Header Include

Amharic translation - Africa Academy

Translated by Muhammad Zain Zahruddin. Published by Africa Academy

QR Code https://quran.islamcontent.com/sr/amharic_zain

إِذَا ٱلشَّمۡسُ كُوِّرَتۡ

1. ጸሐይ በተጠቀለለች ጊዜ፤

1. ጸሐይ በተጠቀለለች ጊዜ፤

وَإِذَا ٱلنُّجُومُ ٱنكَدَرَتۡ

2. ከዋክብትም በረገፉ ጊዜ፤

2. ከዋክብትም በረገፉ ጊዜ፤

وَإِذَا ٱلۡجِبَالُ سُيِّرَتۡ

3. ተራራዎች በተናዱ ጊዜ፤

3. ተራራዎች በተናዱ ጊዜ፤

وَإِذَا ٱلۡعِشَارُ عُطِّلَتۡ

4. የአስር ወር እርጉዝ ግመሎች ያለጠባቂ በተተው ጊዜ፤

4. የአስር ወር እርጉዝ ግመሎች ያለጠባቂ በተተው ጊዜ፤

وَإِذَا ٱلۡوُحُوشُ حُشِرَتۡ

5. አራዊቶችም በተሰበሰቡ ጊዜ፤

5. አራዊቶችም በተሰበሰቡ ጊዜ፤

وَإِذَا ٱلۡبِحَارُ سُجِّرَتۡ

6. ባህሮችም በተቀጣጠሉ ጊዜ፤

6. ባህሮችም በተቀጣጠሉ ጊዜ፤

وَإِذَا ٱلنُّفُوسُ زُوِّجَتۡ

7. ነፍሶች በተቆራኙ ጊዜ፤

7. ነፍሶች በተቆራኙ ጊዜ፤

وَإِذَا ٱلۡمَوۡءُۥدَةُ سُئِلَتۡ

8. ከነሕይወቷ የተቀበረችው ሴት ልጅም በተጠየቀች ጊዜ፤

8. ከነሕይወቷ የተቀበረችው ሴት ልጅም በተጠየቀች ጊዜ፤

بِأَيِّ ذَنۢبٖ قُتِلَتۡ

9. በምን ወንጀል እንደተገደለች፤ በተጠየቀች ጊዜ፤

9. በምን ወንጀል እንደተገደለች፤ በተጠየቀች ጊዜ፤

وَإِذَا ٱلصُّحُفُ نُشِرَتۡ

10. ጹሑፎችም በተዘረጉ ጊዜ፤

10. ጹሑፎችም በተዘረጉ ጊዜ፤

وَإِذَا ٱلسَّمَآءُ كُشِطَتۡ

11. ሰማይም በተገሸለጠች ጊዜ፤

11. ሰማይም በተገሸለጠች ጊዜ፤

وَإِذَا ٱلۡجَحِيمُ سُعِّرَتۡ

12. ገሀነምም በተነደደች ጊዜ፤

12. ገሀነምም በተነደደች ጊዜ፤

وَإِذَا ٱلۡجَنَّةُ أُزۡلِفَتۡ

13 ገነትም በተቀረበች ጊዜ፤

13 ገነትም በተቀረበች ጊዜ፤

عَلِمَتۡ نَفۡسٞ مَّآ أَحۡضَرَتۡ

14. ነፍስ (ሁሉ ከስራ) ያቀረበችውን ታውቃለች፤

14. ነፍስ (ሁሉ ከስራ) ያቀረበችውን ታውቃለች፤

فَلَآ أُقۡسِمُ بِٱلۡخُنَّسِ

15. (ሁኔታው ከሓዲያን እንደሚሉት አይደለም):: ተመላሾች በሆኑት (ከዋክብት) እምላለሁ::

15. (ሁኔታው ከሓዲያን እንደሚሉት አይደለም):: ተመላሾች በሆኑት (ከዋክብት) እምላለሁ::

ٱلۡجَوَارِ ٱلۡكُنَّسِ

16. አንዳንድ ጊዜ ሂያጆች በሌላ ጊዜ ገቢዎች በሆኑት

16. አንዳንድ ጊዜ ሂያጆች በሌላ ጊዜ ገቢዎች በሆኑት

وَٱلَّيۡلِ إِذَا عَسۡعَسَ

17. በሌሊቱም (ጨለማውን) በጠነሰሰ ጊዜ፤

17. በሌሊቱም (ጨለማውን) በጠነሰሰ ጊዜ፤

وَٱلصُّبۡحِ إِذَا تَنَفَّسَ

18. በንጋትም (በብርሃን) በተነፈሰ ጊዜ እምላለሁ::

18. በንጋትም (በብርሃን) በተነፈሰ ጊዜ እምላለሁ::

إِنَّهُۥ لَقَوۡلُ رَسُولٖ كَرِيمٖ

19. እርሱ (ቁርኣን) የተከበረው መልዕክተኛ ጅብሪል ቃል ነው።

19. እርሱ (ቁርኣን) የተከበረው መልዕክተኛ ጅብሪል ቃል ነው።

ذِي قُوَّةٍ عِندَ ذِي ٱلۡعَرۡشِ مَكِينٖ

20. የኃይል ባለቤት የሆነ፤ ከዙፋኑ ባለቤት ዘንድም ባለሟል የሆነ፤

20. የኃይል ባለቤት የሆነ፤ ከዙፋኑ ባለቤት ዘንድም ባለሟል የሆነ፤

مُّطَاعٖ ثَمَّ أَمِينٖ

21. በዚያ ስፍራ ትዕዛዙ ተሰሚ፤ ታማኝም የሆነው (መልዕክተኛ ቃል ነው)።

21. በዚያ ስፍራ ትዕዛዙ ተሰሚ፤ ታማኝም የሆነው (መልዕክተኛ ቃል ነው)።

وَمَا صَاحِبُكُم بِمَجۡنُونٖ

22. ነብያችሁም በፍጹም እብድ አይደለም።

22. ነብያችሁም በፍጹም እብድ አይደለም።

وَلَقَدۡ رَءَاهُ بِٱلۡأُفُقِ ٱلۡمُبِينِ

23. በግልጹ አድማስ ላይ ሆኖ (ጅብሪልን) በእርግጥ አይቶታል።

23. በግልጹ አድማስ ላይ ሆኖ (ጅብሪልን) በእርግጥ አይቶታል።

وَمَا هُوَ عَلَى ٱلۡغَيۡبِ بِضَنِينٖ

24. እርሱም በሩቁ ወሬ ላይ ሰሳች (ንፉግ) አይደለም::

24. እርሱም በሩቁ ወሬ ላይ ሰሳች (ንፉግ) አይደለም::

وَمَا هُوَ بِقَوۡلِ شَيۡطَٰنٖ رَّجِيمٖ

25. (ቁርኣን) የርጉም ሰይጣን ቃልም አይደለም::

25. (ቁርኣን) የርጉም ሰይጣን ቃልም አይደለም::

فَأَيۡنَ تَذۡهَبُونَ

26. ታዲያ (ይህንን በተመለከተ) ወዴት ትሄዳላቸሁ?

26. ታዲያ (ይህንን በተመለከተ) ወዴት ትሄዳላቸሁ?

إِنۡ هُوَ إِلَّا ذِكۡرٞ لِّلۡعَٰلَمِينَ

27. እርሱ የዓለማት መገሰጫ እንጂ ሌላ አይደለም::

27. እርሱ የዓለማት መገሰጫ እንጂ ሌላ አይደለም::

لِمَن شَآءَ مِنكُمۡ أَن يَسۡتَقِيمَ

28. ከናንተ መካከል ቀጥተኛ መሆንን ለፈለገ (ሁሉ መገሰጫ) ነው።

28. ከናንተ መካከል ቀጥተኛ መሆንን ለፈለገ (ሁሉ መገሰጫ) ነው።

وَمَا تَشَآءُونَ إِلَّآ أَن يَشَآءَ ٱللَّهُ رَبُّ ٱلۡعَٰلَمِينَ

29. (ሰዎች ሆይ!) የዓለማት ጌታ የሆነው አላህ ካልሻ በስተቀር እናንተ አንድም ነገር አትሹም።

29. (ሰዎች ሆይ!) የዓለማት ጌታ የሆነው አላህ ካልሻ በስተቀር እናንተ አንድም ነገር አትሹም።
Footer Include