Header Include

アムハラ語対訳

クルアーン・アムハラ語対訳 - Muhammad Sadeq and Muhammad Ath-Thany Habib ルゥワード翻訳事業センター監修

QR Code https://quran.islamcontent.com/ja/amharic_sadiq

إِذَا وَقَعَتِ ٱلۡوَاقِعَةُ

መከራይቱ በወደቀች ጊዜ፡፡

መከራይቱ በወደቀች ጊዜ፡፡

لَيۡسَ لِوَقۡعَتِهَا كَاذِبَةٌ

ለመውደቋ አስተባባይ (ነፍስ) የለችም፡፡

ለመውደቋ አስተባባይ (ነፍስ) የለችም፡፡

خَافِضَةٞ رَّافِعَةٌ

ዝቅ አድራጊና ከፍ አድራጊ ናት፡፡

ዝቅ አድራጊና ከፍ አድራጊ ናት፡፡

إِذَا رُجَّتِ ٱلۡأَرۡضُ رَجّٗا

ምድር መናወጥን በተናወጠች ጊዜ፡፡

ምድር መናወጥን በተናወጠች ጊዜ፡፡

وَبُسَّتِ ٱلۡجِبَالُ بَسّٗا

ተራራዎችም መፍፈርፈርን በተፈረፈሩ ጊዜ (እንደተፈጨ ዱቄት በኾኑ ጊዜ)፡፡

ተራራዎችም መፍፈርፈርን በተፈረፈሩ ጊዜ (እንደተፈጨ ዱቄት በኾኑ ጊዜ)፡፡

فَكَانَتۡ هَبَآءٗ مُّنۢبَثّٗا

የተበተነ ብናኝ በኾኑም ጊዜ

የተበተነ ብናኝ በኾኑም ጊዜ

وَكُنتُمۡ أَزۡوَٰجٗا ثَلَٰثَةٗ

ሦስት ዓይነቶችም በኾናችሁ ጊዜ (ታዋርዳለች፤ ታነሳለችም)፡፡

ሦስት ዓይነቶችም በኾናችሁ ጊዜ (ታዋርዳለች፤ ታነሳለችም)፡፡

فَأَصۡحَٰبُ ٱلۡمَيۡمَنَةِ مَآ أَصۡحَٰبُ ٱلۡمَيۡمَنَةِ

የቀኝ ጓዶችም ምን (የተከበሩ) የቀኝ ጓዶች ናቸው፡፡

የቀኝ ጓዶችም ምን (የተከበሩ) የቀኝ ጓዶች ናቸው፡፡

وَأَصۡحَٰبُ ٱلۡمَشۡـَٔمَةِ مَآ أَصۡحَٰبُ ٱلۡمَشۡـَٔمَةِ

የግራ ጓዶችም ምን (የተዋረዱ) የግራ ጓዶች ናቸው፡፡

የግራ ጓዶችም ምን (የተዋረዱ) የግራ ጓዶች ናቸው፡፡

وَٱلسَّٰبِقُونَ ٱلسَّٰبِقُونَ

(ለበጎ ሥራ) ቀዳሚዎቹም (ለገነት) ቀዳሚዎች ናቸው፡፡

(ለበጎ ሥራ) ቀዳሚዎቹም (ለገነት) ቀዳሚዎች ናቸው፡፡

أُوْلَٰٓئِكَ ٱلۡمُقَرَّبُونَ

እነዚያ ባለሟሎቹ ናቸው፡፡

እነዚያ ባለሟሎቹ ናቸው፡፡

فِي جَنَّٰتِ ٱلنَّعِيمِ

በመጠቀሚያ ገነቶች ውስጥ ሲኾኑ፡፡

በመጠቀሚያ ገነቶች ውስጥ ሲኾኑ፡፡

ثُلَّةٞ مِّنَ ٱلۡأَوَّلِينَ

ከፊተኞቹ ብዙ ጭፍሮች ናቸው፡፡

ከፊተኞቹ ብዙ ጭፍሮች ናቸው፡፡

وَقَلِيلٞ مِّنَ ٱلۡأٓخِرِينَ

ከኋለኞቹም ጥቂቶች ናቸው፡፡

ከኋለኞቹም ጥቂቶች ናቸው፡፡

عَلَىٰ سُرُرٖ مَّوۡضُونَةٖ

በተታቱ አልጋዎች ላይ ይኾናሉ፡፡

በተታቱ አልጋዎች ላይ ይኾናሉ፡፡

مُّتَّكِـِٔينَ عَلَيۡهَا مُتَقَٰبِلِينَ

በእርሷ ላይ የተመቻቹና ፊት ለፊት የተቅጣጩ ሲኾኑ፡፡

በእርሷ ላይ የተመቻቹና ፊት ለፊት የተቅጣጩ ሲኾኑ፡፡

يَطُوفُ عَلَيۡهِمۡ وِلۡدَٰنٞ مُّخَلَّدُونَ

በእነርሱ ላይ ሁል ጊዜ የማያረጁ ወጣቶች ልጆች ይዘዋወራሉ፡፡

በእነርሱ ላይ ሁል ጊዜ የማያረጁ ወጣቶች ልጆች ይዘዋወራሉ፡፡

بِأَكۡوَابٖ وَأَبَارِيقَ وَكَأۡسٖ مِّن مَّعِينٖ

ከጠጅ ምንጭም በብርጭቆዎችና በኩስኩስቶች በጽዋም (በእነርሱ ላይ ይዝዞራሉ)፡፡

ከጠጅ ምንጭም በብርጭቆዎችና በኩስኩስቶች በጽዋም (በእነርሱ ላይ ይዝዞራሉ)፡፡

لَّا يُصَدَّعُونَ عَنۡهَا وَلَا يُنزِفُونَ

ከእርሷ የራስ ምታት አያገኛቸውም፤ አይሰክሩምም፡፡

ከእርሷ የራስ ምታት አያገኛቸውም፤ አይሰክሩምም፡፡

وَفَٰكِهَةٖ مِّمَّا يَتَخَيَّرُونَ

ከሚመርጡትም ዓይነት እሸቶች፡፡

ከሚመርጡትም ዓይነት እሸቶች፡፡

وَلَحۡمِ طَيۡرٖ مِّمَّا يَشۡتَهُونَ

ከሚሹትም በኾነ የበራሪ ሥጋ (ይዞሩባቸዋል)፡፡

ከሚሹትም በኾነ የበራሪ ሥጋ (ይዞሩባቸዋል)፡፡

وَحُورٌ عِينٞ

ዓይናማዎች የኾኑ ነጫጭ ቆንጆዎችም አሏቸው፡፡

ዓይናማዎች የኾኑ ነጫጭ ቆንጆዎችም አሏቸው፡፡

كَأَمۡثَٰلِ ٱللُّؤۡلُوِٕ ٱلۡمَكۡنُونِ

ልክ እንደተሸፈነ ሉል መሰሎች የኾኑ፡፡

ልክ እንደተሸፈነ ሉል መሰሎች የኾኑ፡፡

جَزَآءَۢ بِمَا كَانُواْ يَعۡمَلُونَ

በዚያ ይሠሩት በነበሩት ምክንያት ዋጋ ይኾን ዘንድ (ይህንን አደረግንላቸው)፡፡

በዚያ ይሠሩት በነበሩት ምክንያት ዋጋ ይኾን ዘንድ (ይህንን አደረግንላቸው)፡፡

لَا يَسۡمَعُونَ فِيهَا لَغۡوٗا وَلَا تَأۡثِيمًا

በውስጥዋ ውድቅ ንግግርንና መውወንጀልን አይሰሙም፡፡

በውስጥዋ ውድቅ ንግግርንና መውወንጀልን አይሰሙም፡፡

إِلَّا قِيلٗا سَلَٰمٗا سَلَٰمٗا

ግን ሰላም መባባልን (ይሰማሉ)፡፡

ግን ሰላም መባባልን (ይሰማሉ)፡፡

وَأَصۡحَٰبُ ٱلۡيَمِينِ مَآ أَصۡحَٰبُ ٱلۡيَمِينِ

የቀኝም ጓዶች ምንኛ (የከበሩ) የቀኝ ጓዶች!

የቀኝም ጓዶች ምንኛ (የከበሩ) የቀኝ ጓዶች!

فِي سِدۡرٖ مَّخۡضُودٖ

በተቀፈቀፈ (እሾህ በሌለው) ቁርቁራ ውስጥ ናቸው፡፡

በተቀፈቀፈ (እሾህ በሌለው) ቁርቁራ ውስጥ ናቸው፡፡

وَطَلۡحٖ مَّنضُودٖ

(ፍሬው) በተነባበረ በሙዝ ዛፍም፡፡

(ፍሬው) በተነባበረ በሙዝ ዛፍም፡፡

وَظِلّٖ مَّمۡدُودٖ

በተዘረጋ ጥላ ሥርም፡፡

በተዘረጋ ጥላ ሥርም፡፡

وَمَآءٖ مَّسۡكُوبٖ

በሚንቧቧ ውሃ አጠገብም፡፡

በሚንቧቧ ውሃ አጠገብም፡፡

وَفَٰكِهَةٖ كَثِيرَةٖ

ብዙ (ዓይነት) በኾኑ ፍራፍሬዎችም፡፡

ብዙ (ዓይነት) በኾኑ ፍራፍሬዎችም፡፡

لَّا مَقۡطُوعَةٖ وَلَا مَمۡنُوعَةٖ

የማትቋረጥም የማትከለከልም የኾነች፡፡

የማትቋረጥም የማትከለከልም የኾነች፡፡

وَفُرُشٖ مَّرۡفُوعَةٍ

ከፍ በተደረጉ ምንጣፎችም (ሴቶችም መካከል)፡፡

ከፍ በተደረጉ ምንጣፎችም (ሴቶችም መካከል)፡፡

إِنَّآ أَنشَأۡنَٰهُنَّ إِنشَآءٗ

እኛ አዲስ ፍጥረት አድርገን (ለእነርሱ) ፈጠርናቸው፡፡

እኛ አዲስ ፍጥረት አድርገን (ለእነርሱ) ፈጠርናቸው፡፡

فَجَعَلۡنَٰهُنَّ أَبۡكَارًا

ደናግሎችም አደረግናቸው፡፡

ደናግሎችም አደረግናቸው፡፡

عُرُبًا أَتۡرَابٗا

ለባሎቻቸው ተሽሞርሟሪዎች እኩያዎች (አደረግናቸው)፡፡

ለባሎቻቸው ተሽሞርሟሪዎች እኩያዎች (አደረግናቸው)፡፡

لِّأَصۡحَٰبِ ٱلۡيَمِينِ

ለቀኝ ጓዶች (አዘጋጀናቸው)፡፡

ለቀኝ ጓዶች (አዘጋጀናቸው)፡፡

ثُلَّةٞ مِّنَ ٱلۡأَوَّلِينَ

ከፊተኞቹ ብዙ ጭፍሮች ናቸው፡፡

ከፊተኞቹ ብዙ ጭፍሮች ናቸው፡፡

وَثُلَّةٞ مِّنَ ٱلۡأٓخِرِينَ

ከኋለኞቹም ብዙ ጭፍሮች ናቸው፡፡

ከኋለኞቹም ብዙ ጭፍሮች ናቸው፡፡

وَأَصۡحَٰبُ ٱلشِّمَالِ مَآ أَصۡحَٰبُ ٱلشِّمَالِ

የግራ ጓደኞችም ምንኛ (የተዋረዱ) የግራ ጓዶች! ናቸው፡፡

የግራ ጓደኞችም ምንኛ (የተዋረዱ) የግራ ጓዶች! ናቸው፡፡

فِي سَمُومٖ وَحَمِيمٖ

በመርዛም ነፋስ በጣም በፈላ ውሃም ውስጥ ናቸው፡፡

በመርዛም ነፋስ በጣም በፈላ ውሃም ውስጥ ናቸው፡፡

وَظِلّٖ مِّن يَحۡمُومٖ

ከጥቁር ጭስም በኾነ ጥላ ውስጥ፡፡

ከጥቁር ጭስም በኾነ ጥላ ውስጥ፡፡

لَّا بَارِدٖ وَلَا كَرِيمٍ

ቀዝቃዛም መልካምም ያልኾነ፡፡

ቀዝቃዛም መልካምም ያልኾነ፡፡

إِنَّهُمۡ كَانُواْ قَبۡلَ ذَٰلِكَ مُتۡرَفِينَ

እነርሱ ከዚህ በፊት ቅምጥሎች ነበሩና፡፡

እነርሱ ከዚህ በፊት ቅምጥሎች ነበሩና፡፡

وَكَانُواْ يُصِرُّونَ عَلَى ٱلۡحِنثِ ٱلۡعَظِيمِ

በታላቅ ኀጢአትም ላይ ይዘወትሩ ነበሩና፡፡

በታላቅ ኀጢአትም ላይ ይዘወትሩ ነበሩና፡፡

وَكَانُواْ يَقُولُونَ أَئِذَا مِتۡنَا وَكُنَّا تُرَابٗا وَعِظَٰمًا أَءِنَّا لَمَبۡعُوثُونَ

ይሉም ነበሩ፡- «በሞትንና ዐፈር፣ ዐጥንቶችም በኾን ጊዜ እኛ በእርግጥ የምንቀሰቀስ ነን?

ይሉም ነበሩ፡- «በሞትንና ዐፈር፣ ዐጥንቶችም በኾን ጊዜ እኛ በእርግጥ የምንቀሰቀስ ነን?

أَوَءَابَآؤُنَا ٱلۡأَوَّلُونَ

«የፊተኞቹ አባቶቻችንም?»

«የፊተኞቹ አባቶቻችንም?»

قُلۡ إِنَّ ٱلۡأَوَّلِينَ وَٱلۡأٓخِرِينَ

በላቸው፡- «ፊተኞቹም ኋለኞቹም፡፡

በላቸው፡- «ፊተኞቹም ኋለኞቹም፡፡

لَمَجۡمُوعُونَ إِلَىٰ مِيقَٰتِ يَوۡمٖ مَّعۡلُومٖ

«በተወሰነ ቀን ቀጠሮ በእርግጥ ተሰብሳቢዎች ናቸው፡፡

«በተወሰነ ቀን ቀጠሮ በእርግጥ ተሰብሳቢዎች ናቸው፡፡

ثُمَّ إِنَّكُمۡ أَيُّهَا ٱلضَّآلُّونَ ٱلۡمُكَذِّبُونَ

«ከዚያም እናንተ ጠማሞች አስተባባዮች ሆይ!

«ከዚያም እናንተ ጠማሞች አስተባባዮች ሆይ!

لَأٓكِلُونَ مِن شَجَرٖ مِّن زَقُّومٖ

« ከዘቁም ዛፍ በእርግጥ በይዎች ናችሁ፡፡

« ከዘቁም ዛፍ በእርግጥ በይዎች ናችሁ፡፡

فَمَالِـُٔونَ مِنۡهَا ٱلۡبُطُونَ

«ከእርሷም ሆዶቻችሁን ሞይዎች ናችሁ፡፡

«ከእርሷም ሆዶቻችሁን ሞይዎች ናችሁ፡፡

فَشَٰرِبُونَ عَلَيۡهِ مِنَ ٱلۡحَمِيمِ

«በእርሱ ላይም ከፈላ ውሃ ጠጪዎች ናችሁ፡፡

«በእርሱ ላይም ከፈላ ውሃ ጠጪዎች ናችሁ፡፡

فَشَٰرِبُونَ شُرۡبَ ٱلۡهِيمِ

«የተጠሙንም ግመሎች አጠጣጥ ብጤ ጠጪዎች ናችሁ፡፡»

«የተጠሙንም ግመሎች አጠጣጥ ብጤ ጠጪዎች ናችሁ፡፡»

هَٰذَا نُزُلُهُمۡ يَوۡمَ ٱلدِّينِ

ይህ በፍርዱ ቀን መስተንግዷቸው ነው፡፡

ይህ በፍርዱ ቀን መስተንግዷቸው ነው፡፡

نَحۡنُ خَلَقۡنَٰكُمۡ فَلَوۡلَا تُصَدِّقُونَ

እኛ ፈጠርናችሁ አታምኑምን?

እኛ ፈጠርናችሁ አታምኑምን?

أَفَرَءَيۡتُم مَّا تُمۡنُونَ

(በማኅፀኖች) የምታፈሱትን አያችሁን?

(በማኅፀኖች) የምታፈሱትን አያችሁን?

ءَأَنتُمۡ تَخۡلُقُونَهُۥٓ أَمۡ نَحۡنُ ٱلۡخَٰلِقُونَ

እናንተ ትፈጥሩታላችሁን? ወይስ እኛ ፈጣሪዎቹን ነን?

እናንተ ትፈጥሩታላችሁን? ወይስ እኛ ፈጣሪዎቹን ነን?

نَحۡنُ قَدَّرۡنَا بَيۡنَكُمُ ٱلۡمَوۡتَ وَمَا نَحۡنُ بِمَسۡبُوقِينَ

እኛ ሞትን (ጊዜውን) በመካከላችሁ ወሰንን፡፡ እኛም ተሸናፊዎች አይደለንም፡፡

እኛ ሞትን (ጊዜውን) በመካከላችሁ ወሰንን፡፡ እኛም ተሸናፊዎች አይደለንም፡፡

عَلَىٰٓ أَن نُّبَدِّلَ أَمۡثَٰلَكُمۡ وَنُنشِئَكُمۡ فِي مَا لَا تَعۡلَمُونَ

ብጤዎቻችሁን በመለወጥና በዚያ በማታውቁትም (ቅርጽ) እናንተን በመፍጠር ላይ (አንሸነፍም)፡፡

ብጤዎቻችሁን በመለወጥና በዚያ በማታውቁትም (ቅርጽ) እናንተን በመፍጠር ላይ (አንሸነፍም)፡፡

وَلَقَدۡ عَلِمۡتُمُ ٱلنَّشۡأَةَ ٱلۡأُولَىٰ فَلَوۡلَا تَذَكَّرُونَ

የፊተኛይቱንም አፈጣጠር በእርግጥ ዐውቃችኋል፡፡ አትገነዘቡምን?

የፊተኛይቱንም አፈጣጠር በእርግጥ ዐውቃችኋል፡፡ አትገነዘቡምን?

أَفَرَءَيۡتُم مَّا تَحۡرُثُونَ

የምትዘሩትንም አያችሁን?

የምትዘሩትንም አያችሁን?

ءَأَنتُمۡ تَزۡرَعُونَهُۥٓ أَمۡ نَحۡنُ ٱلزَّٰرِعُونَ

እናንተ ታበቅሉታላችሁን? ወይስ እኛ አብቃዮቹ ነን?

እናንተ ታበቅሉታላችሁን? ወይስ እኛ አብቃዮቹ ነን?

لَوۡ نَشَآءُ لَجَعَلۡنَٰهُ حُطَٰمٗا فَظَلۡتُمۡ تَفَكَّهُونَ

ብነሻ ኖሮ ደረቅ ስብርብር ባደረግነውና የምትደነቁም በኾናችሁ ነበር፡፡

ብነሻ ኖሮ ደረቅ ስብርብር ባደረግነውና የምትደነቁም በኾናችሁ ነበር፡፡

إِنَّا لَمُغۡرَمُونَ

«እኛ በዕዳ ተያዦች ነን፡፡

«እኛ በዕዳ ተያዦች ነን፡፡

بَلۡ نَحۡنُ مَحۡرُومُونَ

«በእርግጥም እኛ (ከመጠቀም) የተከለከልን ነን» (ትሉ ነበር)፡፡

«በእርግጥም እኛ (ከመጠቀም) የተከለከልን ነን» (ትሉ ነበር)፡፡

أَفَرَءَيۡتُمُ ٱلۡمَآءَ ٱلَّذِي تَشۡرَبُونَ

ያንንም የምትጠጡትን ውሃ አየችሁን?

ያንንም የምትጠጡትን ውሃ አየችሁን?

ءَأَنتُمۡ أَنزَلۡتُمُوهُ مِنَ ٱلۡمُزۡنِ أَمۡ نَحۡنُ ٱلۡمُنزِلُونَ

እናንተ ከደመናው አወረዳችሁትን? ወይስ እኛ አውራጆቹ ነን?

እናንተ ከደመናው አወረዳችሁትን? ወይስ እኛ አውራጆቹ ነን?

لَوۡ نَشَآءُ جَعَلۡنَٰهُ أُجَاجٗا فَلَوۡلَا تَشۡكُرُونَ

ብንሻ ኖሮ መርጋጋ ባደረግነው ነበር፡፡ አታመሰግኑምን?

ብንሻ ኖሮ መርጋጋ ባደረግነው ነበር፡፡ አታመሰግኑምን?

أَفَرَءَيۡتُمُ ٱلنَّارَ ٱلَّتِي تُورُونَ

ያቺንም የምትሰብቋትን እሳት አያችሁን?

ያቺንም የምትሰብቋትን እሳት አያችሁን?

ءَأَنتُمۡ أَنشَأۡتُمۡ شَجَرَتَهَآ أَمۡ نَحۡنُ ٱلۡمُنشِـُٔونَ

እናንተ ዛፏን ፈጠራችሁን? ወይስ እኛ ፈጣሪዎችዋ ነን?

እናንተ ዛፏን ፈጠራችሁን? ወይስ እኛ ፈጣሪዎችዋ ነን?

نَحۡنُ جَعَلۡنَٰهَا تَذۡكِرَةٗ وَمَتَٰعٗا لِّلۡمُقۡوِينَ

እኛ (ለገሀናም) ማስታወሻ ለመንገደኞችም መጠቀሚያ አደረግናት፡፡

እኛ (ለገሀናም) ማስታወሻ ለመንገደኞችም መጠቀሚያ አደረግናት፡፡

فَسَبِّحۡ بِٱسۡمِ رَبِّكَ ٱلۡعَظِيمِ

የታላቁን ጌታህንም ስም አወድስ፡፡

የታላቁን ጌታህንም ስም አወድስ፡፡

۞ فَلَآ أُقۡسِمُ بِمَوَٰقِعِ ٱلنُّجُومِ

በከዋክብትም መጥለቂያዎች እምላለሁ፡፡

በከዋክብትም መጥለቂያዎች እምላለሁ፡፡

وَإِنَّهُۥ لَقَسَمٞ لَّوۡ تَعۡلَمُونَ عَظِيمٌ

እርሱም ብታወቁ ታላቅ መሓላ ነው፡፡

እርሱም ብታወቁ ታላቅ መሓላ ነው፡፡

إِنَّهُۥ لَقُرۡءَانٞ كَرِيمٞ

እርሱ የከበረ ቁርኣን ነው፡፡

እርሱ የከበረ ቁርኣን ነው፡፡

فِي كِتَٰبٖ مَّكۡنُونٖ

በተጠበቀ መጽሐፍ ውስጥ ነው፡፡

በተጠበቀ መጽሐፍ ውስጥ ነው፡፡

لَّا يَمَسُّهُۥٓ إِلَّا ٱلۡمُطَهَّرُونَ

የተጥራሩት እንጅ ሌላ አይነካውም፡፡

የተጥራሩት እንጅ ሌላ አይነካውም፡፡

تَنزِيلٞ مِّن رَّبِّ ٱلۡعَٰلَمِينَ

ከዓለማት ጌታ የተወረደ ነው፡፡

ከዓለማት ጌታ የተወረደ ነው፡፡

أَفَبِهَٰذَا ٱلۡحَدِيثِ أَنتُم مُّدۡهِنُونَ

በዚህ ንግግር እናንተ ቸልተኞች ናችሁን?

በዚህ ንግግር እናንተ ቸልተኞች ናችሁን?

وَتَجۡعَلُونَ رِزۡقَكُمۡ أَنَّكُمۡ تُكَذِّبُونَ

ሲሳያችሁንም (ዝናምን) እናንተ የምታስተባብሉት ታደርጋላችሁን?

ሲሳያችሁንም (ዝናምን) እናንተ የምታስተባብሉት ታደርጋላችሁን?

فَلَوۡلَآ إِذَا بَلَغَتِ ٱلۡحُلۡقُومَ

(ነፍስ) ጉረሮንም በደረሰች ጊዜ፡፡

(ነፍስ) ጉረሮንም በደረሰች ጊዜ፡፡

وَأَنتُمۡ حِينَئِذٖ تَنظُرُونَ

እናንተ ያን ጊዜ የምታዩ ስትኾኑ፡፡

እናንተ ያን ጊዜ የምታዩ ስትኾኑ፡፡

وَنَحۡنُ أَقۡرَبُ إِلَيۡهِ مِنكُمۡ وَلَٰكِن لَّا تُبۡصِرُونَ

እኛም ግን አታዩም እንጅ ከእናንተ ይልቅ ወደእርሱ የቀረብን ስንኾን፡፡

እኛም ግን አታዩም እንጅ ከእናንተ ይልቅ ወደእርሱ የቀረብን ስንኾን፡፡

فَلَوۡلَآ إِن كُنتُمۡ غَيۡرَ مَدِينِينَ

የማትዳኙም ከኾናችሁ፡፡

የማትዳኙም ከኾናችሁ፡፡

تَرۡجِعُونَهَآ إِن كُنتُمۡ صَٰدِقِينَ

እውነተኞች እንደ ኾናችሁ (ነፍሲቱን ወደ አካሉ) ለምን አትመልሷትም፡፡

እውነተኞች እንደ ኾናችሁ (ነፍሲቱን ወደ አካሉ) ለምን አትመልሷትም፡፡

فَأَمَّآ إِن كَانَ مِنَ ٱلۡمُقَرَّبِينَ

(ሟቹ) ከባለሟሎቹ ቢኾንማ፡፡

(ሟቹ) ከባለሟሎቹ ቢኾንማ፡፡

فَرَوۡحٞ وَرَيۡحَانٞ وَجَنَّتُ نَعِيمٖ

(ለእርሱ) ዕረፍት፣ መልካም ሲሳይም፣ የመጠቀሚያ ገነትም አልለው፡፡

(ለእርሱ) ዕረፍት፣ መልካም ሲሳይም፣ የመጠቀሚያ ገነትም አልለው፡፡

وَأَمَّآ إِن كَانَ مِنۡ أَصۡحَٰبِ ٱلۡيَمِينِ

ከቀኝ ጓዶችም ቢኾንማ፡፡

ከቀኝ ጓዶችም ቢኾንማ፡፡

فَسَلَٰمٞ لَّكَ مِنۡ أَصۡحَٰبِ ٱلۡيَمِينِ

ከቀኝ ጓዶች ስለ ኾንክ ላንተ ሰላም አልለህ (ይባላል)፡፡

ከቀኝ ጓዶች ስለ ኾንክ ላንተ ሰላም አልለህ (ይባላል)፡፡

وَأَمَّآ إِن كَانَ مِنَ ٱلۡمُكَذِّبِينَ ٱلضَّآلِّينَ

ከሚያስዋሹት ጠማማዎችም ቢኾንማ፡፡

ከሚያስዋሹት ጠማማዎችም ቢኾንማ፡፡

فَنُزُلٞ مِّنۡ حَمِيمٖ

ከፈላ ውሃ የኾነ መስተንግዶ አልለው፡፡

ከፈላ ውሃ የኾነ መስተንግዶ አልለው፡፡

وَتَصۡلِيَةُ جَحِيمٍ

በገሀነም መቃጠልም (አልለው)፡፡

በገሀነም መቃጠልም (አልለው)፡፡

إِنَّ هَٰذَا لَهُوَ حَقُّ ٱلۡيَقِينِ

ይህ እርሱ እርግጠኛ እውነት ነው፡፡

ይህ እርሱ እርግጠኛ እውነት ነው፡፡

فَسَبِّحۡ بِٱسۡمِ رَبِّكَ ٱلۡعَظِيمِ

የታላቁንም ጌታህን ስም አወድስ፡፡

የታላቁንም ጌታህን ስም አወድስ፡፡
Footer Include