アムハラ語対訳
クルアーン・アムハラ語対訳 - Muhammad Sadeq and Muhammad Ath-Thany Habib ルゥワード翻訳事業センター監修
سَبِّحِ ٱسۡمَ رَبِّكَ ٱلۡأَعۡلَى
ከሁሉ በላይ የኾነውን ጌታህን ስም አሞግሥ፡፡
ٱلَّذِي خَلَقَ فَسَوَّىٰ
የዚያን (ሁሉን ነገር) የፈጠረውን ያስተካከለውንም፡፡
وَٱلَّذِي قَدَّرَ فَهَدَىٰ
የዚያንም የወሰነውን፡፡ (ለተፈጠረለት ነገር) የመራውንም፡፡
وَٱلَّذِيٓ أَخۡرَجَ ٱلۡمَرۡعَىٰ
የዚያንም ግጦሽን (ለምለም አድርጎ) ያወጣውን፡፡
فَجَعَلَهُۥ غُثَآءً أَحۡوَىٰ
(ከዚያ) ደረቅ ጥቁር ያደረገውንም (አምላክ ስም አሞግስ)፡፡
سَنُقۡرِئُكَ فَلَا تَنسَىٰٓ
(ቁርኣንን) በእርግጥ እናስነብብሃለን፤ አትረሳምም፡፡
إِلَّا مَا شَآءَ ٱللَّهُۚ إِنَّهُۥ يَعۡلَمُ ٱلۡجَهۡرَ وَمَا يَخۡفَىٰ
አላህ ከሻው ነገር በስተቀር፡፡ እርሱ ግልጹን የሚሸሸገውንም ሁሉ ያውቃልና፡፡
وَنُيَسِّرُكَ لِلۡيُسۡرَىٰ
ለገሪቱም (ሕግጋት) እንገጥምሃለን፡፡
فَذَكِّرۡ إِن نَّفَعَتِ ٱلذِّكۡرَىٰ
ግሣጼይቱ ብትጠቅም (ሰዎችን) ገሥጽም፡፡
سَيَذَّكَّرُ مَن يَخۡشَىٰ
(አላህን) የሚፈራ ሰው በእርግጥ ይገሠጻል፡፡
وَيَتَجَنَّبُهَا ٱلۡأَشۡقَى
መናጢውም ይርቃታል፡፡
ٱلَّذِي يَصۡلَى ٱلنَّارَ ٱلۡكُبۡرَىٰ
ያ ታላቂቱን እሳት የሚገባው፡፡
ثُمَّ لَا يَمُوتُ فِيهَا وَلَا يَحۡيَىٰ
ከዚያም በእርሷ ውስጥ አይሞትም ሕያውም አይኾንም፡፡
قَدۡ أَفۡلَحَ مَن تَزَكَّىٰ
የተጥራራ ሰው በእርግጥ ዳነ፡፡
وَذَكَرَ ٱسۡمَ رَبِّهِۦ فَصَلَّىٰ
የጌታውንም ስም ያወሳና የሰገደ፡፡
بَلۡ تُؤۡثِرُونَ ٱلۡحَيَوٰةَ ٱلدُّنۡيَا
ይልቁንም ቅርቢቱን ሕይወት ትመርጣላችሁ፡፡
وَٱلۡأٓخِرَةُ خَيۡرٞ وَأَبۡقَىٰٓ
መጨረሻይቱ (ሕይወት) በላጭ ሁል ጊዜ ዘውታሪም ስትኾን፡፡
إِنَّ هَٰذَا لَفِي ٱلصُّحُفِ ٱلۡأُولَىٰ
ይህ በፊተኞቹ መጻሕፍት ውስጥ ያልለ ነው፡፡
صُحُفِ إِبۡرَٰهِيمَ وَمُوسَىٰ
በኢብራሂምና በሙሳ ጽሑፎች ውስጥ፡፡
مشاركة عبر