Amharische Übersetzung - Muhammad Sadiq
Übersetzung der Bedeutungen des Edlen Korans
Übersetzt von Sheikh Muhammad Sadiq und Muhammad al-Thani Habib. Die Übersetzung wurde unter der Aufsicht des Rowwad-Übersetzungszentrums entwickelt. Es ist möglich sich die Originalübersetzung zum Zwecke der Meinungsäußerung, Bewertung und kontinuierlichen Weiterentwicklung anzuschauen.
ٱقۡرَأۡ بِٱسۡمِ رَبِّكَ ٱلَّذِي خَلَقَ
አንብብ በዚያ (ሁሉን) በፈጠረው ጌታህ ስም፡፡[1]
خَلَقَ ٱلۡإِنسَٰنَ مِنۡ عَلَقٍ
ሰውን ከረጋ ደም በፈጠረው (ጌታህ ስም)፡፡
ٱقۡرَأۡ وَرَبُّكَ ٱلۡأَكۡرَمُ
አንብብ፤ ጌታህ በጣም ቸር ሲኾን፤
ٱلَّذِي عَلَّمَ بِٱلۡقَلَمِ
ያ በብርዕ ያስተማረ፡፡
عَلَّمَ ٱلۡإِنسَٰنَ مَا لَمۡ يَعۡلَمۡ
ሰውን ያላወቀውን ሁሉ ያሳወቀ ሲኾን፡፡
كَلَّآ إِنَّ ٱلۡإِنسَٰنَ لَيَطۡغَىٰٓ
በእውነቱ ሰው ወሰንን ያልፋል፡፡
أَن رَّءَاهُ ٱسۡتَغۡنَىٰٓ
ራሱን የተብቃቃ (ባለ ሀብት) ኾኖ ለማየቱ፡፡
إِنَّ إِلَىٰ رَبِّكَ ٱلرُّجۡعَىٰٓ
መመለሻው ወደ ጌታህ ብቻ ነው፡፡
أَرَءَيۡتَ ٱلَّذِي يَنۡهَىٰ
አየህን? ያንን የሚከለክለውን፡፡
عَبۡدًا إِذَا صَلَّىٰٓ
ባሪያን በሰገደ ጊዜ፤
أَرَءَيۡتَ إِن كَانَ عَلَى ٱلۡهُدَىٰٓ
አየህን? ንገረኝ (ተከልካዩ) በትክክለኛ መንገድ ላይ ቢኾን፤
أَوۡ أَمَرَ بِٱلتَّقۡوَىٰٓ
ወይም (ፈጣሪውን) በመፍራት ቢያዝ፤
أَرَءَيۡتَ إِن كَذَّبَ وَتَوَلَّىٰٓ
አየህን? ንገረኝ (ከልካዩ) ቢያስተባብልና (ከእምነት) ቢሸሽ፤
أَلَمۡ يَعۡلَم بِأَنَّ ٱللَّهَ يَرَىٰ
አላህ የሚያይ መኾኑን አያውቅምን?
كَلَّا لَئِن لَّمۡ يَنتَهِ لَنَسۡفَعَۢا بِٱلنَّاصِيَةِ
ይተው ባይከለከል አናቱን ይዘን እንጎትተዋለን፡፡
نَاصِيَةٖ كَٰذِبَةٍ خَاطِئَةٖ
ውሸታም ስሕተተኛ የኾነችውን አናቱን፡፡
فَلۡيَدۡعُ نَادِيَهُۥ
ሸንጎውንም ይጥራ፡፡
سَنَدۡعُ ٱلزَّبَانِيَةَ
(እኛም) ዘበኞቻችንን እንጠራለን፡፡
كَلَّا لَا تُطِعۡهُ وَٱسۡجُدۡۤ وَٱقۡتَرِب۩
ይከልከል አትታዘዘው፡፡ ስገድም፤ (ወደ አላህ) ተቃረብም፡፡ [1]
share_via