Header Include

الترجمة الأمهرية

ترجمة معاني القرآن الكريم إلى اللغة الامهرية، ترجمها الشيخ محمد صادق ومحمد الثاني حبيب. تم تصويبها بإشراف مركز رواد الترجمة، ويتاح الإطلاع على الترجمة الأصلية لغرض إبداء الرأي والتقييم والتطوير المستمر.

QR Code https://quran.islamcontent.com/ar/amharic_sadiq

لَآ أُقۡسِمُ بِيَوۡمِ ٱلۡقِيَٰمَةِ

(ነገሩ ከሓዲዎች እንደሚሉት) አይደለም፡፡ በትንሣኤ ቀን እምላለሁ፡፡

(ነገሩ ከሓዲዎች እንደሚሉት) አይደለም፡፡ በትንሣኤ ቀን እምላለሁ፡፡

وَلَآ أُقۡسِمُ بِٱلنَّفۡسِ ٱللَّوَّامَةِ

(ራሷን) ወቃሽ በኾነች ነፍስም እምላለሁ፡፡ (በእርግጥ ትቀሰቀሳላችሁ)፡፡

(ራሷን) ወቃሽ በኾነች ነፍስም እምላለሁ፡፡ (በእርግጥ ትቀሰቀሳላችሁ)፡፡

أَيَحۡسَبُ ٱلۡإِنسَٰنُ أَلَّن نَّجۡمَعَ عِظَامَهُۥ

ሰው አጥንቶቹን አለመሰብሰባችንን ያስባልን?

ሰው አጥንቶቹን አለመሰብሰባችንን ያስባልን?

بَلَىٰ قَٰدِرِينَ عَلَىٰٓ أَن نُّسَوِّيَ بَنَانَهُۥ

አይደለም ጣቶቹን (ፊት እንደ ነበሩ) በማስተካከል ላይ ቻዮች ስንኾን (እንሰበስባቸዋለን)፡፡

አይደለም ጣቶቹን (ፊት እንደ ነበሩ) በማስተካከል ላይ ቻዮች ስንኾን (እንሰበስባቸዋለን)፡፡

بَلۡ يُرِيدُ ٱلۡإِنسَٰنُ لِيَفۡجُرَ أَمَامَهُۥ

ይልቁንም ሰው በፊቱ ባለው ነገር (በትንሣኤ) ሊያስተባብል ይፈልጋል፡፡

ይልቁንም ሰው በፊቱ ባለው ነገር (በትንሣኤ) ሊያስተባብል ይፈልጋል፡፡

يَسۡـَٔلُ أَيَّانَ يَوۡمُ ٱلۡقِيَٰمَةِ

«የትንሣኤው ቀን መቼ ነው?» ሲል ይጠይቃል፡፡

«የትንሣኤው ቀን መቼ ነው?» ሲል ይጠይቃል፡፡

فَإِذَا بَرِقَ ٱلۡبَصَرُ

ዓይንም በዋለለ ጊዜ፡፡

ዓይንም በዋለለ ጊዜ፡፡

وَخَسَفَ ٱلۡقَمَرُ

ጨረቃም በጨለመ ጊዜ፡፡

ጨረቃም በጨለመ ጊዜ፡፡

وَجُمِعَ ٱلشَّمۡسُ وَٱلۡقَمَرُ

ፀሐይና ጨረቃም በተሰበሰቡ ጊዜ፡፡

ፀሐይና ጨረቃም በተሰበሰቡ ጊዜ፡፡

يَقُولُ ٱلۡإِنسَٰنُ يَوۡمَئِذٍ أَيۡنَ ٱلۡمَفَرُّ

«ሰው በዚያ ቀን መሸሻው የት ነው?» ይላል፡፡

«ሰው በዚያ ቀን መሸሻው የት ነው?» ይላል፡፡

كَلَّا لَا وَزَرَ

ይከልከል፤ ምንም መጠጊያ የለም፡፡

ይከልከል፤ ምንም መጠጊያ የለም፡፡

إِلَىٰ رَبِّكَ يَوۡمَئِذٍ ٱلۡمُسۡتَقَرُّ

በዚያ ቀን መርጊያው ወደ ጌታህ ብቻ ነው፡፡

በዚያ ቀን መርጊያው ወደ ጌታህ ብቻ ነው፡፡

يُنَبَّؤُاْ ٱلۡإِنسَٰنُ يَوۡمَئِذِۭ بِمَا قَدَّمَ وَأَخَّرَ

ሰው በዚያ ቀን ባስቀደመውና ባስቆየው ሁሉ ይነገራል፡፡

ሰው በዚያ ቀን ባስቀደመውና ባስቆየው ሁሉ ይነገራል፡፡

بَلِ ٱلۡإِنسَٰنُ عَلَىٰ نَفۡسِهِۦ بَصِيرَةٞ

በእርግጥም ሰው በነፍሱ ላይ አስረጅ ነው፡፡ (አካሎቹ ይመሰክሩበታል)፡፡

በእርግጥም ሰው በነፍሱ ላይ አስረጅ ነው፡፡ (አካሎቹ ይመሰክሩበታል)፡፡

وَلَوۡ أَلۡقَىٰ مَعَاذِيرَهُۥ

ምክንያቶቹን ሁሉ ቢያመጣም እንኳ (አይሰማም)፡፡

ምክንያቶቹን ሁሉ ቢያመጣም እንኳ (አይሰማም)፡፡

لَا تُحَرِّكۡ بِهِۦ لِسَانَكَ لِتَعۡجَلَ بِهِۦٓ

በእርሱ (በቁርኣን ንባብ) ልትቸኩል ምላስህን በእርሱ አታላውስ፡፡

በእርሱ (በቁርኣን ንባብ) ልትቸኩል ምላስህን በእርሱ አታላውስ፡፡

إِنَّ عَلَيۡنَا جَمۡعَهُۥ وَقُرۡءَانَهُۥ

(በልብህ ውስጥ) መሰብሰቡና ማንበቡ በእኛ ላይ ነውና፡፡

(በልብህ ውስጥ) መሰብሰቡና ማንበቡ በእኛ ላይ ነውና፡፡

فَإِذَا قَرَأۡنَٰهُ فَٱتَّبِعۡ قُرۡءَانَهُۥ

ባነበብነውም ጊዜ (ካለቀ በኋላ) ንባቡን ተከተል፡፡

ባነበብነውም ጊዜ (ካለቀ በኋላ) ንባቡን ተከተል፡፡

ثُمَّ إِنَّ عَلَيۡنَا بَيَانَهُۥ

ከዚያም ማብራራቱ በእኛ ላይ ነው፡፡

ከዚያም ማብራራቱ በእኛ ላይ ነው፡፡

كَلَّا بَلۡ تُحِبُّونَ ٱلۡعَاجِلَةَ

(ከመጣደፍ) ተከልከል፡፡ ይልቁንም (ሰዎች) ፈጣኒቱን (ዓለም) ትወዳላችሁ፡፡

(ከመጣደፍ) ተከልከል፡፡ ይልቁንም (ሰዎች) ፈጣኒቱን (ዓለም) ትወዳላችሁ፡፡

وَتَذَرُونَ ٱلۡأٓخِرَةَ

መጨረሻይቱንም (ዓለም) ትተዋላችሁ፡፡ (አትዘጋጁላትም)፡፡

መጨረሻይቱንም (ዓለም) ትተዋላችሁ፡፡ (አትዘጋጁላትም)፡፡

وُجُوهٞ يَوۡمَئِذٖ نَّاضِرَةٌ

ፊቶች በዚያ ቀን አብሪዎች ናቸው፡፡

ፊቶች በዚያ ቀን አብሪዎች ናቸው፡፡

إِلَىٰ رَبِّهَا نَاظِرَةٞ

ወደ ጌታቸው ተመልካቾች ናቸው፡፡

ወደ ጌታቸው ተመልካቾች ናቸው፡፡

وَوُجُوهٞ يَوۡمَئِذِۭ بَاسِرَةٞ

ፊቶችም በዚያ ቀን ጨፍጋጊዎች ናቸው፡፡

ፊቶችም በዚያ ቀን ጨፍጋጊዎች ናቸው፡፡

تَظُنُّ أَن يُفۡعَلَ بِهَا فَاقِرَةٞ

በርሳቸውም ዐደጋ እንደሚሠራባቸው ያረጋግጣሉ፡፡

በርሳቸውም ዐደጋ እንደሚሠራባቸው ያረጋግጣሉ፡፡

كَلَّآ إِذَا بَلَغَتِ ٱلتَّرَاقِيَ

ንቁ (ነፍስ) ብሪዎችን በደረሰች ጊዜ፤

ንቁ (ነፍስ) ብሪዎችን በደረሰች ጊዜ፤

وَقِيلَ مَنۡۜ رَاقٖ

«አሻሪው ማነው?» በተባለም ጊዜ፡፡

«አሻሪው ማነው?» በተባለም ጊዜ፡፡

وَظَنَّ أَنَّهُ ٱلۡفِرَاقُ

(ሕመምተኛው) እርሱ (የሰፈረበት ነገር ከዚህ ዓለም) መልለየት መኾኑን ባረጋገጠም ጊዜ፡፡

(ሕመምተኛው) እርሱ (የሰፈረበት ነገር ከዚህ ዓለም) መልለየት መኾኑን ባረጋገጠም ጊዜ፡፡

وَٱلۡتَفَّتِ ٱلسَّاقُ بِٱلسَّاقِ

ባትም በባት በተጣበቀች ጊዜ፡፡

ባትም በባት በተጣበቀች ጊዜ፡፡

إِلَىٰ رَبِّكَ يَوۡمَئِذٍ ٱلۡمَسَاقُ

በዚያ ቀን መነዳቱ ወደ ጌታህ ነው፡፡

በዚያ ቀን መነዳቱ ወደ ጌታህ ነው፡፡

فَلَا صَدَّقَ وَلَا صَلَّىٰ

አላመነምም አልሰገደምም፡፡

አላመነምም አልሰገደምም፡፡

وَلَٰكِن كَذَّبَ وَتَوَلَّىٰ

ግን አስተባበለ፤ (ከእምነት) ዞረም፡፡

ግን አስተባበለ፤ (ከእምነት) ዞረም፡፡

ثُمَّ ذَهَبَ إِلَىٰٓ أَهۡلِهِۦ يَتَمَطَّىٰٓ

ከዚያም እየተንጎባለለ ወደ ቤተሰቡ ኼደ፡፡

ከዚያም እየተንጎባለለ ወደ ቤተሰቡ ኼደ፡፡

أَوۡلَىٰ لَكَ فَأَوۡلَىٰ

የምትጠላውን ነገር (አላህ) ያስከትልህ፡፡ ለአንተ ተገቢህም ነው፡፡

የምትጠላውን ነገር (አላህ) ያስከትልህ፡፡ ለአንተ ተገቢህም ነው፡፡

ثُمَّ أَوۡلَىٰ لَكَ فَأَوۡلَىٰٓ

ከዚያም ጥፋት ይጠጋህ ለአንተ የተገባህም ነው፡፡

ከዚያም ጥፋት ይጠጋህ ለአንተ የተገባህም ነው፡፡

أَيَحۡسَبُ ٱلۡإِنسَٰنُ أَن يُتۡرَكَ سُدًى

ሰው ስድ ኾኖ መትተውን ይጠረጥራልን?

ሰው ስድ ኾኖ መትተውን ይጠረጥራልን?

أَلَمۡ يَكُ نُطۡفَةٗ مِّن مَّنِيّٖ يُمۡنَىٰ

የሚፈሰስ ከኾነ የፍትወት ጠብታ አልነበረምን?

የሚፈሰስ ከኾነ የፍትወት ጠብታ አልነበረምን?

ثُمَّ كَانَ عَلَقَةٗ فَخَلَقَ فَسَوَّىٰ

ከዚያም የረጋ ደም ኾነ (አላህ ሰው አድርጎ) ፈጠረውም፡፡ አስተካከለውም፡፡

ከዚያም የረጋ ደም ኾነ (አላህ ሰው አድርጎ) ፈጠረውም፡፡ አስተካከለውም፡፡

فَجَعَلَ مِنۡهُ ٱلزَّوۡجَيۡنِ ٱلذَّكَرَ وَٱلۡأُنثَىٰٓ

ከእርሱም ሁለት ዓይነቶችን ወንድና ሴትን አደረገ፡፡

ከእርሱም ሁለት ዓይነቶችን ወንድና ሴትን አደረገ፡፡

أَلَيۡسَ ذَٰلِكَ بِقَٰدِرٍ عَلَىٰٓ أَن يُحۡـِۧيَ ٱلۡمَوۡتَىٰ

ይህ (ጌታ) ሙታንን ሕያው በማድረግ ላይ ቻይ አይደለምን?

ይህ (ጌታ) ሙታንን ሕያው በማድረግ ላይ ቻይ አይደለምን?
Footer Include