Amharic translation - Africa Academy
Translated by Muhammad Zain Zahruddin. Published by Africa Academy
وَٱلسَّمَآءِ ذَاتِ ٱلۡبُرُوجِ
1. የህብረ ከዋክብት ባለቤት በሆነችው ሰማይ፤
وَٱلۡيَوۡمِ ٱلۡمَوۡعُودِ
2. በተቀጠረዉም ቀን፤
وَشَاهِدٖ وَمَشۡهُودٖ
3. በመስካሪና በሚመሰከርበትም እምላለሁ::
قُتِلَ أَصۡحَٰبُ ٱلۡأُخۡدُودِ
4. የጉድቡ ባለቤቶች ተረገሙ::
ٱلنَّارِ ذَاتِ ٱلۡوَقُودِ
5. የባለማገዶዋ እሳት ባለቤቶች።
إِذۡ هُمۡ عَلَيۡهَا قُعُودٞ
6. እነርሱ በርሷ (አፋፍ) ላይ ተቀማጮች በሆኑ ጊዜ (ተረገሙ)።
وَهُمۡ عَلَىٰ مَا يَفۡعَلُونَ بِٱلۡمُؤۡمِنِينَ شُهُودٞ
7. እነርሱም በምዕመኖች ላይ ለሚሰሩት (ማሰቃየት) መስካሪዎች ናቸው።
وَمَا نَقَمُواْ مِنۡهُمۡ إِلَّآ أَن يُؤۡمِنُواْ بِٱللَّهِ ٱلۡعَزِيزِ ٱلۡحَمِيدِ
8. ከእነርሱም በአሸናፊውና በምስጉኑ ጌታ ማመናቸውን እንጂ ሌላን ምንንም አልጠሉም::
ٱلَّذِي لَهُۥ مُلۡكُ ٱلسَّمَٰوَٰتِ وَٱلۡأَرۡضِۚ وَٱللَّهُ عَلَىٰ كُلِّ شَيۡءٖ شَهِيدٌ
9. ያ የሰማይና የምድር ንግስና ለእርሱ ብቻ የሆነውን (ነው ያመኑበት)። አላህም በነገሩ ሁሉ ላይ መስካሪ ነው (አዋቂ ነው)።
إِنَّ ٱلَّذِينَ فَتَنُواْ ٱلۡمُؤۡمِنِينَ وَٱلۡمُؤۡمِنَٰتِ ثُمَّ لَمۡ يَتُوبُواْ فَلَهُمۡ عَذَابُ جَهَنَّمَ وَلَهُمۡ عَذَابُ ٱلۡحَرِيقِ
10. እነዚያ አማኞችና ምዕመናትን ያሰቃዩና ከዚያ ያልተጸጸቱ ሁሉ ለእነርሱ የገሀነም ቅጣት አለላቸው:: ለእነርሱም የመቃጠሉ ስቃይ አልላቸው::
إِنَّ ٱلَّذِينَ ءَامَنُواْ وَعَمِلُواْ ٱلصَّٰلِحَٰتِ لَهُمۡ جَنَّٰتٞ تَجۡرِي مِن تَحۡتِهَا ٱلۡأَنۡهَٰرُۚ ذَٰلِكَ ٱلۡفَوۡزُ ٱلۡكَبِيرُ
11. እነዚያ በአላህ አምነው መልካም ስራዎችን የሰሩ ሁሉ ለእነርሱ ከስሮቻቸው ወንዞች የሚፈሱባቸው ገነቶች አሏቸው:: ይህ ታላቅ ስኬት ነው::
إِنَّ بَطۡشَ رَبِّكَ لَشَدِيدٌ
12. (መልዕክተኛችን ሙሐመድ ሆይ!) የጌታህ በኃይል መያዝ ብርቱ ነው።
إِنَّهُۥ هُوَ يُبۡدِئُ وَيُعِيدُ
13. እነሆ እርሱ መፍጠርን ይጀምራል፤ ይመልሳልም::
وَهُوَ ٱلۡغَفُورُ ٱلۡوَدُودُ
14. እርሱም ምህረቱ የበዛ ወዳድ ነው::
ذُو ٱلۡعَرۡشِ ٱلۡمَجِيدُ
15. የላቀው የዙፋኑ ባለቤት ነው።
فَعَّالٞ لِّمَا يُرِيدُ
16. የሚሻውን ሁሉ ሰሪ (ፈፃሚ) ነው::
هَلۡ أَتَىٰكَ حَدِيثُ ٱلۡجُنُودِ
17. (መልዕክተኛችን ሙሐመድ ሆይ! የእነዚያ ነብያትን ያስተባበሉ) ሰራዊቶች ወሬ መጣልህን?
فِرۡعَوۡنَ وَثَمُودَ
18. የፊርዓውንና የሰሙድ (ወሬ ደርሶሃልን)?
بَلِ ٱلَّذِينَ كَفَرُواْ فِي تَكۡذِيبٖ
19. በእውነት እነዚያ (በአላህ) የካዱት (ሰዎች ሁሉ) እውነትን በማስተባበል ውስጥ ናቸው::
وَٱللَّهُ مِن وَرَآئِهِم مُّحِيطُۢ
20. አላህም በዙሪያቸው (በዕውቀቱ) ከባቢ ነው::
بَلۡ هُوَ قُرۡءَانٞ مَّجِيدٞ
21. ይልቁንም እርሱ የተከበረ ቁርኣን ነው::
فِي لَوۡحٖ مَّحۡفُوظِۭ
22. የተጠበቀ በሆነ ሰሌዳ (ሎህ) ውስጥ ነው::
مشاركة عبر