Amharische Übersetzung - Muhammad Sadiq

Übersetzung der Bedeutungen des Edlen Korans

Übersetzt von Sheikh Muhammad Sadiq und Muhammad al-Thani Habib. Die Übersetzung wurde unter der Aufsicht des Rowwad-Übersetzungszentrums entwickelt. Es ist möglich sich die Originalübersetzung zum Zwecke der Meinungsäußerung, Bewertung und kontinuierlichen Weiterentwicklung anzuschauen.

QR Code https://quran.islamcontent.com/de/amharic_sadiq

إِذَا زُلۡزِلَتِ ٱلۡأَرۡضُ زِلۡزَالَهَا

ምድር (በኀይል) መንቀጥቀጥዋን በተንቀጠቀጠች ጊዜ፤

ምድር (በኀይል) መንቀጥቀጥዋን በተንቀጠቀጠች ጊዜ፤

وَأَخۡرَجَتِ ٱلۡأَرۡضُ أَثۡقَالَهَا

ምድር ሸክሞችዋን ባወጣችም ጊዜ፤

ምድር ሸክሞችዋን ባወጣችም ጊዜ፤

وَقَالَ ٱلۡإِنسَٰنُ مَا لَهَا

ሰውም ምን ኾነች? ባለ ጊዜ፤

ሰውም ምን ኾነች? ባለ ጊዜ፤

يَوۡمَئِذٖ تُحَدِّثُ أَخۡبَارَهَا

በዚያ ቀን ወሬዎችዋን ትናገራለች፡፡

በዚያ ቀን ወሬዎችዋን ትናገራለች፡፡

بِأَنَّ رَبَّكَ أَوۡحَىٰ لَهَا

ጌታህ ለእርሷ በማሳወቁ ምክንያት፡፡

ጌታህ ለእርሷ በማሳወቁ ምክንያት፡፡

يَوۡمَئِذٖ يَصۡدُرُ ٱلنَّاسُ أَشۡتَاتٗا لِّيُرَوۡاْ أَعۡمَٰلَهُمۡ

በዚያ ቀን ሰዎች ሥራዎቻቸውን (ምንዳዋን) እንዲያዩ ይደረጉ ዘንድ (እንደየሥራቸው) የተለያዩ ኾነው (ከመቆሚያው ስፍራ) ይመለሳሉ፡፡

በዚያ ቀን ሰዎች ሥራዎቻቸውን (ምንዳዋን) እንዲያዩ ይደረጉ ዘንድ (እንደየሥራቸው) የተለያዩ ኾነው (ከመቆሚያው ስፍራ) ይመለሳሉ፡፡

فَمَن يَعۡمَلۡ مِثۡقَالَ ذَرَّةٍ خَيۡرٗا يَرَهُۥ

የብናኝ ክብደት ያክልም መልካምን የሠራ ሰው ያገኘዋል፡፡

የብናኝ ክብደት ያክልም መልካምን የሠራ ሰው ያገኘዋል፡፡

وَمَن يَعۡمَلۡ مِثۡقَالَ ذَرَّةٖ شَرّٗا يَرَهُۥ

የብናኝ ክብደት ያክልም ክፉን የሠራ ሰው ያገኘዋል፡፡

የብናኝ ክብደት ያክልም ክፉን የሠራ ሰው ያገኘዋል፡፡