Header Include

Amharic translation - Africa Academy

Translated by Muhammad Zain Zahruddin. Published by Africa Academy

QR Code https://quran.islamcontent.com/sr/amharic_zain

وَٱلسَّمَآءِ ذَاتِ ٱلۡبُرُوجِ

1. የህብረ ከዋክብት ባለቤት በሆነችው ሰማይ፤

1. የህብረ ከዋክብት ባለቤት በሆነችው ሰማይ፤

وَٱلۡيَوۡمِ ٱلۡمَوۡعُودِ

2. በተቀጠረዉም ቀን፤

2. በተቀጠረዉም ቀን፤

وَشَاهِدٖ وَمَشۡهُودٖ

3. በመስካሪና በሚመሰከርበትም እምላለሁ::

3. በመስካሪና በሚመሰከርበትም እምላለሁ::

قُتِلَ أَصۡحَٰبُ ٱلۡأُخۡدُودِ

4. የጉድቡ ባለቤቶች ተረገሙ::

4. የጉድቡ ባለቤቶች ተረገሙ::

ٱلنَّارِ ذَاتِ ٱلۡوَقُودِ

5. የባለማገዶዋ እሳት ባለቤቶች።

5. የባለማገዶዋ እሳት ባለቤቶች።

إِذۡ هُمۡ عَلَيۡهَا قُعُودٞ

6. እነርሱ በርሷ (አፋፍ) ላይ ተቀማጮች በሆኑ ጊዜ (ተረገሙ)።

6. እነርሱ በርሷ (አፋፍ) ላይ ተቀማጮች በሆኑ ጊዜ (ተረገሙ)።

وَهُمۡ عَلَىٰ مَا يَفۡعَلُونَ بِٱلۡمُؤۡمِنِينَ شُهُودٞ

7. እነርሱም በምዕመኖች ላይ ለሚሰሩት (ማሰቃየት) መስካሪዎች ናቸው።

7. እነርሱም በምዕመኖች ላይ ለሚሰሩት (ማሰቃየት) መስካሪዎች ናቸው።

وَمَا نَقَمُواْ مِنۡهُمۡ إِلَّآ أَن يُؤۡمِنُواْ بِٱللَّهِ ٱلۡعَزِيزِ ٱلۡحَمِيدِ

8. ከእነርሱም በአሸናፊውና በምስጉኑ ጌታ ማመናቸውን እንጂ ሌላን ምንንም አልጠሉም::

8. ከእነርሱም በአሸናፊውና በምስጉኑ ጌታ ማመናቸውን እንጂ ሌላን ምንንም አልጠሉም::

ٱلَّذِي لَهُۥ مُلۡكُ ٱلسَّمَٰوَٰتِ وَٱلۡأَرۡضِۚ وَٱللَّهُ عَلَىٰ كُلِّ شَيۡءٖ شَهِيدٌ

9. ያ የሰማይና የምድር ንግስና ለእርሱ ብቻ የሆነውን (ነው ያመኑበት)። አላህም በነገሩ ሁሉ ላይ መስካሪ ነው (አዋቂ ነው)።

9. ያ የሰማይና የምድር ንግስና ለእርሱ ብቻ የሆነውን (ነው ያመኑበት)። አላህም በነገሩ ሁሉ ላይ መስካሪ ነው (አዋቂ ነው)።

إِنَّ ٱلَّذِينَ فَتَنُواْ ٱلۡمُؤۡمِنِينَ وَٱلۡمُؤۡمِنَٰتِ ثُمَّ لَمۡ يَتُوبُواْ فَلَهُمۡ عَذَابُ جَهَنَّمَ وَلَهُمۡ عَذَابُ ٱلۡحَرِيقِ

10. እነዚያ አማኞችና ምዕመናትን ያሰቃዩና ከዚያ ያልተጸጸቱ ሁሉ ለእነርሱ የገሀነም ቅጣት አለላቸው:: ለእነርሱም የመቃጠሉ ስቃይ አልላቸው::

10. እነዚያ አማኞችና ምዕመናትን ያሰቃዩና ከዚያ ያልተጸጸቱ ሁሉ ለእነርሱ የገሀነም ቅጣት አለላቸው:: ለእነርሱም የመቃጠሉ ስቃይ አልላቸው::

إِنَّ ٱلَّذِينَ ءَامَنُواْ وَعَمِلُواْ ٱلصَّٰلِحَٰتِ لَهُمۡ جَنَّٰتٞ تَجۡرِي مِن تَحۡتِهَا ٱلۡأَنۡهَٰرُۚ ذَٰلِكَ ٱلۡفَوۡزُ ٱلۡكَبِيرُ

11. እነዚያ በአላህ አምነው መልካም ስራዎችን የሰሩ ሁሉ ለእነርሱ ከስሮቻቸው ወንዞች የሚፈሱባቸው ገነቶች አሏቸው:: ይህ ታላቅ ስኬት ነው::

11. እነዚያ በአላህ አምነው መልካም ስራዎችን የሰሩ ሁሉ ለእነርሱ ከስሮቻቸው ወንዞች የሚፈሱባቸው ገነቶች አሏቸው:: ይህ ታላቅ ስኬት ነው::

إِنَّ بَطۡشَ رَبِّكَ لَشَدِيدٌ

12. (መልዕክተኛችን ሙሐመድ ሆይ!) የጌታህ በኃይል መያዝ ብርቱ ነው።

12. (መልዕክተኛችን ሙሐመድ ሆይ!) የጌታህ በኃይል መያዝ ብርቱ ነው።

إِنَّهُۥ هُوَ يُبۡدِئُ وَيُعِيدُ

13. እነሆ እርሱ መፍጠርን ይጀምራል፤ ይመልሳልም::

13. እነሆ እርሱ መፍጠርን ይጀምራል፤ ይመልሳልም::

وَهُوَ ٱلۡغَفُورُ ٱلۡوَدُودُ

14. እርሱም ምህረቱ የበዛ ወዳድ ነው::

14. እርሱም ምህረቱ የበዛ ወዳድ ነው::

ذُو ٱلۡعَرۡشِ ٱلۡمَجِيدُ

15. የላቀው የዙፋኑ ባለቤት ነው።

15. የላቀው የዙፋኑ ባለቤት ነው።

فَعَّالٞ لِّمَا يُرِيدُ

16. የሚሻውን ሁሉ ሰሪ (ፈፃሚ) ነው::

16. የሚሻውን ሁሉ ሰሪ (ፈፃሚ) ነው::

هَلۡ أَتَىٰكَ حَدِيثُ ٱلۡجُنُودِ

17. (መልዕክተኛችን ሙሐመድ ሆይ! የእነዚያ ነብያትን ያስተባበሉ) ሰራዊቶች ወሬ መጣልህን?

17. (መልዕክተኛችን ሙሐመድ ሆይ! የእነዚያ ነብያትን ያስተባበሉ) ሰራዊቶች ወሬ መጣልህን?

فِرۡعَوۡنَ وَثَمُودَ

18. የፊርዓውንና የሰሙድ (ወሬ ደርሶሃልን)?

18. የፊርዓውንና የሰሙድ (ወሬ ደርሶሃልን)?

بَلِ ٱلَّذِينَ كَفَرُواْ فِي تَكۡذِيبٖ

19. በእውነት እነዚያ (በአላህ) የካዱት (ሰዎች ሁሉ) እውነትን በማስተባበል ውስጥ ናቸው::

19. በእውነት እነዚያ (በአላህ) የካዱት (ሰዎች ሁሉ) እውነትን በማስተባበል ውስጥ ናቸው::

وَٱللَّهُ مِن وَرَآئِهِم مُّحِيطُۢ

20. አላህም በዙሪያቸው (በዕውቀቱ) ከባቢ ነው::

20. አላህም በዙሪያቸው (በዕውቀቱ) ከባቢ ነው::

بَلۡ هُوَ قُرۡءَانٞ مَّجِيدٞ

21. ይልቁንም እርሱ የተከበረ ቁርኣን ነው::

21. ይልቁንም እርሱ የተከበረ ቁርኣን ነው::

فِي لَوۡحٖ مَّحۡفُوظِۭ

22. የተጠበቀ በሆነ ሰሌዳ (ሎህ) ውስጥ ነው::

22. የተጠበቀ በሆነ ሰሌዳ (ሎህ) ውስጥ ነው::
Footer Include