Header Include

الترجمة الأمهرية

ترجمة معاني القرآن الكريم إلى اللغة الامهرية، ترجمها الشيخ محمد صادق ومحمد الثاني حبيب. تم تصويبها بإشراف مركز رواد الترجمة، ويتاح الإطلاع على الترجمة الأصلية لغرض إبداء الرأي والتقييم والتطوير المستمر.

QR Code https://quran.islamcontent.com/ar/amharic_sadiq

وَٱلصَّٰٓفَّٰتِ صَفّٗا

መሰለፍን በሚሰለፉት፡፡

መሰለፍን በሚሰለፉት፡፡

فَٱلزَّٰجِرَٰتِ زَجۡرٗا

መገሠጽንም በሚገሥጹት፤

መገሠጽንም በሚገሥጹት፤

فَٱلتَّٰلِيَٰتِ ذِكۡرًا

ቁርኣንንም በሚያነቡት እምላለሁ፡፡

ቁርኣንንም በሚያነቡት እምላለሁ፡፡

إِنَّ إِلَٰهَكُمۡ لَوَٰحِدٞ

አምላካችሁ በእርግጥ አንድ ነው፡፡

አምላካችሁ በእርግጥ አንድ ነው፡፡

رَّبُّ ٱلسَّمَٰوَٰتِ وَٱلۡأَرۡضِ وَمَا بَيۡنَهُمَا وَرَبُّ ٱلۡمَشَٰرِقِ

የሰማያትና የምድር በመካከላቸው ያለውም ፍጡር ሁሉ ጌታ ነው፡፡ የምሥራቆችም ጌታ ነው፡፡

የሰማያትና የምድር በመካከላቸው ያለውም ፍጡር ሁሉ ጌታ ነው፡፡ የምሥራቆችም ጌታ ነው፡፡

إِنَّا زَيَّنَّا ٱلسَّمَآءَ ٱلدُّنۡيَا بِزِينَةٍ ٱلۡكَوَاكِبِ

እኛ ቅርቢቱን ሰማይ በከዋክብት ጌጥ አጌጥናት፡፡

እኛ ቅርቢቱን ሰማይ በከዋክብት ጌጥ አጌጥናት፡፡

وَحِفۡظٗا مِّن كُلِّ شَيۡطَٰنٖ مَّارِدٖ

አመጸኛም ከሆነ ሰይጣን ሁሉ መጠበቅን ጠበቅናት፡፡

አመጸኛም ከሆነ ሰይጣን ሁሉ መጠበቅን ጠበቅናት፡፡

لَّا يَسَّمَّعُونَ إِلَى ٱلۡمَلَإِ ٱلۡأَعۡلَىٰ وَيُقۡذَفُونَ مِن كُلِّ جَانِبٖ

ወደላይኛው ሰራዊት አያዳምጡም፡፡ ከየወገኑም ሁሉ ችቦ ይጣልባቸዋል፡፡

ወደላይኛው ሰራዊት አያዳምጡም፡፡ ከየወገኑም ሁሉ ችቦ ይጣልባቸዋል፡፡

دُحُورٗاۖ وَلَهُمۡ عَذَابٞ وَاصِبٌ

የሚባረሩ ሲሆኑ (ይጣልባቸዋል)፡፡ ለእነሱም ዘውታሪ ቅጣት አላቸው፡፡

የሚባረሩ ሲሆኑ (ይጣልባቸዋል)፡፡ ለእነሱም ዘውታሪ ቅጣት አላቸው፡፡

إِلَّا مَنۡ خَطِفَ ٱلۡخَطۡفَةَ فَأَتۡبَعَهُۥ شِهَابٞ ثَاقِبٞ

ንጥቂያን የነጠቀ ወዲያውም አብሪ ኮከብ የተከተለው ሲቀር፤ (እርሱ ይሰማዋል)፡፡

ንጥቂያን የነጠቀ ወዲያውም አብሪ ኮከብ የተከተለው ሲቀር፤ (እርሱ ይሰማዋል)፡፡

فَٱسۡتَفۡتِهِمۡ أَهُمۡ أَشَدُّ خَلۡقًا أَم مَّنۡ خَلَقۡنَآۚ إِنَّا خَلَقۡنَٰهُم مِّن طِينٖ لَّازِبِۭ

ጠይቃቸውም፤ እነርሱ በአፈጣጠር ይበልጥ የበረቱ ናቸውን? ወይስ እኛ (ከእነርሱ በፊት) የፈጠርነው? (ፍጡር) እኛ ከሚጣበቅ ጭቃ ፈጠርናቸው፡፡

ጠይቃቸውም፤ እነርሱ በአፈጣጠር ይበልጥ የበረቱ ናቸውን? ወይስ እኛ (ከእነርሱ በፊት) የፈጠርነው? (ፍጡር) እኛ ከሚጣበቅ ጭቃ ፈጠርናቸው፡፡

بَلۡ عَجِبۡتَ وَيَسۡخَرُونَ

ይልቁንም (በማስተባበላቸው) ተደነቅህ፤(ከመደነቅህ) ይሳለቃሉም፡፡

ይልቁንም (በማስተባበላቸው) ተደነቅህ፤(ከመደነቅህ) ይሳለቃሉም፡፡

وَإِذَا ذُكِّرُواْ لَا يَذۡكُرُونَ

በተገሠጹም ጊዜ አይመለሱም፡፡

በተገሠጹም ጊዜ አይመለሱም፡፡

وَإِذَا رَأَوۡاْ ءَايَةٗ يَسۡتَسۡخِرُونَ

ተዓምርን ባዩም ጊዜ ለመሳለቅ ይጠራራሉ፡፡

ተዓምርን ባዩም ጊዜ ለመሳለቅ ይጠራራሉ፡፡

وَقَالُوٓاْ إِنۡ هَٰذَآ إِلَّا سِحۡرٞ مُّبِينٌ

ይላሉም «ይህ ግልጽ ድግምት እንጂ ሌላ አይደለም፡፡

ይላሉም «ይህ ግልጽ ድግምት እንጂ ሌላ አይደለም፡፡

أَءِذَا مِتۡنَا وَكُنَّا تُرَابٗا وَعِظَٰمًا أَءِنَّا لَمَبۡعُوثُونَ

«በሞትንና ዐፈርና አጥንቶችም በኾን ጊዜ እኛ የምንቀሰቀስ ነን?

«በሞትንና ዐፈርና አጥንቶችም በኾን ጊዜ እኛ የምንቀሰቀስ ነን?

أَوَءَابَآؤُنَا ٱلۡأَوَّلُونَ

«የቀድሞዎቹ አባቶችንም? (ይላሉ)፡፡

«የቀድሞዎቹ አባቶችንም? (ይላሉ)፡፡

قُلۡ نَعَمۡ وَأَنتُمۡ دَٰخِرُونَ

«አዎን እናንተ ወራዶች ሆናችሁ (ትነሳላችሁ)» በላቸው፡፡

«አዎን እናንተ ወራዶች ሆናችሁ (ትነሳላችሁ)» በላቸው፡፡

فَإِنَّمَا هِيَ زَجۡرَةٞ وَٰحِدَةٞ فَإِذَا هُمۡ يَنظُرُونَ

እርሷም አንዲት ጩኸት ብቻ ናት፡፡ እነርሱም ወዲያውኑ (ምን እንደሚፈጸምባቸው) ያያሉ፡፡

እርሷም አንዲት ጩኸት ብቻ ናት፡፡ እነርሱም ወዲያውኑ (ምን እንደሚፈጸምባቸው) ያያሉ፡፡

وَقَالُواْ يَٰوَيۡلَنَا هَٰذَا يَوۡمُ ٱلدِّينِ

«ዋ ጥፋታችን! ይህ የፍርዱ ቀን ነው» ይላሉም፡፡

«ዋ ጥፋታችን! ይህ የፍርዱ ቀን ነው» ይላሉም፡፡

هَٰذَا يَوۡمُ ٱلۡفَصۡلِ ٱلَّذِي كُنتُم بِهِۦ تُكَذِّبُونَ

«ይህ ያ በእርሱ ታስተባብሉ የነበራችሁት መለያው ቀን ነው» (ይባላሉ)፡፡

«ይህ ያ በእርሱ ታስተባብሉ የነበራችሁት መለያው ቀን ነው» (ይባላሉ)፡፡

۞ ٱحۡشُرُواْ ٱلَّذِينَ ظَلَمُواْ وَأَزۡوَٰجَهُمۡ وَمَا كَانُواْ يَعۡبُدُونَ

(ለመላእክቶችም) «እነዚያን ነፍሶቻቸውን የበደሉትን ሰዎች ጓደኞቻቸውንም ይግገዟቸው የነበሩትንም (ጣዖታት) ሰብስቡ፡፡

(ለመላእክቶችም) «እነዚያን ነፍሶቻቸውን የበደሉትን ሰዎች ጓደኞቻቸውንም ይግገዟቸው የነበሩትንም (ጣዖታት) ሰብስቡ፡፡

مِن دُونِ ٱللَّهِ فَٱهۡدُوهُمۡ إِلَىٰ صِرَٰطِ ٱلۡجَحِيمِ

«ከአላህ ሌላ (የሚገዙዋቸውን ሰብስቧቸው) ወደ እሳት መንገድም ምሩዋቸው፡፡

«ከአላህ ሌላ (የሚገዙዋቸውን ሰብስቧቸው) ወደ እሳት መንገድም ምሩዋቸው፡፡

وَقِفُوهُمۡۖ إِنَّهُم مَّسۡـُٔولُونَ

«አቁሟቸውም፡፡ እነርሱ ተጠያቂዎች ናቸውና» (ይባላል)፡፡

«አቁሟቸውም፡፡ እነርሱ ተጠያቂዎች ናቸውና» (ይባላል)፡፡

مَا لَكُمۡ لَا تَنَاصَرُونَ

(ለእነርሱም) «የማትረዳዱት ለእናንተ ምን አላችሁ? (ይባላሉ)፡፡

(ለእነርሱም) «የማትረዳዱት ለእናንተ ምን አላችሁ? (ይባላሉ)፡፡

بَلۡ هُمُ ٱلۡيَوۡمَ مُسۡتَسۡلِمُونَ

በእርግጥ እነርሱ ዛሬ እጃቸውን የሰጡ ወራዳዎች ናቸው፡፡

በእርግጥ እነርሱ ዛሬ እጃቸውን የሰጡ ወራዳዎች ናቸው፡፡

وَأَقۡبَلَ بَعۡضُهُمۡ عَلَىٰ بَعۡضٖ يَتَسَآءَلُونَ

የሚወቃቀሱም ሆነው ከፊላቸው በከፊሉ ላይ ይመጣሉ፡፡

የሚወቃቀሱም ሆነው ከፊላቸው በከፊሉ ላይ ይመጣሉ፡፡

قَالُوٓاْ إِنَّكُمۡ كُنتُمۡ تَأۡتُونَنَا عَنِ ٱلۡيَمِينِ

(ለአስከታዮቹ) እናንተ ከስተቀኝ ትመጡብን ነበር ይላሉ፡፡

(ለአስከታዮቹ) እናንተ ከስተቀኝ ትመጡብን ነበር ይላሉ፡፡

قَالُواْ بَل لَّمۡ تَكُونُواْ مُؤۡمِنِينَ

(አስከታዮቹም) ይላሉ «አይደለም ፈጽሞ ምእምናን አልነበራችሁም፡፡

(አስከታዮቹም) ይላሉ «አይደለም ፈጽሞ ምእምናን አልነበራችሁም፡፡

وَمَا كَانَ لَنَا عَلَيۡكُم مِّن سُلۡطَٰنِۭۖ بَلۡ كُنتُمۡ قَوۡمٗا طَٰغِينَ

«ለእኛም በእናንተ ላይ ምንም ስልጣን አልነበረንም፡፡ በእርግጥ እናንተ ጠማሞች ሕዝቦች ነበራችሁ፡፡

«ለእኛም በእናንተ ላይ ምንም ስልጣን አልነበረንም፡፡ በእርግጥ እናንተ ጠማሞች ሕዝቦች ነበራችሁ፡፡

فَحَقَّ عَلَيۡنَا قَوۡلُ رَبِّنَآۖ إِنَّا لَذَآئِقُونَ

«በእኛም ላይ የጌታችን ቃል ተረጋገጠብን፤ እኛ (ሁላችንም ቅጣቱን) ቀማሾች ነን፡፡

«በእኛም ላይ የጌታችን ቃል ተረጋገጠብን፤ እኛ (ሁላችንም ቅጣቱን) ቀማሾች ነን፡፡

فَأَغۡوَيۡنَٰكُمۡ إِنَّا كُنَّا غَٰوِينَ

«ወደ ጥምመት ጠራናችሁም፡፡ እኛ ጠማሞች ነበርንና» (ይላሉ)፡፡

«ወደ ጥምመት ጠራናችሁም፡፡ እኛ ጠማሞች ነበርንና» (ይላሉ)፡፡

فَإِنَّهُمۡ يَوۡمَئِذٖ فِي ٱلۡعَذَابِ مُشۡتَرِكُونَ

ስለዚህ እነርሱ በዚያ ቀን በቅጣቱ ተጋሪዎች ናቸው፡፡

ስለዚህ እነርሱ በዚያ ቀን በቅጣቱ ተጋሪዎች ናቸው፡፡

إِنَّا كَذَٰلِكَ نَفۡعَلُ بِٱلۡمُجۡرِمِينَ

እኛ በአመጸኞች ሁሉ እንደዚሁ እንሠራለን፡፡

እኛ በአመጸኞች ሁሉ እንደዚሁ እንሠራለን፡፡

إِنَّهُمۡ كَانُوٓاْ إِذَا قِيلَ لَهُمۡ لَآ إِلَٰهَ إِلَّا ٱللَّهُ يَسۡتَكۡبِرُونَ

እነርሱ ከአላህ ሌላ አምላክ የለም በተባሉ ጊዜ ይኮሩ ነበሩ፡፡

እነርሱ ከአላህ ሌላ አምላክ የለም በተባሉ ጊዜ ይኮሩ ነበሩ፡፡

وَيَقُولُونَ أَئِنَّا لَتَارِكُوٓاْ ءَالِهَتِنَا لِشَاعِرٖ مَّجۡنُونِۭ

እኛ ለዕብድ ባለቅኔ ብለን አማልክቶቻችንን የምንተው ነን? ይሉም ነበር፡፡

እኛ ለዕብድ ባለቅኔ ብለን አማልክቶቻችንን የምንተው ነን? ይሉም ነበር፡፡

بَلۡ جَآءَ بِٱلۡحَقِّ وَصَدَّقَ ٱلۡمُرۡسَلِينَ

አይደለም እውነቱን (ሃይማኖት) አመጣ፡፡ መልክተኞቹንም እውነተኛነታቸውን አረጋገጠ፡፡

አይደለም እውነቱን (ሃይማኖት) አመጣ፡፡ መልክተኞቹንም እውነተኛነታቸውን አረጋገጠ፡፡

إِنَّكُمۡ لَذَآئِقُواْ ٱلۡعَذَابِ ٱلۡأَلِيمِ

እናንተ አሳማሚውን ቅጣት በእርግጥ ቀማሾች ናችሁ፡፡

እናንተ አሳማሚውን ቅጣት በእርግጥ ቀማሾች ናችሁ፡፡

وَمَا تُجۡزَوۡنَ إِلَّا مَا كُنتُمۡ تَعۡمَلُونَ

ትሠሩትም የነበራችሁትን እንጂ ሌላን አትመነዱም፡፡

ትሠሩትም የነበራችሁትን እንጂ ሌላን አትመነዱም፡፡

إِلَّا عِبَادَ ٱللَّهِ ٱلۡمُخۡلَصِينَ

ግን ምርጥ የሆኑት የአላህ ባሮች (ቅጣትን አይቀምሱም)፡፡

ግን ምርጥ የሆኑት የአላህ ባሮች (ቅጣትን አይቀምሱም)፡፡

أُوْلَٰٓئِكَ لَهُمۡ رِزۡقٞ مَّعۡلُومٞ

እነዚያ ለእነርሱ የታወቀ ሲሳይ አላቸው፡፡

እነዚያ ለእነርሱ የታወቀ ሲሳይ አላቸው፡፡

فَوَٰكِهُ وَهُم مُّكۡرَمُونَ

ፍራፍሬዎች (አሏቸው) እነርሱም የተከበሩ ናቸው፤

ፍራፍሬዎች (አሏቸው) እነርሱም የተከበሩ ናቸው፤

فِي جَنَّٰتِ ٱلنَّعِيمِ

በድሎት ገነቶች ውስጥ፡፡

በድሎት ገነቶች ውስጥ፡፡

عَلَىٰ سُرُرٖ مُّتَقَٰبِلِينَ

ፊት ለፊት የሚታያዩ ሲሆኑ በአልጋዎች ላይ (ይንፈላሰሳሉ)፡፡

ፊት ለፊት የሚታያዩ ሲሆኑ በአልጋዎች ላይ (ይንፈላሰሳሉ)፡፡

يُطَافُ عَلَيۡهِم بِكَأۡسٖ مِّن مَّعِينِۭ

ከሚመነጭ ወይን ጠጅ በያዘ ብርጭቆ በእነርሱ ላይ ይዞርባቸዋል፡፡

ከሚመነጭ ወይን ጠጅ በያዘ ብርጭቆ በእነርሱ ላይ ይዞርባቸዋል፡፡

بَيۡضَآءَ لَذَّةٖ لِّلشَّٰرِبِينَ

ነጭ ለጠጪዎች ጣፋጭ ከኾነች፡፡

ነጭ ለጠጪዎች ጣፋጭ ከኾነች፡፡

لَا فِيهَا غَوۡلٞ وَلَا هُمۡ عَنۡهَا يُنزَفُونَ

በእርሷ ውስጥም ምታት የለባትም፡፡ እነርሱም ከእርሷ የሚሰክሩ አይደሉም፡፡

በእርሷ ውስጥም ምታት የለባትም፡፡ እነርሱም ከእርሷ የሚሰክሩ አይደሉም፡፡

وَعِندَهُمۡ قَٰصِرَٰتُ ٱلطَّرۡفِ عِينٞ

እነርሱም ዘንድ ዓይናቸውን (በባሎቻቸው ላይ) አሳጣሪዎች የኾኑ ዓይናማዎች አልሉ፡፡

እነርሱም ዘንድ ዓይናቸውን (በባሎቻቸው ላይ) አሳጣሪዎች የኾኑ ዓይናማዎች አልሉ፡፡

كَأَنَّهُنَّ بَيۡضٞ مَّكۡنُونٞ

እነርሱ ልክ የተሸፈነ (የሰጎን) ዕንቁላል ይመስላሉ፡፡

እነርሱ ልክ የተሸፈነ (የሰጎን) ዕንቁላል ይመስላሉ፡፡

فَأَقۡبَلَ بَعۡضُهُمۡ عَلَىٰ بَعۡضٖ يَتَسَآءَلُونَ

የሚጠያየቁም ሆነው ከፊላቸው ወደ ከፊሉ ይመጣሉ፡፡

የሚጠያየቁም ሆነው ከፊላቸው ወደ ከፊሉ ይመጣሉ፡፡

قَالَ قَآئِلٞ مِّنۡهُمۡ إِنِّي كَانَ لِي قَرِينٞ

ከእነርሱ የሆነ ተናጋሪ ይላል «እኔ ጓደኛ ነበረኝ፡፡

ከእነርሱ የሆነ ተናጋሪ ይላል «እኔ ጓደኛ ነበረኝ፡፡

يَقُولُ أَءِنَّكَ لَمِنَ ٱلۡمُصَدِّقِينَ

«በእርግጥ አንተ ከሚያምኑት ነህን? የሚል፡፡

«በእርግጥ አንተ ከሚያምኑት ነህን? የሚል፡፡

أَءِذَا مِتۡنَا وَكُنَّا تُرَابٗا وَعِظَٰمًا أَءِنَّا لَمَدِينُونَ

«በሞትንና ዐፈር አጥንቶችም በሆን ጊዜ እኛ በእርግጥ እንመረመራለን?» (የሚል)፡፡

«በሞትንና ዐፈር አጥንቶችም በሆን ጊዜ እኛ በእርግጥ እንመረመራለን?» (የሚል)፡፡

قَالَ هَلۡ أَنتُم مُّطَّلِعُونَ

እናንተ ተመልካቾች ናችሁን? ይላል፡፡

እናንተ ተመልካቾች ናችሁን? ይላል፡፡

فَٱطَّلَعَ فَرَءَاهُ فِي سَوَآءِ ٱلۡجَحِيمِ

ይመለከታልም፤ በገሀነም መካከልም (ጓደኛውን) ያየዋል፡፡

ይመለከታልም፤ በገሀነም መካከልም (ጓደኛውን) ያየዋል፡፡

قَالَ تَٱللَّهِ إِن كِدتَّ لَتُرۡدِينِ

ይላል «በአላህ እምላለሁ፤ በእርግጥ ልታጠፋኝ ቀርበህ ነበር፡፡

ይላል «በአላህ እምላለሁ፤ በእርግጥ ልታጠፋኝ ቀርበህ ነበር፡፡

وَلَوۡلَا نِعۡمَةُ رَبِّي لَكُنتُ مِنَ ٱلۡمُحۡضَرِينَ

«የጌታየም ጸጋ ባልነበረ ኖሮ ወደ እሳት ከሚቀርቡት እሆን ነበር፡፡»

«የጌታየም ጸጋ ባልነበረ ኖሮ ወደ እሳት ከሚቀርቡት እሆን ነበር፡፡»

أَفَمَا نَحۡنُ بِمَيِّتِينَ

(የገነት ሰዎች ይላሉ) «እኛ የምንሞት አይደለንምን?

(የገነት ሰዎች ይላሉ) «እኛ የምንሞት አይደለንምን?

إِلَّا مَوۡتَتَنَا ٱلۡأُولَىٰ وَمَا نَحۡنُ بِمُعَذَّبِينَ

«የመጀመሪያይቱ መሞታችን ብቻ ስትቀር፡፡ እኛም የምንቅቀጣ አይደለንምን?» (ይላሉ)፡፡

«የመጀመሪያይቱ መሞታችን ብቻ ስትቀር፡፡ እኛም የምንቅቀጣ አይደለንምን?» (ይላሉ)፡፡

إِنَّ هَٰذَا لَهُوَ ٱلۡفَوۡزُ ٱلۡعَظِيمُ

ይህ (ለገነት ሰዎች የተወሳው) እርሱ በእርግጥ ታላቅ ዕድል ነው፡፡

ይህ (ለገነት ሰዎች የተወሳው) እርሱ በእርግጥ ታላቅ ዕድል ነው፡፡

لِمِثۡلِ هَٰذَا فَلۡيَعۡمَلِ ٱلۡعَٰمِلُونَ

ለዚህ ብጤ ሠሪዎች ይሥሩ፡፡

ለዚህ ብጤ ሠሪዎች ይሥሩ፡፡

أَذَٰلِكَ خَيۡرٞ نُّزُلًا أَمۡ شَجَرَةُ ٱلزَّقُّومِ

በመስተንግዶነት ይህ ይበልጣልን? ወይስ የዘቁም ዛፍ?

በመስተንግዶነት ይህ ይበልጣልን? ወይስ የዘቁም ዛፍ?

إِنَّا جَعَلۡنَٰهَا فِتۡنَةٗ لِّلظَّٰلِمِينَ

እኛ ለበዳዮች ፈተና አድርገናታል፡፡

እኛ ለበዳዮች ፈተና አድርገናታል፡፡

إِنَّهَا شَجَرَةٞ تَخۡرُجُ فِيٓ أَصۡلِ ٱلۡجَحِيمِ

እርሷ በገሀነም አዘቅት ውስጥ የምትወጣ ዛፍ ናት፡፡

እርሷ በገሀነም አዘቅት ውስጥ የምትወጣ ዛፍ ናት፡፡

طَلۡعُهَا كَأَنَّهُۥ رُءُوسُ ٱلشَّيَٰطِينِ

እንቡጧ ልክ የሰይጣናት ራሶች ይመስላል፡፡

እንቡጧ ልክ የሰይጣናት ራሶች ይመስላል፡፡

فَإِنَّهُمۡ لَأٓكِلُونَ مِنۡهَا فَمَالِـُٔونَ مِنۡهَا ٱلۡبُطُونَ

እነርሱም ከእርሷ በይዎች ናቸው፤ ሆዶችንም ከእርሷ ሞይዎች ናቸው፡፡

እነርሱም ከእርሷ በይዎች ናቸው፤ ሆዶችንም ከእርሷ ሞይዎች ናቸው፡፡

ثُمَّ إِنَّ لَهُمۡ عَلَيۡهَا لَشَوۡبٗا مِّنۡ حَمِيمٖ

ከዚያም ለእነርሱ በእርሷ ላይ ከተኳሳ ውሃ ቅልቅል (መጠጥ) አልላቸው፡፡

ከዚያም ለእነርሱ በእርሷ ላይ ከተኳሳ ውሃ ቅልቅል (መጠጥ) አልላቸው፡፡

ثُمَّ إِنَّ مَرۡجِعَهُمۡ لَإِلَى ٱلۡجَحِيمِ

ከዚያም መመለሻቸው ወደ ተጋጋመች እሳት ነው፡፡

ከዚያም መመለሻቸው ወደ ተጋጋመች እሳት ነው፡፡

إِنَّهُمۡ أَلۡفَوۡاْ ءَابَآءَهُمۡ ضَآلِّينَ

እነሱ አባቶቻቸውን የተሳሳቱ ሆነው አግኝተዋልና፡፡

እነሱ አባቶቻቸውን የተሳሳቱ ሆነው አግኝተዋልና፡፡

فَهُمۡ عَلَىٰٓ ءَاثَٰرِهِمۡ يُهۡرَعُونَ

እነሱም በፈለጎቻቸው ላይ ይገሰግሳሉና፡፡

እነሱም በፈለጎቻቸው ላይ ይገሰግሳሉና፡፡

وَلَقَدۡ ضَلَّ قَبۡلَهُمۡ أَكۡثَرُ ٱلۡأَوَّلِينَ

ከእነርሱ በፊትም የቀድሞዎቹ (ሕዝቦች) አብዛኞቻቸው በእርግጥ ተሳስተዋል፡፡

ከእነርሱ በፊትም የቀድሞዎቹ (ሕዝቦች) አብዛኞቻቸው በእርግጥ ተሳስተዋል፡፡

وَلَقَدۡ أَرۡسَلۡنَا فِيهِم مُّنذِرِينَ

በውስጣቸውም አስፈራሪዎችን በእርግጥ ልከናል፡፡

በውስጣቸውም አስፈራሪዎችን በእርግጥ ልከናል፡፡

فَٱنظُرۡ كَيۡفَ كَانَ عَٰقِبَةُ ٱلۡمُنذَرِينَ

የተስፈራሪዎቹም መጨረሻ እንዴት እንደነበረ ተመልከት፡፡

የተስፈራሪዎቹም መጨረሻ እንዴት እንደነበረ ተመልከት፡፡

إِلَّا عِبَادَ ٱللَّهِ ٱلۡمُخۡلَصِينَ

ምርጥ የሆኑት የአላህ ባሮች ብቻ ሲቀሩ፡፡

ምርጥ የሆኑት የአላህ ባሮች ብቻ ሲቀሩ፡፡

وَلَقَدۡ نَادَىٰنَا نُوحٞ فَلَنِعۡمَ ٱلۡمُجِيبُونَ

ኑሕም በእርግጥ ጠራን፡፡ ጥሪውን ተቀባዮቹም ምንኛ አማርን!

ኑሕም በእርግጥ ጠራን፡፡ ጥሪውን ተቀባዮቹም ምንኛ አማርን!

وَنَجَّيۡنَٰهُ وَأَهۡلَهُۥ مِنَ ٱلۡكَرۡبِ ٱلۡعَظِيمِ

እርሱንም ቤተሰቦቹንም ከከባድ ጭንቅ አዳንን፡፡

እርሱንም ቤተሰቦቹንም ከከባድ ጭንቅ አዳንን፡፡

وَجَعَلۡنَا ذُرِّيَّتَهُۥ هُمُ ٱلۡبَاقِينَ

ዘሮቹንም እነርሱን ብቻ ቀሪዎች አደረግን፤

ዘሮቹንም እነርሱን ብቻ ቀሪዎች አደረግን፤

وَتَرَكۡنَا عَلَيۡهِ فِي ٱلۡأٓخِرِينَ

በርሱም ላይ በኋለኞቹ ሕዝቦች ውስጥ (መልካም ዝናን) ተውን፡፡

በርሱም ላይ በኋለኞቹ ሕዝቦች ውስጥ (መልካም ዝናን) ተውን፡፡

سَلَٰمٌ عَلَىٰ نُوحٖ فِي ٱلۡعَٰلَمِينَ

«በዓለማት ውስጥ ሰላም በኑሕ ላይ ይኹን፡፡»

«በዓለማት ውስጥ ሰላም በኑሕ ላይ ይኹን፡፡»

إِنَّا كَذَٰلِكَ نَجۡزِي ٱلۡمُحۡسِنِينَ

እኛ እንደዚሁ መልካም ሠሪዎችን እንመነዳለን፡፡

እኛ እንደዚሁ መልካም ሠሪዎችን እንመነዳለን፡፡

إِنَّهُۥ مِنۡ عِبَادِنَا ٱلۡمُؤۡمِنِينَ

እርሱ ከምእምናን ባሮቻችን ነውና፡፡

እርሱ ከምእምናን ባሮቻችን ነውና፡፡

ثُمَّ أَغۡرَقۡنَا ٱلۡأٓخَرِينَ

ከዚያም ሌሎቹን አሰጠምን፡፡

ከዚያም ሌሎቹን አሰጠምን፡፡

۞ وَإِنَّ مِن شِيعَتِهِۦ لَإِبۡرَٰهِيمَ

ኢብራሂምም በእርግጥ ከተከታዮቹ ነው፡፡

ኢብራሂምም በእርግጥ ከተከታዮቹ ነው፡፡

إِذۡ جَآءَ رَبَّهُۥ بِقَلۡبٖ سَلِيمٍ

ወደ ጌታው በቅን ልብ በመጣ ጊዜ (የኾነውን አስታውስ)፡፡፡

ወደ ጌታው በቅን ልብ በመጣ ጊዜ (የኾነውን አስታውስ)፡፡፡

إِذۡ قَالَ لِأَبِيهِ وَقَوۡمِهِۦ مَاذَا تَعۡبُدُونَ

«ለአባቱና ለሕዝቦቹ ምንን ትግገዛላችሁ?» ባለ ጊዜ፡፡

«ለአባቱና ለሕዝቦቹ ምንን ትግገዛላችሁ?» ባለ ጊዜ፡፡

أَئِفۡكًا ءَالِهَةٗ دُونَ ٱللَّهِ تُرِيدُونَ

«ለቅጥፈት ብላችሁ ከአላህ ሌላ አማልክትን ትሻላችሁን?

«ለቅጥፈት ብላችሁ ከአላህ ሌላ አማልክትን ትሻላችሁን?

فَمَا ظَنُّكُم بِرَبِّ ٱلۡعَٰلَمِينَ

«በዓለማትም ጌታ ሃሳባችሁ ምንድን ነው?» አለ፡፡

«በዓለማትም ጌታ ሃሳባችሁ ምንድን ነው?» አለ፡፡

فَنَظَرَ نَظۡرَةٗ فِي ٱلنُّجُومِ

በከዋክብትም መመልከትን ተመለከተ፡፡

በከዋክብትም መመልከትን ተመለከተ፡፡

فَقَالَ إِنِّي سَقِيمٞ

«እኔ በሽተኛ ነኝም» አለ፡፡

«እኔ በሽተኛ ነኝም» አለ፡፡

فَتَوَلَّوۡاْ عَنۡهُ مُدۡبِرِينَ

ከእርሱም የሸሹ ሆነው ኼዱ፡፡

ከእርሱም የሸሹ ሆነው ኼዱ፡፡

فَرَاغَ إِلَىٰٓ ءَالِهَتِهِمۡ فَقَالَ أَلَا تَأۡكُلُونَ

ወደ አማልክቶቻቸውም ተዘነበለ፡፡ አለም፡- «አትበሉምን?»

ወደ አማልክቶቻቸውም ተዘነበለ፡፡ አለም፡- «አትበሉምን?»

مَا لَكُمۡ لَا تَنطِقُونَ

«የማትናገሩት ለናንተ ምን አላችሁ?»

«የማትናገሩት ለናንተ ምን አላችሁ?»

فَرَاغَ عَلَيۡهِمۡ ضَرۡبَۢا بِٱلۡيَمِينِ

በኀይል የሚመታቸውም ሆኖ በእነርሱ ላይ በድብቅ ተዘነበለ፡፡

በኀይል የሚመታቸውም ሆኖ በእነርሱ ላይ በድብቅ ተዘነበለ፡፡

فَأَقۡبَلُوٓاْ إِلَيۡهِ يَزِفُّونَ

ወደእርሱም (ሰዎቹ) እየሮጡ መጡ፡፡

ወደእርሱም (ሰዎቹ) እየሮጡ መጡ፡፡

قَالَ أَتَعۡبُدُونَ مَا تَنۡحِتُونَ

አላቸው «የምትጠርቡትን ትግገዛላችሁን?»

አላቸው «የምትጠርቡትን ትግገዛላችሁን?»

وَٱللَّهُ خَلَقَكُمۡ وَمَا تَعۡمَلُونَ

«አላህ እናንተንም የምትሠሩትንም የፈጠረ ሲኾን፡፡»

«አላህ እናንተንም የምትሠሩትንም የፈጠረ ሲኾን፡፡»

قَالُواْ ٱبۡنُواْ لَهُۥ بُنۡيَٰنٗا فَأَلۡقُوهُ فِي ٱلۡجَحِيمِ

«ለእርሱም ግንብን ገንቡ በእሳት ነበልባል ውስጥ ጣሉትም» አሉ፡፡

«ለእርሱም ግንብን ገንቡ በእሳት ነበልባል ውስጥ ጣሉትም» አሉ፡፡

فَأَرَادُواْ بِهِۦ كَيۡدٗا فَجَعَلۡنَٰهُمُ ٱلۡأَسۡفَلِينَ

በእርሱም ተንኮልን አሰቡ፡፡ ዝቅተኞችም አደረግናቸው፡፡

በእርሱም ተንኮልን አሰቡ፡፡ ዝቅተኞችም አደረግናቸው፡፡

وَقَالَ إِنِّي ذَاهِبٌ إِلَىٰ رَبِّي سَيَهۡدِينِ

አለም «እኔ ወደ ጌታዬ ኼያጅ ነኝ፡፡ በእርግጥ ይመራኛልና፡፡»

አለም «እኔ ወደ ጌታዬ ኼያጅ ነኝ፡፡ በእርግጥ ይመራኛልና፡፡»

رَبِّ هَبۡ لِي مِنَ ٱلصَّٰلِحِينَ

ጌታዬ ሆይ! ከመልካሞቹ የሆነን (ልጅ) ስጠኝ፡፡

ጌታዬ ሆይ! ከመልካሞቹ የሆነን (ልጅ) ስጠኝ፡፡

فَبَشَّرۡنَٰهُ بِغُلَٰمٍ حَلِيمٖ

ታጋሽ በሆነ ወጣት ልጅም አበሰርነው፡፡

ታጋሽ በሆነ ወጣት ልጅም አበሰርነው፡፡

فَلَمَّا بَلَغَ مَعَهُ ٱلسَّعۡيَ قَالَ يَٰبُنَيَّ إِنِّيٓ أَرَىٰ فِي ٱلۡمَنَامِ أَنِّيٓ أَذۡبَحُكَ فَٱنظُرۡ مَاذَا تَرَىٰۚ قَالَ يَٰٓأَبَتِ ٱفۡعَلۡ مَا تُؤۡمَرُۖ سَتَجِدُنِيٓ إِن شَآءَ ٱللَّهُ مِنَ ٱلصَّٰبِرِينَ

ከእርሱ ጋርም ለሥራ በደረሰ ጊዜ «ልጄ ሆይ! እኔ በሕልሜ እኔ የማርድህ ሆኜ አያለሁ፡፡ ተመልከትም፤ ምን ታያለህ?» አለው፡፡ «አባቴ ሆይ! የታዘዝከውን ሥራ፡፡ አላህ ቢሻ ከታጋሾቹ ሆኜ ታገኘኛለህ» አለ፡፡

ከእርሱ ጋርም ለሥራ በደረሰ ጊዜ «ልጄ ሆይ! እኔ በሕልሜ እኔ የማርድህ ሆኜ አያለሁ፡፡ ተመልከትም፤ ምን ታያለህ?» አለው፡፡ «አባቴ ሆይ! የታዘዝከውን ሥራ፡፡ አላህ ቢሻ ከታጋሾቹ ሆኜ ታገኘኛለህ» አለ፡፡

فَلَمَّآ أَسۡلَمَا وَتَلَّهُۥ لِلۡجَبِينِ

ሁለቱም ትዕዛዙን በተቀበሉና በግንባሩም ጎን ላይ በጣለው ጊዜ (የሆነው ሆነ)፡፡

ሁለቱም ትዕዛዙን በተቀበሉና በግንባሩም ጎን ላይ በጣለው ጊዜ (የሆነው ሆነ)፡፡

وَنَٰدَيۡنَٰهُ أَن يَٰٓإِبۡرَٰهِيمُ

ጠራነውም፤ (አልነው) «ኢብራሂም ሆይ!

ጠራነውም፤ (አልነው) «ኢብራሂም ሆይ!

قَدۡ صَدَّقۡتَ ٱلرُّءۡيَآۚ إِنَّا كَذَٰلِكَ نَجۡزِي ٱلۡمُحۡسِنِينَ

ራእይቱን በእውነት አረጋገጥክ፡፡» እኛ እንደዚሁ መልካም ሠሪዎችን እንመነዳለን፡፡

ራእይቱን በእውነት አረጋገጥክ፡፡» እኛ እንደዚሁ መልካም ሠሪዎችን እንመነዳለን፡፡

إِنَّ هَٰذَا لَهُوَ ٱلۡبَلَٰٓؤُاْ ٱلۡمُبِينُ

ይህ እርሱ በእውነት ግልጽ ፈተና ነው፡፡

ይህ እርሱ በእውነት ግልጽ ፈተና ነው፡፡

وَفَدَيۡنَٰهُ بِذِبۡحٍ عَظِيمٖ

በታላቅ ዕርድም (መስዋዕት) ተቤዠነው፡፡

በታላቅ ዕርድም (መስዋዕት) ተቤዠነው፡፡

وَتَرَكۡنَا عَلَيۡهِ فِي ٱلۡأٓخِرِينَ

በእርሱም ላይ በኋለኞቹ ሕዝቦች ውስጥ መልካም ዝናን አስቀረንለት፡፡

በእርሱም ላይ በኋለኞቹ ሕዝቦች ውስጥ መልካም ዝናን አስቀረንለት፡፡

سَلَٰمٌ عَلَىٰٓ إِبۡرَٰهِيمَ

ሰላም በኢብራሂም ላይ ይሁን፡፡

ሰላም በኢብራሂም ላይ ይሁን፡፡

كَذَٰلِكَ نَجۡزِي ٱلۡمُحۡسِنِينَ

እንደዚሁ መልካም ሠሪዎችን ሁሉ እንመነዳለን፡፡

እንደዚሁ መልካም ሠሪዎችን ሁሉ እንመነዳለን፡፡

إِنَّهُۥ مِنۡ عِبَادِنَا ٱلۡمُؤۡمِنِينَ

እርሱ በእርግጥ ካመኑት ባሮቻችን ነው፡፡

እርሱ በእርግጥ ካመኑት ባሮቻችን ነው፡፡

وَبَشَّرۡنَٰهُ بِإِسۡحَٰقَ نَبِيّٗا مِّنَ ٱلصَّٰلِحِينَ

በኢስሐቅም አበሰርነው፡፡ ከመልካሞቹ የሆነ ነቢይ ሲሆን፡፡

በኢስሐቅም አበሰርነው፡፡ ከመልካሞቹ የሆነ ነቢይ ሲሆን፡፡

وَبَٰرَكۡنَا عَلَيۡهِ وَعَلَىٰٓ إِسۡحَٰقَۚ وَمِن ذُرِّيَّتِهِمَا مُحۡسِنٞ وَظَالِمٞ لِّنَفۡسِهِۦ مُبِينٞ

በእርሱና በኢስሐቅ ላይም ባረክን፡፡ ከሁለቱም ዘሮች በጎ ሠሪ አልለ፡፡ ለነፍሱ ግልጽ በዳይም አለ፡፡

በእርሱና በኢስሐቅ ላይም ባረክን፡፡ ከሁለቱም ዘሮች በጎ ሠሪ አልለ፡፡ ለነፍሱ ግልጽ በዳይም አለ፡፡

وَلَقَدۡ مَنَنَّا عَلَىٰ مُوسَىٰ وَهَٰرُونَ

በሙሳና በሃሩን ላይም በእርግጥ ለገስን፡፡

በሙሳና በሃሩን ላይም በእርግጥ ለገስን፡፡

وَنَجَّيۡنَٰهُمَا وَقَوۡمَهُمَا مِنَ ٱلۡكَرۡبِ ٱلۡعَظِيمِ

እነርሱንም ሕዝቦቻቸውንም ከታላቅ ጭንቅ አዳንን፡፡

እነርሱንም ሕዝቦቻቸውንም ከታላቅ ጭንቅ አዳንን፡፡

وَنَصَرۡنَٰهُمۡ فَكَانُواْ هُمُ ٱلۡغَٰلِبِينَ

ረዳናቸውም፡፡ እነርሱም አሸናፊዎች ነበሩ፡፡

ረዳናቸውም፡፡ እነርሱም አሸናፊዎች ነበሩ፡፡

وَءَاتَيۡنَٰهُمَا ٱلۡكِتَٰبَ ٱلۡمُسۡتَبِينَ

በጣም የተብራራውንም መጽሐፍ ሰጠናቸው፡፡

በጣም የተብራራውንም መጽሐፍ ሰጠናቸው፡፡

وَهَدَيۡنَٰهُمَا ٱلصِّرَٰطَ ٱلۡمُسۡتَقِيمَ

ቀጥተኛውንም መንገድ መራናቸው፡፡

ቀጥተኛውንም መንገድ መራናቸው፡፡

وَتَرَكۡنَا عَلَيۡهِمَا فِي ٱلۡأٓخِرِينَ

በሁለቱም ላይ በኋለኞቹ ሕዝቦች ውስጥ መልካም ዝናን ተውንላቸው፡፡

በሁለቱም ላይ በኋለኞቹ ሕዝቦች ውስጥ መልካም ዝናን ተውንላቸው፡፡

سَلَٰمٌ عَلَىٰ مُوسَىٰ وَهَٰرُونَ

ሰላም በሙሳና በሃሩን ላይ ይሁን፡፡

ሰላም በሙሳና በሃሩን ላይ ይሁን፡፡

إِنَّا كَذَٰلِكَ نَجۡزِي ٱلۡمُحۡسِنِينَ

እኛ እንደዚሁ በጎ አድራጊዎችን ሁሉ እንመነዳለን፡፡

እኛ እንደዚሁ በጎ አድራጊዎችን ሁሉ እንመነዳለን፡፡

إِنَّهُمَا مِنۡ عِبَادِنَا ٱلۡمُؤۡمِنِينَ

ሁለቱም በእርግጥ ከአመኑት ባሮቻችን ናቸው፡፡

ሁለቱም በእርግጥ ከአመኑት ባሮቻችን ናቸው፡፡

وَإِنَّ إِلۡيَاسَ لَمِنَ ٱلۡمُرۡسَلِينَ

ኢልያስም በእርግጥ ከመልክተኞቹ ነው፡፡

ኢልያስም በእርግጥ ከመልክተኞቹ ነው፡፡

إِذۡ قَالَ لِقَوۡمِهِۦٓ أَلَا تَتَّقُونَ

ለሕዝቦቹ ባለ ጊዜ (አስታውስ)፤ አላህን አትፈሩምን?

ለሕዝቦቹ ባለ ጊዜ (አስታውስ)፤ አላህን አትፈሩምን?

أَتَدۡعُونَ بَعۡلٗا وَتَذَرُونَ أَحۡسَنَ ٱلۡخَٰلِقِينَ

በዕልን ትገዛላችሁን? ከሰዓሊዎቹ ሁሉ ይበልጥ በጣም አሳማሪ የሆነውንም አምላክ ትተዋላችሁን?

በዕልን ትገዛላችሁን? ከሰዓሊዎቹ ሁሉ ይበልጥ በጣም አሳማሪ የሆነውንም አምላክ ትተዋላችሁን?

ٱللَّهَ رَبَّكُمۡ وَرَبَّ ءَابَآئِكُمُ ٱلۡأَوَّلِينَ

አላህን ጌታችሁንና የቀድሞዎቹ አባቶቻችሁን ጌታ (ትተዋላችሁን)?

አላህን ጌታችሁንና የቀድሞዎቹ አባቶቻችሁን ጌታ (ትተዋላችሁን)?

فَكَذَّبُوهُ فَإِنَّهُمۡ لَمُحۡضَرُونَ

አስተባበሉትም፡፡ ስለዚህ እነርሱ (ለቅጣት) የሚጣዱ ናቸው፡፡

አስተባበሉትም፡፡ ስለዚህ እነርሱ (ለቅጣት) የሚጣዱ ናቸው፡፡

إِلَّا عِبَادَ ٱللَّهِ ٱلۡمُخۡلَصِينَ

ንጹሕ የተደረጉት የአላህ ባሮች ብቻ ሲቀሩ፡፡

ንጹሕ የተደረጉት የአላህ ባሮች ብቻ ሲቀሩ፡፡

وَتَرَكۡنَا عَلَيۡهِ فِي ٱلۡأٓخِرِينَ

በእርሱ ላይም በኋለኞቹ ሕዝቦች ውስጥ መልካም ዝናን ተውንለት፡፡

በእርሱ ላይም በኋለኞቹ ሕዝቦች ውስጥ መልካም ዝናን ተውንለት፡፡

سَلَٰمٌ عَلَىٰٓ إِلۡ يَاسِينَ

ሰላም በኢልያሲን ላይ ይሁን፡፡

ሰላም በኢልያሲን ላይ ይሁን፡፡

إِنَّا كَذَٰلِكَ نَجۡزِي ٱلۡمُحۡسِنِينَ

እኛ እንደዚሁ መልካም ሠሪዎችን እንመነዳለን፡፡

እኛ እንደዚሁ መልካም ሠሪዎችን እንመነዳለን፡፡

إِنَّهُۥ مِنۡ عِبَادِنَا ٱلۡمُؤۡمِنِينَ

እርሱ በእርግጥ ከምእመናን ባሮቻችን ነው፡፡

እርሱ በእርግጥ ከምእመናን ባሮቻችን ነው፡፡

وَإِنَّ لُوطٗا لَّمِنَ ٱلۡمُرۡسَلِينَ

ሉጥም በእርግጥ ከመልክተኞቹ ነው፡፡

ሉጥም በእርግጥ ከመልክተኞቹ ነው፡፡

إِذۡ نَجَّيۡنَٰهُ وَأَهۡلَهُۥٓ أَجۡمَعِينَ

እርሱንና ቤተሰቦቹን ሁሉንም በአዳንናቸው ጊዜ (አስታውስ)፡፡

እርሱንና ቤተሰቦቹን ሁሉንም በአዳንናቸው ጊዜ (አስታውስ)፡፡

إِلَّا عَجُوزٗا فِي ٱلۡغَٰبِرِينَ

(በቅጣቱ ውስጥ) ከቀሪዎቹ የሆነችው አሮጊት ብቻ ስትቀር፡፡

(በቅጣቱ ውስጥ) ከቀሪዎቹ የሆነችው አሮጊት ብቻ ስትቀር፡፡

ثُمَّ دَمَّرۡنَا ٱلۡأٓخَرِينَ

ከዚያም ሌሎቹን አጠፋን፡፡

ከዚያም ሌሎቹን አጠፋን፡፡

وَإِنَّكُمۡ لَتَمُرُّونَ عَلَيۡهِم مُّصۡبِحِينَ

እናንተም ያነጋችሁ ስትሆኑ በእነርሱ (መኖሪያዎች) ላይ (በቀን) ታልፋላችሁ፡፡

እናንተም ያነጋችሁ ስትሆኑ በእነርሱ (መኖሪያዎች) ላይ (በቀን) ታልፋላችሁ፡፡

وَبِٱلَّيۡلِۚ أَفَلَا تَعۡقِلُونَ

በሌሊትም (ታልፋላችሁ)፤ ልብም አታደርጉምን?

በሌሊትም (ታልፋላችሁ)፤ ልብም አታደርጉምን?

وَإِنَّ يُونُسَ لَمِنَ ٱلۡمُرۡسَلِينَ

ዩኑስም በእርግጥ ከመልክተኞቹ ነው፡፡

ዩኑስም በእርግጥ ከመልክተኞቹ ነው፡፡

إِذۡ أَبَقَ إِلَى ٱلۡفُلۡكِ ٱلۡمَشۡحُونِ

ወደ ተመላው መርከብ በኮበለለ ጊዜ (አስታውስ)፡፡

ወደ ተመላው መርከብ በኮበለለ ጊዜ (አስታውስ)፡፡

فَسَاهَمَ فَكَانَ مِنَ ٱلۡمُدۡحَضِينَ

ዕጣም ተጣጣለ፡፡ ከተሸነፉትም ሆነ፡፡

ዕጣም ተጣጣለ፡፡ ከተሸነፉትም ሆነ፡፡

فَٱلۡتَقَمَهُ ٱلۡحُوتُ وَهُوَ مُلِيمٞ

እርሱም ተወቃሽ ሲሆን ዐሳው ዋጠው፡፡

እርሱም ተወቃሽ ሲሆን ዐሳው ዋጠው፡፡

فَلَوۡلَآ أَنَّهُۥ كَانَ مِنَ ٱلۡمُسَبِّحِينَ

እርሱ ለጌታው ከአወዳሾቹ ባልሆነም ኖሮ፤

እርሱ ለጌታው ከአወዳሾቹ ባልሆነም ኖሮ፤

لَلَبِثَ فِي بَطۡنِهِۦٓ إِلَىٰ يَوۡمِ يُبۡعَثُونَ

እስከሚቀሰቀሱበት ቀን ድረስ በሆዱ ውስጥ በቆየ ነበር፡፡

እስከሚቀሰቀሱበት ቀን ድረስ በሆዱ ውስጥ በቆየ ነበር፡፡

۞ فَنَبَذۡنَٰهُ بِٱلۡعَرَآءِ وَهُوَ سَقِيمٞ

እርሱ በሽተኛ ሆኖ በቃይ በሌለው (በባሕር) ዳርቻ ላይ ጣልነውም፡፡

እርሱ በሽተኛ ሆኖ በቃይ በሌለው (በባሕር) ዳርቻ ላይ ጣልነውም፡፡

وَأَنۢبَتۡنَا عَلَيۡهِ شَجَرَةٗ مِّن يَقۡطِينٖ

በእርሱም ላይ (በአጠገቡ) ከቅል የሆነችን ዛፍ አበቀልን፡፡

በእርሱም ላይ (በአጠገቡ) ከቅል የሆነችን ዛፍ አበቀልን፡፡

وَأَرۡسَلۡنَٰهُ إِلَىٰ مِاْئَةِ أَلۡفٍ أَوۡ يَزِيدُونَ

ወደ መቶ ሺሕ ሰዎችም (ዳግመኛ) ላክነው፡፡ ከቶውንም ይጨምራሉ።

ወደ መቶ ሺሕ ሰዎችም (ዳግመኛ) ላክነው፡፡ ከቶውንም ይጨምራሉ።

فَـَٔامَنُواْ فَمَتَّعۡنَٰهُمۡ إِلَىٰ حِينٖ

አመኑም፡፡ እስከ ጊዜ ድረስም አጣቀምናቸው፡፡

አመኑም፡፡ እስከ ጊዜ ድረስም አጣቀምናቸው፡፡

فَٱسۡتَفۡتِهِمۡ أَلِرَبِّكَ ٱلۡبَنَاتُ وَلَهُمُ ٱلۡبَنُونَ

ጠይቃቸውም፡፡ «ለጌታህ ሴቶች ልጆች ለእነርሱም ወንዶች ልጆች ይኖራልን?»

ጠይቃቸውም፡፡ «ለጌታህ ሴቶች ልጆች ለእነርሱም ወንዶች ልጆች ይኖራልን?»

أَمۡ خَلَقۡنَا ٱلۡمَلَٰٓئِكَةَ إِنَٰثٗا وَهُمۡ شَٰهِدُونَ

ወይስ እኛ እነርሱ የተጣዱ ሆነው መላእክትን ሴቶች አድርገን ፈጠርን?

ወይስ እኛ እነርሱ የተጣዱ ሆነው መላእክትን ሴቶች አድርገን ፈጠርን?

أَلَآ إِنَّهُم مِّنۡ إِفۡكِهِمۡ لَيَقُولُونَ

ንቁ! እነርሱ ከቅጥፈታቸው (የተነሳ) ይላሉ፡-

ንቁ! እነርሱ ከቅጥፈታቸው (የተነሳ) ይላሉ፡-

وَلَدَ ٱللَّهُ وَإِنَّهُمۡ لَكَٰذِبُونَ

«አላህ (መላእክትን) ወለደ፡፡» እነርሱም በእርግጥ ውሸታሞች ናቸው፡፡

«አላህ (መላእክትን) ወለደ፡፡» እነርሱም በእርግጥ ውሸታሞች ናቸው፡፡

أَصۡطَفَى ٱلۡبَنَاتِ عَلَى ٱلۡبَنِينَ

በወንዶች ልጆች ላይ ይልቅ ሴቶችን ልጆች መረጥን?

በወንዶች ልጆች ላይ ይልቅ ሴቶችን ልጆች መረጥን?

مَا لَكُمۡ كَيۡفَ تَحۡكُمُونَ

ለእናንተ ምን (አስረጅ) አላችሁ? እንዴት ትፈርዳላችሁ!

ለእናንተ ምን (አስረጅ) አላችሁ? እንዴት ትፈርዳላችሁ!

أَفَلَا تَذَكَّرُونَ

አትገነዘቡምን?

አትገነዘቡምን?

أَمۡ لَكُمۡ سُلۡطَٰنٞ مُّبِينٞ

ወይስ ለእናንተ ግልጽ አስረጅ አላችሁን?

ወይስ ለእናንተ ግልጽ አስረጅ አላችሁን?

فَأۡتُواْ بِكِتَٰبِكُمۡ إِن كُنتُمۡ صَٰدِقِينَ

«እውነተኞች እንደ ሆናችሁ መጽሐፋችሁን አምጡ» (በላቸው)፡፡

«እውነተኞች እንደ ሆናችሁ መጽሐፋችሁን አምጡ» (በላቸው)፡፡

وَجَعَلُواْ بَيۡنَهُۥ وَبَيۡنَ ٱلۡجِنَّةِ نَسَبٗاۚ وَلَقَدۡ عَلِمَتِ ٱلۡجِنَّةُ إِنَّهُمۡ لَمُحۡضَرُونَ

በአላህና በአጋንንት መካከልም ዝምድናን አደረጉ፡፡ አጋንንትም እነርሱ (ይህን ባዮች በእሳት) የሚጣዱ መሆናቸውን በእርግጥ ዐውቀዋል፡፡

በአላህና በአጋንንት መካከልም ዝምድናን አደረጉ፡፡ አጋንንትም እነርሱ (ይህን ባዮች በእሳት) የሚጣዱ መሆናቸውን በእርግጥ ዐውቀዋል፡፡

سُبۡحَٰنَ ٱللَّهِ عَمَّا يَصِفُونَ

አላህ ከሚመጥኑት ሁሉ ጠራ፡፡

አላህ ከሚመጥኑት ሁሉ ጠራ፡፡

إِلَّا عِبَادَ ٱللَّهِ ٱلۡمُخۡلَصِينَ

ግን የተመረጡት የአላህ ባሮች (በአላህ ላይ አይዋሹም)፡፡

ግን የተመረጡት የአላህ ባሮች (በአላህ ላይ አይዋሹም)፡፡

فَإِنَّكُمۡ وَمَا تَعۡبُدُونَ

እናንተም የምትገዟቸውም ሁሉ፤

እናንተም የምትገዟቸውም ሁሉ፤

مَآ أَنتُمۡ عَلَيۡهِ بِفَٰتِنِينَ

በእርሱ (በአላህ) ላይ አንድንም አጥማሚዎች አይደላችሁም፡፡

በእርሱ (በአላህ) ላይ አንድንም አጥማሚዎች አይደላችሁም፡፡

إِلَّا مَنۡ هُوَ صَالِ ٱلۡجَحِيمِ

ያንን እርሱ ገሀነምን ገቢ የሆነውን ሰው ቢሆን እንጅ፡፡

ያንን እርሱ ገሀነምን ገቢ የሆነውን ሰው ቢሆን እንጅ፡፡

وَمَا مِنَّآ إِلَّا لَهُۥ مَقَامٞ مَّعۡلُومٞ

(ጂብሪል አለ) ከእኛም አንድም የለም፤ ለእርሱ የታወቀ ደረጃ ያለው ቢሆን እንጅ፡፡

(ጂብሪል አለ) ከእኛም አንድም የለም፤ ለእርሱ የታወቀ ደረጃ ያለው ቢሆን እንጅ፡፡

وَإِنَّا لَنَحۡنُ ٱلصَّآفُّونَ

እኛም (ጌታን ለመግገዛት) ተሰላፊዎቹ እኛ ነን፡፡

እኛም (ጌታን ለመግገዛት) ተሰላፊዎቹ እኛ ነን፡፡

وَإِنَّا لَنَحۡنُ ٱلۡمُسَبِّحُونَ

እኛም (አላህን) አጥሪዎቹ እኛ ነን፡፡

እኛም (አላህን) አጥሪዎቹ እኛ ነን፡፡

وَإِن كَانُواْ لَيَقُولُونَ

እነርሱም (ከሓዲዎቹ) በእርግጥ ይሉ ነበሩ፡-

እነርሱም (ከሓዲዎቹ) በእርግጥ ይሉ ነበሩ፡-

لَوۡ أَنَّ عِندَنَا ذِكۡرٗا مِّنَ ٱلۡأَوَّلِينَ

«ከቀድሞዎቹ (መጻሕፍት) ገሳጭ መጽሐፍ እኛ ዘንድ በነበረን ኖሮ፤

«ከቀድሞዎቹ (መጻሕፍት) ገሳጭ መጽሐፍ እኛ ዘንድ በነበረን ኖሮ፤

لَكُنَّا عِبَادَ ٱللَّهِ ٱلۡمُخۡلَصِينَ

«የአላህ ምርጦች ባሮች በሆን ነበር፡፡»

«የአላህ ምርጦች ባሮች በሆን ነበር፡፡»

فَكَفَرُواْ بِهِۦۖ فَسَوۡفَ يَعۡلَمُونَ

ግን (ቁርኣኑ በመጣላቸው ጊዜ) በእርሱ ካዱ፡፡ ወደፊትም በእርግጥ ያውቃሉ፡፡

ግን (ቁርኣኑ በመጣላቸው ጊዜ) በእርሱ ካዱ፡፡ ወደፊትም በእርግጥ ያውቃሉ፡፡

وَلَقَدۡ سَبَقَتۡ كَلِمَتُنَا لِعِبَادِنَا ٱلۡمُرۡسَلِينَ

(የእርዳታ) ቃላችንም መልክተኞች ለሆኑት ባሮቻችን በእውነት አልፋለች፡፡

(የእርዳታ) ቃላችንም መልክተኞች ለሆኑት ባሮቻችን በእውነት አልፋለች፡፡

إِنَّهُمۡ لَهُمُ ٱلۡمَنصُورُونَ

እነርሱ ተረጂዎቹ እነርሱ ናቸው፡፡

እነርሱ ተረጂዎቹ እነርሱ ናቸው፡፡

وَإِنَّ جُندَنَا لَهُمُ ٱلۡغَٰلِبُونَ

ሰራዊቶቻችንም በእርግጥ አሸናፊዎቹ እነርሱ ናቸው፡፡

ሰራዊቶቻችንም በእርግጥ አሸናፊዎቹ እነርሱ ናቸው፡፡

فَتَوَلَّ عَنۡهُمۡ حَتَّىٰ حِينٖ

ከእነርሱም (ከመካ ከሓዲዎች) እስከ ጥቂት ጊዜ ድረስ ዙር (ተዋቸው)፡፡

ከእነርሱም (ከመካ ከሓዲዎች) እስከ ጥቂት ጊዜ ድረስ ዙር (ተዋቸው)፡፡

وَأَبۡصِرۡهُمۡ فَسَوۡفَ يُبۡصِرُونَ

እያቸውም ወደፊትም (የሚደርስባቸውን) ያያሉ፡፡

እያቸውም ወደፊትም (የሚደርስባቸውን) ያያሉ፡፡

أَفَبِعَذَابِنَا يَسۡتَعۡجِلُونَ

በቅጣታችንም ያቻኩላሉን?

በቅጣታችንም ያቻኩላሉን?

فَإِذَا نَزَلَ بِسَاحَتِهِمۡ فَسَآءَ صَبَاحُ ٱلۡمُنذَرِينَ

በቀያቸውም በወረደ ጊዜ የተስፈራሪዎቹ ንጋት ከፋ!

በቀያቸውም በወረደ ጊዜ የተስፈራሪዎቹ ንጋት ከፋ!

وَتَوَلَّ عَنۡهُمۡ حَتَّىٰ حِينٖ

እነርሱንም እስከ (ጥቂት) ጊዜ ድረስ ተዋቸው፡፡

እነርሱንም እስከ (ጥቂት) ጊዜ ድረስ ተዋቸው፡፡

وَأَبۡصِرۡ فَسَوۡفَ يُبۡصِرُونَ

ተመልከትም በእርግጥም ያያሉ፡፡

ተመልከትም በእርግጥም ያያሉ፡፡

سُبۡحَٰنَ رَبِّكَ رَبِّ ٱلۡعِزَّةِ عَمَّا يَصِفُونَ

የማሸነፍ ጌታ የሆነው ጌታህ ከሚሉት ሁሉ ጠራ፡፡

የማሸነፍ ጌታ የሆነው ጌታህ ከሚሉት ሁሉ ጠራ፡፡

وَسَلَٰمٌ عَلَى ٱلۡمُرۡسَلِينَ

በመልክተኞቹም ላይ ሰላም ይኹኑ፤

በመልክተኞቹም ላይ ሰላም ይኹኑ፤

وَٱلۡحَمۡدُ لِلَّهِ رَبِّ ٱلۡعَٰلَمِينَ

ምስጋናም ለዓለማት ጌታ ለአላህ ይሁን፡፡

ምስጋናም ለዓለማት ጌታ ለአላህ ይሁን፡፡
Footer Include