Amharische Übersetzung - Muhammad Sadiq
Übersetzung der Bedeutungen des Edlen Korans
Übersetzt von Sheikh Muhammad Sadiq und Muhammad al-Thani Habib. Die Übersetzung wurde unter der Aufsicht des Rowwad-Übersetzungszentrums entwickelt. Es ist möglich sich die Originalübersetzung zum Zwecke der Meinungsäußerung, Bewertung und kontinuierlichen Weiterentwicklung anzuschauen.
ٱلۡقَارِعَةُ
ቆርቋሪይቱ (ጩኸት)፤
مَا ٱلۡقَارِعَةُ
ምን አስደናቂ ቆርቋሪ ናት!
وَمَآ أَدۡرَىٰكَ مَا ٱلۡقَارِعَةُ
ቆርቋሪይቱም ምን እንደኾነች ምን አሳወቀህ?
يَوۡمَ يَكُونُ ٱلنَّاسُ كَٱلۡفَرَاشِ ٱلۡمَبۡثُوثِ
ሰዎች እንደ ተበታተነ ቢራቢሮ (ወይም ኩብኩባ) በሚኾኑበት ቀን፤
وَتَكُونُ ٱلۡجِبَالُ كَٱلۡعِهۡنِ ٱلۡمَنفُوشِ
ጋራዎችም እንደ ተነደፈ ሱፍ በሚኾኑበት (ቀን ልቦችን በድንጋጤ ትቆረቁራለች፡፡)
فَأَمَّا مَن ثَقُلَتۡ مَوَٰزِينُهُۥ
ሚዛኖቹ የከበዱለት ሰውማ፤
فَهُوَ فِي عِيشَةٖ رَّاضِيَةٖ
እርሱ በምትወደድ ኑሮ ውስጥ ይኾናል፡፡
وَأَمَّا مَنۡ خَفَّتۡ مَوَٰزِينُهُۥ
ሚዛኖቹም የቀለሉበት ሰውማ፤
فَأُمُّهُۥ هَاوِيَةٞ
መኖሪያው ሃዊያህ ናት
وَمَآ أَدۡرَىٰكَ مَا هِيَهۡ
እርሷም ምን እንደ ኾነች ምን አሳወቀህ?
نَارٌ حَامِيَةُۢ
(እርሷ) በጣም ተኳሳ እሳት ናት፡፡
share_via