۡإِنسَٰنَ مَا لَمۡ يَعۡلَمۡ
5. የሰውን ልጅ ያላወቀውን ሁሉ ያሳወቀ (ጌታ)::
كَلَّآ إِنَّ ٱلۡإِنسَٰنَ لَيَطۡغَىٰٓ
6. በእውነቱ የሰው ልጅ ወሰንን ያልፋል::
أَن رَّءَاهُ ٱسۡتَغۡنَىٰٓ
7. ራሱን የተብቃቃ ሆኖ በማየቱ ምክንያት
إِنَّ إِلَىٰ رَبِّكَ ٱلرُّجۡعَىٰٓ
8. መመለሻው ወደ ጌታህ ብቻ ነው::
أَرَءَيۡتَ ٱلَّذِي يَنۡهَىٰ
9. ያንን የሚከለክለውን አየህን?
عَبۡدًا إِذَا صَلَّىٰٓ
10. ባሪያን በሰገደ ጊዜ (የሚከለክለውን):
أَرَءَيۡتَ إِن كَانَ عَلَى ٱلۡهُدَىٰٓ
11. እስቲ ንገረኝ (ተከልካዩ ባሪያየ) በትክክል መንገድ ላይ ቢሆን፤
أَوۡ أَمَرَ بِٱلتَّقۡوَىٰٓ
12. ወይም (ፈጣሪውን) በመፍራት ቢያዝ ምን እንደሚሆን አየህን?
أَرَءَيۡتَ إِن كَذَّبَ وَتَوَلَّىٰٓ
13. እስቲ ንገረኝ (ከልካዩ) ቢያስተባብልና ከእምነት ቢሸሽ፤
أَلَمۡ يَعۡلَم بِأَنَّ ٱللَّهَ يَرَىٰ
14. አላህ የሚያይ መሆኑን አያውቅምን?
كَلَّا لَئِن لَّمۡ يَنتَهِ لَنَسۡفَعَۢا بِٱلنَّاصِيَةِ
15. ይታቀብ፤ የማይከለከል ከሆነ አናቱን ይዘን አንጎትተዋለን::
نَاصِيَةٖ كَٰذِبَةٍ خَاطِئَةٖ
16. ያቺን ውሸታምና ስህተተኛ የሆነችውን አናቱን::
فَلۡيَدۡعُ نَادِيَهُۥ
17. ሸንጎውንም ይጥራ፤
سَنَدۡعُ ٱلزَّبَانِيَةَ
18. እኛም ዘበኞቻችንን እንጠራለን::
كَلَّا لَا تُطِعۡهُ وَٱسۡجُدۡۤ وَٱقۡتَرِب۩
19. በጭራሽ፤ (መልዕክተኛችን ሙሐመድ ሆይ!) ይህን ለሚል ከሓዲ አትታዘዘው፤ ስገድ፤ ወደ አላህም ተቃረብ። [1]
share_via