Header Include

Amharic translation - Africa Academy

Translated by Muhammad Zain Zahruddin. Published by Africa Academy

QR Code https://quran.islamcontent.com/sr/amharic_zain

وَٱلشَّمۡسِ وَضُحَىٰهَا

1. በጸሐይና በብርሀኗ፤ (እምላለሁ)

1. በጸሐይና በብርሀኗ፤ (እምላለሁ)

وَٱلۡقَمَرِ إِذَا تَلَىٰهَا

2. በጨረቃም ጸሐይን በተከተላት ጊዜ፤

2. በጨረቃም ጸሐይን በተከተላት ጊዜ፤

وَٱلنَّهَارِ إِذَا جَلَّىٰهَا

3. በቀንም ጸሐይን በገለፃት ጊዜ፤

3. በቀንም ጸሐይን በገለፃት ጊዜ፤

وَٱلَّيۡلِ إِذَا يَغۡشَىٰهَا

4. በሌሊቱም ጸሐይን በሸፈናት ጊዜ፤

4. በሌሊቱም ጸሐይን በሸፈናት ጊዜ፤

وَٱلسَّمَآءِ وَمَا بَنَىٰهَا

5. በሰማይ እና በገነባትም፤

5. በሰማይ እና በገነባትም፤

وَٱلۡأَرۡضِ وَمَا طَحَىٰهَا

6. በምድር እና በዘረጋትም፤

6. በምድር እና በዘረጋትም፤

وَنَفۡسٖ وَمَا سَوَّىٰهَا

7. በነፍስም ባስተካከላትም

7. በነፍስም ባስተካከላትም

فَأَلۡهَمَهَا فُجُورَهَا وَتَقۡوَىٰهَا

8. አመጽዋንና ፍርሃቷንም ባሳወቃት (አምላክም በአላህ እምላለሁ)።

8. አመጽዋንና ፍርሃቷንም ባሳወቃት (አምላክም በአላህ እምላለሁ)።

قَدۡ أَفۡلَحَ مَن زَكَّىٰهَا

9. (ነፍስን) ከኃጢአት ያጠራ ሰው ሁሉ በእርግጥ ተሳካለት።

9. (ነፍስን) ከኃጢአት ያጠራ ሰው ሁሉ በእርግጥ ተሳካለት።

وَقَدۡ خَابَ مَن دَسَّىٰهَا

10. በኃጢአትም የሸፈናት ሰው ሁሉ በእውነት አፈረ (ከሰረ)::

10. በኃጢአትም የሸፈናት ሰው ሁሉ በእውነት አፈረ (ከሰረ)::

كَذَّبَتۡ ثَمُودُ بِطَغۡوَىٰهَآ

11. ሰሙድ ወሰን በማለፍዋ ምክንያት አስተባበለች፤

11. ሰሙድ ወሰን በማለፍዋ ምክንያት አስተባበለች፤

إِذِ ٱنۢبَعَثَ أَشۡقَىٰهَا

12. ጠማማዋ በተነሳ ጊዜ።

12. ጠማማዋ በተነሳ ጊዜ።

فَقَالَ لَهُمۡ رَسُولُ ٱللَّهِ نَاقَةَ ٱللَّهِ وَسُقۡيَٰهَا

13. ለእነርሱም የአላህ መልዕክተኛ (ሷሊህ)፡-የአላህን ግመልና የመጠጥ ተራዋን (ጠብቁላት) አላቸው::

13. ለእነርሱም የአላህ መልዕክተኛ (ሷሊህ)፡-የአላህን ግመልና የመጠጥ ተራዋን (ጠብቁላት) አላቸው::

فَكَذَّبُوهُ فَعَقَرُوهَا فَدَمۡدَمَ عَلَيۡهِمۡ رَبُّهُم بِذَنۢبِهِمۡ فَسَوَّىٰهَا

14. እነርሱ አስተባበሉትም፤ ከዚያ ወጓት፤ በኃጢአታቸዉም ምክንያት ጌታቸው (ቅጣትን) በእነርሱ ላይ ደመደመባቸው፤ አስተካከላትም::

14. እነርሱ አስተባበሉትም፤ ከዚያ ወጓት፤ በኃጢአታቸዉም ምክንያት ጌታቸው (ቅጣትን) በእነርሱ ላይ ደመደመባቸው፤ አስተካከላትም::

وَلَا يَخَافُ عُقۡبَٰهَا

15. (የምታስተካክለውን) ፍፃሜዋንም አይፈራም።

15. (የምታስተካክለውን) ፍፃሜዋንም አይፈራም።
Footer Include