Header Include

الترجمة الأمهرية

ترجمة معاني القرآن الكريم إلى اللغة الامهرية، ترجمها الشيخ محمد صادق ومحمد الثاني حبيب. تم تصويبها بإشراف مركز رواد الترجمة، ويتاح الإطلاع على الترجمة الأصلية لغرض إبداء الرأي والتقييم والتطوير المستمر.

QR Code https://quran.islamcontent.com/ar/amharic_sadiq

عَبَسَ وَتَوَلَّىٰٓ

ፊቱን አጨፈገገ፤ ዞረም፡፡

ፊቱን አጨፈገገ፤ ዞረም፡፡

أَن جَآءَهُ ٱلۡأَعۡمَىٰ

ዕውሩ ስለ መጣው፡፡

ዕውሩ ስለ መጣው፡፡

وَمَا يُدۡرِيكَ لَعَلَّهُۥ يَزَّكَّىٰٓ

ምን ያሳውቅሃል? (ከኀጢአቶቹ) ሊጥራራ ይከጀላል፡፡

ምን ያሳውቅሃል? (ከኀጢአቶቹ) ሊጥራራ ይከጀላል፡፡

أَوۡ يَذَّكَّرُ فَتَنفَعَهُ ٱلذِّكۡرَىٰٓ

ወይም ሊገሠጽ ግሠጼይቱም ልትጠቅመው (ይከጀላል)፡፡

ወይም ሊገሠጽ ግሠጼይቱም ልትጠቅመው (ይከጀላል)፡፡

أَمَّا مَنِ ٱسۡتَغۡنَىٰ

የተብቃቃው ሰውማ፤

የተብቃቃው ሰውማ፤

فَأَنتَ لَهُۥ تَصَدَّىٰ

አንተ ለእርሱ (ለእምነቱ በመጓጓት) በፈገግታ ትቀበለዋለህ፡፡

አንተ ለእርሱ (ለእምነቱ በመጓጓት) በፈገግታ ትቀበለዋለህ፡፡

وَمَا عَلَيۡكَ أَلَّا يَزَّكَّىٰ

ባይጥራራ (ባያምን) ባንተ ላይ ምንም የሌለብህ ስትኾን፡፡

ባይጥራራ (ባያምን) ባንተ ላይ ምንም የሌለብህ ስትኾን፡፡

وَأَمَّا مَن جَآءَكَ يَسۡعَىٰ

እየገሰገሰ የመጣህ ሰውማ፤

እየገሰገሰ የመጣህ ሰውማ፤

وَهُوَ يَخۡشَىٰ

እርሱ (አላህን) የሚፈራ ሲኾን፤

እርሱ (አላህን) የሚፈራ ሲኾን፤

فَأَنتَ عَنۡهُ تَلَهَّىٰ

አንተ ከእርሱ ትዝዘናጋለህ፡፡

አንተ ከእርሱ ትዝዘናጋለህ፡፡

كَلَّآ إِنَّهَا تَذۡكِرَةٞ

ተከልከል፡፡ እርሷ ማስገንዘቢያ ናት፡፡

ተከልከል፡፡ እርሷ ማስገንዘቢያ ናት፡፡

فَمَن شَآءَ ذَكَرَهُۥ

የሻም ሰው (ቁርኣኑን) ያስታውሰዋል፡፡

የሻም ሰው (ቁርኣኑን) ያስታውሰዋል፡፡

فِي صُحُفٖ مُّكَرَّمَةٖ

በተከበሩ ጽሑፎች ውስጥ ነው፡፡

በተከበሩ ጽሑፎች ውስጥ ነው፡፡

مَّرۡفُوعَةٖ مُّطَهَّرَةِۭ

ከፍ በተደረገች ንጹሕ በተደረገች (ጽሑፍ ውስጥ ነው)፡፡

ከፍ በተደረገች ንጹሕ በተደረገች (ጽሑፍ ውስጥ ነው)፡፡

بِأَيۡدِي سَفَرَةٖ

በጸሐፊዎቹ (መላእክት) እጆች (ንጹሕ የተደረገች)፡፡

በጸሐፊዎቹ (መላእክት) እጆች (ንጹሕ የተደረገች)፡፡

كِرَامِۭ بَرَرَةٖ

የተከበሩና ታዛዦች በኾኑት (ጸሐፊዎች እጆች)፡፡

የተከበሩና ታዛዦች በኾኑት (ጸሐፊዎች እጆች)፡፡

قُتِلَ ٱلۡإِنسَٰنُ مَآ أَكۡفَرَهُۥ

ሰው ተረገመ፤ ምን ከሓዲ አደረገው?

ሰው ተረገመ፤ ምን ከሓዲ አደረገው?

مِنۡ أَيِّ شَيۡءٍ خَلَقَهُۥ

(ጌታው) በምን ነገር ፈጠረው? (አያስብምን?)

(ጌታው) በምን ነገር ፈጠረው? (አያስብምን?)

مِن نُّطۡفَةٍ خَلَقَهُۥ فَقَدَّرَهُۥ

ከፍትወት ጠብታ ፈጠረው፤ መጠነውም፡፡

ከፍትወት ጠብታ ፈጠረው፤ መጠነውም፡፡

ثُمَّ ٱلسَّبِيلَ يَسَّرَهُۥ

ከዚያም (መውጫ) መንገዱን አገራው፡፡

ከዚያም (መውጫ) መንገዱን አገራው፡፡

ثُمَّ أَمَاتَهُۥ فَأَقۡبَرَهُۥ

ከዚያም ገደለው፤ እንዲቀበርም አደረገው፡፡

ከዚያም ገደለው፤ እንዲቀበርም አደረገው፡፡

ثُمَّ إِذَا شَآءَ أَنشَرَهُۥ

ከዚያም (ማንሳቱን) በሻ ጊዜ ያስነሳዋል፡፡

ከዚያም (ማንሳቱን) በሻ ጊዜ ያስነሳዋል፡፡

كَلَّا لَمَّا يَقۡضِ مَآ أَمَرَهُۥ

በእውነት ያንን (ጌታው) ያዘዘውን ገና አልፈጸመም፡፡

በእውነት ያንን (ጌታው) ያዘዘውን ገና አልፈጸመም፡፡

فَلۡيَنظُرِ ٱلۡإِنسَٰنُ إِلَىٰ طَعَامِهِۦٓ

ሰውም ወደ ምግቡ ይመልከት፡፡

ሰውም ወደ ምግቡ ይመልከት፡፡

أَنَّا صَبَبۡنَا ٱلۡمَآءَ صَبّٗا

እኛ ውሃን ማንቧቧትን ያንቧቧን መኾናችንን፡፡

እኛ ውሃን ማንቧቧትን ያንቧቧን መኾናችንን፡፡

ثُمَّ شَقَقۡنَا ٱلۡأَرۡضَ شَقّٗا

ከዚያም ምድርን (በደካማ ቡቃያ) መሰንጠቅን የሰነጠቅን፤

ከዚያም ምድርን (በደካማ ቡቃያ) መሰንጠቅን የሰነጠቅን፤

فَأَنۢبَتۡنَا فِيهَا حَبّٗا

በውስጧም እኽልን ያበቀልን፤

በውስጧም እኽልን ያበቀልን፤

وَعِنَبٗا وَقَضۡبٗا

ወይንንም፤ እርጥብ (ያበቀልን)፤

ወይንንም፤ እርጥብ (ያበቀልን)፤

وَزَيۡتُونٗا وَنَخۡلٗا

የዘይት ወይራንም ዘንባባንም፤

የዘይት ወይራንም ዘንባባንም፤

وَحَدَآئِقَ غُلۡبٗا

ጭፍቆች አትክልቶችንም፤

ጭፍቆች አትክልቶችንም፤

وَفَٰكِهَةٗ وَأَبّٗا

ፍራፍሬንም ገለባንም፤ (ያበቀልን መኾናችንን ይመልከት)፡፡

ፍራፍሬንም ገለባንም፤ (ያበቀልን መኾናችንን ይመልከት)፡፡

مَّتَٰعٗا لَّكُمۡ وَلِأَنۡعَٰمِكُمۡ

ለእናንተም ለእንስሶቻችሁም መጠቀሚያ ይኾን ዘንድ (ይህን ሠራን)፡፡

ለእናንተም ለእንስሶቻችሁም መጠቀሚያ ይኾን ዘንድ (ይህን ሠራን)፡፡

فَإِذَا جَآءَتِ ٱلصَّآخَّةُ

አደንቋሪይቱም (መከራ) በመጣች ጊዜ፤

አደንቋሪይቱም (መከራ) በመጣች ጊዜ፤

يَوۡمَ يَفِرُّ ٱلۡمَرۡءُ مِنۡ أَخِيهِ

ሰው ከወንድሙ በሚሸሽበት ቀን፤

ሰው ከወንድሙ በሚሸሽበት ቀን፤

وَأُمِّهِۦ وَأَبِيهِ

ከናቱም ካባቱም፤

ከናቱም ካባቱም፤

وَصَٰحِبَتِهِۦ وَبَنِيهِ

ከሚስቱም ከልጁም፤

ከሚስቱም ከልጁም፤

لِكُلِّ ٱمۡرِيٕٖ مِّنۡهُمۡ يَوۡمَئِذٖ شَأۡنٞ يُغۡنِيهِ

ከእነርሱ ለየሰው ሁሉ በዚያ ቀን (ከሌላው) የሚያብቃቃው ኹነታ አልለው፡፡

ከእነርሱ ለየሰው ሁሉ በዚያ ቀን (ከሌላው) የሚያብቃቃው ኹነታ አልለው፡፡

وُجُوهٞ يَوۡمَئِذٖ مُّسۡفِرَةٞ

ፊቶች በዚያ ቀን አብሪዎች ናቸው፤

ፊቶች በዚያ ቀን አብሪዎች ናቸው፤

ضَاحِكَةٞ مُّسۡتَبۡشِرَةٞ

ሳቂዎችም ተደሳቾችም ናቸው፡፡

ሳቂዎችም ተደሳቾችም ናቸው፡፡

وَوُجُوهٞ يَوۡمَئِذٍ عَلَيۡهَا غَبَرَةٞ

ፊቶችም በዚያ ቀን በላያቸው ላይ ትቢያ አልለባቸው፤

ፊቶችም በዚያ ቀን በላያቸው ላይ ትቢያ አልለባቸው፤

تَرۡهَقُهَا قَتَرَةٌ

ጥቁረት ትሸፍናቸዋለች፤

ጥቁረት ትሸፍናቸዋለች፤

أُوْلَٰٓئِكَ هُمُ ٱلۡكَفَرَةُ ٱلۡفَجَرَةُ

እነዚያ እነሱ ከሓዲዎቹ አመጸኞቹ ናቸው፡፡

እነዚያ እነሱ ከሓዲዎቹ አመጸኞቹ ናቸው፡፡
Footer Include