Header Include

アムハラ語対訳

クルアーン・アムハラ語対訳 - Muhammad Sadeq and Muhammad Ath-Thany Habib ルゥワード翻訳事業センター監修

QR Code https://quran.islamcontent.com/ja/amharic_sadiq

ٱقۡرَأۡ بِٱسۡمِ رَبِّكَ ٱلَّذِي خَلَقَ

አንብብ በዚያ (ሁሉን) በፈጠረው ጌታህ ስም፡፡{1}

{1} ይህ አንቀጽና ቀጥሎ ያሉት ከቁርአን መጀመሪያ የወረዱ አንቀጾች ናቸው። በኑር ተራራ ላይ በምገኘው የሂራእ ዋሻ ውስጥ ነቢዩ ሰ/ዐ/ወ/ ኸልዋ ወጥተው እያሉ ነው የወረደባቸው። (ቡኻሪና ሙስሊም፤ የወህይ አጀማመር ምእራፍ)
አንብብ በዚያ (ሁሉን) በፈጠረው ጌታህ ስም፡፡{1}

خَلَقَ ٱلۡإِنسَٰنَ مِنۡ عَلَقٍ

ሰውን ከረጋ ደም በፈጠረው (ጌታህ ስም)፡፡

ሰውን ከረጋ ደም በፈጠረው (ጌታህ ስም)፡፡

ٱقۡرَأۡ وَرَبُّكَ ٱلۡأَكۡرَمُ

አንብብ፤ ጌታህ በጣም ቸር ሲኾን፤

አንብብ፤ ጌታህ በጣም ቸር ሲኾን፤

ٱلَّذِي عَلَّمَ بِٱلۡقَلَمِ

ያ በብርዕ ያስተማረ፡፡

ያ በብርዕ ያስተማረ፡፡

عَلَّمَ ٱلۡإِنسَٰنَ مَا لَمۡ يَعۡلَمۡ

ሰውን ያላወቀውን ሁሉ ያሳወቀ ሲኾን፡፡

ሰውን ያላወቀውን ሁሉ ያሳወቀ ሲኾን፡፡

كَلَّآ إِنَّ ٱلۡإِنسَٰنَ لَيَطۡغَىٰٓ

በእውነቱ ሰው ወሰንን ያልፋል፡፡

በእውነቱ ሰው ወሰንን ያልፋል፡፡

أَن رَّءَاهُ ٱسۡتَغۡنَىٰٓ

ራሱን የተብቃቃ (ባለ ሀብት) ኾኖ ለማየቱ፡፡

ራሱን የተብቃቃ (ባለ ሀብት) ኾኖ ለማየቱ፡፡

إِنَّ إِلَىٰ رَبِّكَ ٱلرُّجۡعَىٰٓ

መመለሻው ወደ ጌታህ ብቻ ነው፡፡

መመለሻው ወደ ጌታህ ብቻ ነው፡፡

أَرَءَيۡتَ ٱلَّذِي يَنۡهَىٰ

አየህን? ያንን የሚከለክለውን፡፡

አየህን? ያንን የሚከለክለውን፡፡

عَبۡدًا إِذَا صَلَّىٰٓ

ባሪያን በሰገደ ጊዜ፤

ባሪያን በሰገደ ጊዜ፤

أَرَءَيۡتَ إِن كَانَ عَلَى ٱلۡهُدَىٰٓ

አየህን? ንገረኝ (ተከልካዩ) በትክክለኛ መንገድ ላይ ቢኾን፤

አየህን? ንገረኝ (ተከልካዩ) በትክክለኛ መንገድ ላይ ቢኾን፤

أَوۡ أَمَرَ بِٱلتَّقۡوَىٰٓ

ወይም (ፈጣሪውን) በመፍራት ቢያዝ፤

ወይም (ፈጣሪውን) በመፍራት ቢያዝ፤

أَرَءَيۡتَ إِن كَذَّبَ وَتَوَلَّىٰٓ

አየህን? ንገረኝ (ከልካዩ) ቢያስተባብልና (ከእምነት) ቢሸሽ፤

አየህን? ንገረኝ (ከልካዩ) ቢያስተባብልና (ከእምነት) ቢሸሽ፤

أَلَمۡ يَعۡلَم بِأَنَّ ٱللَّهَ يَرَىٰ

አላህ የሚያይ መኾኑን አያውቅምን?

አላህ የሚያይ መኾኑን አያውቅምን?

كَلَّا لَئِن لَّمۡ يَنتَهِ لَنَسۡفَعَۢا بِٱلنَّاصِيَةِ

ይተው ባይከለከል አናቱን ይዘን እንጎትተዋለን፡፡

ይተው ባይከለከል አናቱን ይዘን እንጎትተዋለን፡፡

نَاصِيَةٖ كَٰذِبَةٍ خَاطِئَةٖ

ውሸታም ስሕተተኛ የኾነችውን አናቱን፡፡

ውሸታም ስሕተተኛ የኾነችውን አናቱን፡፡

فَلۡيَدۡعُ نَادِيَهُۥ

ሸንጎውንም ይጥራ፡፡

ሸንጎውንም ይጥራ፡፡

سَنَدۡعُ ٱلزَّبَانِيَةَ

(እኛም) ዘበኞቻችንን እንጠራለን፡፡

(እኛም) ዘበኞቻችንን እንጠራለን፡፡

كَلَّا لَا تُطِعۡهُ وَٱسۡجُدۡۤ وَٱقۡتَرِب۩

ይከልከል አትታዘዘው፡፡ ስገድም፤ (ወደ አላህ) ተቃረብም፡፡ {1}

{1} እዚህ የንባብ ሱጁድ አለ። ይህ የመጨረሻ ሱጁድ ነው።
ይከልከል አትታዘዘው፡፡ ስገድም፤ (ወደ አላህ) ተቃረብም፡፡ {1}
Footer Include