Header Include

アムハラ語対訳

クルアーン・アムハラ語対訳 - Muhammad Sadeq and Muhammad Ath-Thany Habib ルゥワード翻訳事業センター監修

QR Code https://quran.islamcontent.com/ja/amharic_sadiq

وَٱلنَّٰزِعَٰتِ غَرۡقٗا

በኃይል አውጪዎች በኾኑት፤

በኃይል አውጪዎች በኾኑት፤

وَٱلنَّٰشِطَٰتِ نَشۡطٗا

በቀስታ መምዘዝንም መዘዦች በኾኑት፤

በቀስታ መምዘዝንም መዘዦች በኾኑት፤

وَٱلسَّٰبِحَٰتِ سَبۡحٗا

መዋኘትም ዋኚዎች በኾኑት፤

መዋኘትም ዋኚዎች በኾኑት፤

فَٱلسَّٰبِقَٰتِ سَبۡقٗا

መቅደምንም ቀዳሚዎች በኾኑት፤

መቅደምንም ቀዳሚዎች በኾኑት፤

فَٱلۡمُدَبِّرَٰتِ أَمۡرٗا

ነገርንም አስተናባሪዎች በኾኑት (መላእክት) እምላለሁ፡፡ (በእርግጥ ትቀሰቀሳላችሁ)፡፡

ነገርንም አስተናባሪዎች በኾኑት (መላእክት) እምላለሁ፡፡ (በእርግጥ ትቀሰቀሳላችሁ)፡፡

يَوۡمَ تَرۡجُفُ ٱلرَّاجِفَةُ

ተርገፍጋፊይቱ (ምድር) በምትርገፈገፍበት ቀን፤

ተርገፍጋፊይቱ (ምድር) በምትርገፈገፍበት ቀን፤

تَتۡبَعُهَا ٱلرَّادِفَةُ

ለጣቂይቱ የምትከተላት ስትኾን (ትቀሰቀሳላችሁ)፡፡

ለጣቂይቱ የምትከተላት ስትኾን (ትቀሰቀሳላችሁ)፡፡

قُلُوبٞ يَوۡمَئِذٖ وَاجِفَةٌ

በዚያ ቀን ልቦች ተሸባሪዎች ናቸው፡፡

በዚያ ቀን ልቦች ተሸባሪዎች ናቸው፡፡

أَبۡصَٰرُهَا خَٰشِعَةٞ

ዓይኖቻቸው ተዋራጆች (አቀርቃሪዎች) ናቸው፡፡

ዓይኖቻቸው ተዋራጆች (አቀርቃሪዎች) ናቸው፡፡

يَقُولُونَ أَءِنَّا لَمَرۡدُودُونَ فِي ٱلۡحَافِرَةِ

«እኛ ወደ መጀመሪያይቱ ኹነታ ተመላሾች ነን?» ይላሉ፡፡

«እኛ ወደ መጀመሪያይቱ ኹነታ ተመላሾች ነን?» ይላሉ፡፡

أَءِذَا كُنَّا عِظَٰمٗا نَّخِرَةٗ

«የበሰበሱ አጥንቶች በኾን ጊዜ (እንቀሰቀሳለን?)»

«የበሰበሱ አጥንቶች በኾን ጊዜ (እንቀሰቀሳለን?)»

قَالُواْ تِلۡكَ إِذٗا كَرَّةٌ خَاسِرَةٞ

«ይህቺ ያን ጊዜ ባለ ከሳራ መመለስ ናት» ይላሉ፡፡

«ይህቺ ያን ጊዜ ባለ ከሳራ መመለስ ናት» ይላሉ፡፡

فَإِنَّمَا هِيَ زَجۡرَةٞ وَٰحِدَةٞ

እርሷም አንዲት ጩኸት ብቻ ናት፡፡

እርሷም አንዲት ጩኸት ብቻ ናት፡፡

فَإِذَا هُم بِٱلسَّاهِرَةِ

ወዲያውኑም እነርሱ እንቅልፍ በሌለባት (ምድር) ላይ ይኾናሉ፡፡

ወዲያውኑም እነርሱ እንቅልፍ በሌለባት (ምድር) ላይ ይኾናሉ፡፡

هَلۡ أَتَىٰكَ حَدِيثُ مُوسَىٰٓ

የሙሳ ወሬ መጣልህን?

የሙሳ ወሬ መጣልህን?

إِذۡ نَادَىٰهُ رَبُّهُۥ بِٱلۡوَادِ ٱلۡمُقَدَّسِ طُوًى

ጌታው በተቀደሰው ሸለቆ በጡዋ በጠራው ጊዜ፤

ጌታው በተቀደሰው ሸለቆ በጡዋ በጠራው ጊዜ፤

ٱذۡهَبۡ إِلَىٰ فِرۡعَوۡنَ إِنَّهُۥ طَغَىٰ

ወደ ፈርዖን ኺድ፡፡ እርሱ ወሰን አልፏልና፡፡

ወደ ፈርዖን ኺድ፡፡ እርሱ ወሰን አልፏልና፡፡

فَقُلۡ هَل لَّكَ إِلَىٰٓ أَن تَزَكَّىٰ

በለውም፡- «ወደ መጥራራትህ ላንተ (መንገድ) አለህን?»

በለውም፡- «ወደ መጥራራትህ ላንተ (መንገድ) አለህን?»

وَأَهۡدِيَكَ إِلَىٰ رَبِّكَ فَتَخۡشَىٰ

«ወደ ጌታህም ልመራህ ትፈራውም ዘንድ፤ (መንገድ አለህን?)» አለው፡፡

«ወደ ጌታህም ልመራህ ትፈራውም ዘንድ፤ (መንገድ አለህን?)» አለው፡፡

فَأَرَىٰهُ ٱلۡأٓيَةَ ٱلۡكُبۡرَىٰ

ታላቂቱንም ተዓምር አሳየው፡፡

ታላቂቱንም ተዓምር አሳየው፡፡

فَكَذَّبَ وَعَصَىٰ

አስተባበለም፤ አመጸም፡፡

አስተባበለም፤ አመጸም፡፡

ثُمَّ أَدۡبَرَ يَسۡعَىٰ

ከዚያም (ለማጥፋት) የሚተጋ ኾኖ ዞረ፡፡

ከዚያም (ለማጥፋት) የሚተጋ ኾኖ ዞረ፡፡

فَحَشَرَ فَنَادَىٰ

(ሰራዊቶቹን) ሰበሰበም፤ ተጣራም፡፡

(ሰራዊቶቹን) ሰበሰበም፤ ተጣራም፡፡

فَقَالَ أَنَا۠ رَبُّكُمُ ٱلۡأَعۡلَىٰ

አለም፡- «እኔ ታላቁ ጌታችሁ ነኝ፡፡»

አለም፡- «እኔ ታላቁ ጌታችሁ ነኝ፡፡»

فَأَخَذَهُ ٱللَّهُ نَكَالَ ٱلۡأٓخِرَةِ وَٱلۡأُولَىٰٓ

አላህም በኋለኛይቱና በፊተኛይቱ (ቃል) ቅጣት ያዘው፡፡

አላህም በኋለኛይቱና በፊተኛይቱ (ቃል) ቅጣት ያዘው፡፡

إِنَّ فِي ذَٰلِكَ لَعِبۡرَةٗ لِّمَن يَخۡشَىٰٓ

በዚህ ውስጥ ለሚፈራ ሰው በእርግጥ መገምገሚያ አለበት፡፡

በዚህ ውስጥ ለሚፈራ ሰው በእርግጥ መገምገሚያ አለበት፡፡

ءَأَنتُمۡ أَشَدُّ خَلۡقًا أَمِ ٱلسَّمَآءُۚ بَنَىٰهَا

ባፈጣጠር እናንተ ይበልጥ የበረታችሁ ናችሁን? ወይንስ ሰማይ? (አላህ) ገነባት፡፡

ባፈጣጠር እናንተ ይበልጥ የበረታችሁ ናችሁን? ወይንስ ሰማይ? (አላህ) ገነባት፡፡

رَفَعَ سَمۡكَهَا فَسَوَّىٰهَا

ከፍታዋን አጓነ፤ አስተካከላትም፡፡

ከፍታዋን አጓነ፤ አስተካከላትም፡፡

وَأَغۡطَشَ لَيۡلَهَا وَأَخۡرَجَ ضُحَىٰهَا

ሌሊቷንም አጨለመ፡፡ ቀንዋንም ገለጸ፡፡

ሌሊቷንም አጨለመ፡፡ ቀንዋንም ገለጸ፡፡

وَٱلۡأَرۡضَ بَعۡدَ ذَٰلِكَ دَحَىٰهَآ

ምድርንም ከዚህ በኋላ ዘረጋት፡፡

ምድርንም ከዚህ በኋላ ዘረጋት፡፡

أَخۡرَجَ مِنۡهَا مَآءَهَا وَمَرۡعَىٰهَا

ውሃዋንና ግጦሿን ከእርሷ አወጣ፡፡

ውሃዋንና ግጦሿን ከእርሷ አወጣ፡፡

وَٱلۡجِبَالَ أَرۡسَىٰهَا

ጋራዎችንም አደላደላቸው፡፡

ጋራዎችንም አደላደላቸው፡፡

مَتَٰعٗا لَّكُمۡ وَلِأَنۡعَٰمِكُمۡ

ለእናንተና ለእንስሶቻችሁ መጣቀሚያ ይኾን ዘንድ (ይህን አደረገ)፡፡

ለእናንተና ለእንስሶቻችሁ መጣቀሚያ ይኾን ዘንድ (ይህን አደረገ)፡፡

فَإِذَا جَآءَتِ ٱلطَّآمَّةُ ٱلۡكُبۡرَىٰ

ታላቂቱም መዐት በመጣች ጊዜ፣

ታላቂቱም መዐት በመጣች ጊዜ፣

يَوۡمَ يَتَذَكَّرُ ٱلۡإِنسَٰنُ مَا سَعَىٰ

ሰው ሁሉ የሠራውን በሚያስታውስበት ቀን፣

ሰው ሁሉ የሠራውን በሚያስታውስበት ቀን፣

وَبُرِّزَتِ ٱلۡجَحِيمُ لِمَن يَرَىٰ

ገሀነምም ለሚያይ ሰው በተገለጠች ጊዜ፣

ገሀነምም ለሚያይ ሰው በተገለጠች ጊዜ፣

فَأَمَّا مَن طَغَىٰ

የካደ ሰውማ፣

የካደ ሰውማ፣

وَءَاثَرَ ٱلۡحَيَوٰةَ ٱلدُّنۡيَا

ቅርቢቱንም ሕይወት የመረጠ፣

ቅርቢቱንም ሕይወት የመረጠ፣

فَإِنَّ ٱلۡجَحِيمَ هِيَ ٱلۡمَأۡوَىٰ

ገሀነም እርሷ በእርግጥ መኖሪያው ናት፡፡

ገሀነም እርሷ በእርግጥ መኖሪያው ናት፡፡

وَأَمَّا مَنۡ خَافَ مَقَامَ رَبِّهِۦ وَنَهَى ٱلنَّفۡسَ عَنِ ٱلۡهَوَىٰ

በጌታው ፊት መቆምን የፈራ ሰውማ ነፍሱንም ከዝንባሌዋ የከለከለ

በጌታው ፊት መቆምን የፈራ ሰውማ ነፍሱንም ከዝንባሌዋ የከለከለ

فَإِنَّ ٱلۡجَنَّةَ هِيَ ٱلۡمَأۡوَىٰ

ገነት እርሷ በእርግጥ መኖሪያው ናት፡፡

ገነት እርሷ በእርግጥ መኖሪያው ናት፡፡

يَسۡـَٔلُونَكَ عَنِ ٱلسَّاعَةِ أَيَّانَ مُرۡسَىٰهَا

«ከሰዓቲቱ መቼ ነው መኾኛዋ?» ሲሉ ይጠይቁሃል፡፡

«ከሰዓቲቱ መቼ ነው መኾኛዋ?» ሲሉ ይጠይቁሃል፡፡

فِيمَ أَنتَ مِن ذِكۡرَىٰهَآ

አንተ እርሷን ከማስታወስ በምን ውስጥ ነህ?

አንተ እርሷን ከማስታወስ በምን ውስጥ ነህ?

إِلَىٰ رَبِّكَ مُنتَهَىٰهَآ

(የዕውቀት) መጨረሻዋ ወደ ጌታህ ብቻ ነው፡፡

(የዕውቀት) መጨረሻዋ ወደ ጌታህ ብቻ ነው፡፡

إِنَّمَآ أَنتَ مُنذِرُ مَن يَخۡشَىٰهَا

አንተ የሚፈራትን ሰው አስፈራሪ ብቻ ነህ፡፡

አንተ የሚፈራትን ሰው አስፈራሪ ብቻ ነህ፡፡

كَأَنَّهُمۡ يَوۡمَ يَرَوۡنَهَا لَمۡ يَلۡبَثُوٓاْ إِلَّا عَشِيَّةً أَوۡ ضُحَىٰهَا

እነርሱ በሚያዩዋት ቀን ያንዲት ቀን ምሽትን ወይም ረፏዷን እንጅ ያልቆዩ ይመስላሉ፡፡

እነርሱ በሚያዩዋት ቀን ያንዲት ቀን ምሽትን ወይም ረፏዷን እንጅ ያልቆዩ ይመስላሉ፡፡
Footer Include