Amharic translation - Africa Academy
Translated by Muhammad Zain Zahruddin. Published by Africa Academy
سَبِّحِ ٱسۡمَ رَبِّكَ ٱلۡأَعۡلَى
1. (መልዕክተኛችን ሙሐመድ ሆይ!) የዚያን ከሁሉ በላይ የሆነውን ጌታህን ስም አጥራ (አሞግስ)።
ٱلَّذِي خَلَقَ فَسَوَّىٰ
2. ያ ሁሉን ነገር የፈጠረውንና ያስተካከለውን፤
وَٱلَّذِي قَدَّرَ فَهَدَىٰ
3. ያን የወሰነውን ነገርንም ሁሉ ለተፈጠረለት የመራውን፤
وَٱلَّذِيٓ أَخۡرَجَ ٱلۡمَرۡعَىٰ
4. ያም ግጦሽን ለምለም አርጎ ያወጣውን፤
فَجَعَلَهُۥ غُثَآءً أَحۡوَىٰ
5.(ከዚያ) ደረቅ ጥቁር ያደረገውንም (አምላክ ስም አሞግስ)፡፡
سَنُقۡرِئُكَ فَلَا تَنسَىٰٓ
6. (መልዕክተኛችን ሙሐመድ ሆይ!) ቁርኣንን በእርግጥ እናስነብብሃለን፤ አትረሳምም፤
إِلَّا مَا شَآءَ ٱللَّهُۚ إِنَّهُۥ يَعۡلَمُ ٱلۡجَهۡرَ وَمَا يَخۡفَىٰ
7. አላህ ከፈለገው ነገር በስተቀር፤ እናም እርሱ ግልጹንም የሚሸሽገውንም ሁሉ ያውቃልና፤
وَنُيَسِّرُكَ لِلۡيُسۡرَىٰ
8. ለገሪቱም (ሕይወት እስላምን ትከተል ዘንድ) እናገራሃለን።
فَذَكِّرۡ إِن نَّفَعَتِ ٱلذِّكۡرَىٰ
9. (ሰዎችንም) ገስፅ፤ ግሳፄይቱ ብትጠቅም።
سَيَذَّكَّرُ مَن يَخۡشَىٰ
10. (አላህን) የሚፈራ በእርግጥ ይገሰፃል።
وَيَتَجَنَّبُهَا ٱلۡأَشۡقَى
11. መናጢዉም ይርቃታል::
ٱلَّذِي يَصۡلَى ٱلنَّارَ ٱلۡكُبۡرَىٰ
12. ያ! ታላቂቱን እሳት የሚገባው፤
ثُمَّ لَا يَمُوتُ فِيهَا وَلَا يَحۡيَىٰ
13. ከዚያም በእርሷ ውስጥ የማይሞትና ህያዉም የማይሆነው።
قَدۡ أَفۡلَحَ مَن تَزَكَّىٰ
14. (አላህን ከማመፅ) የተጥራራ ሰው በእርግጥ ዳነ፤
وَذَكَرَ ٱسۡمَ رَبِّهِۦ فَصَلَّىٰ
15. የጌታውንም ስም ያወሳና የሰገደ::
بَلۡ تُؤۡثِرُونَ ٱلۡحَيَوٰةَ ٱلدُّنۡيَا
16. ይልቁንም ቅርቢቱን ሕይወት ታስቀድማላችሁ፤
وَٱلۡأٓخِرَةُ خَيۡرٞ وَأَبۡقَىٰٓ
17. (ሰዎች ሆይ!) መጨረሻይቱ ሕይወት በላጭና፤ ዘወታሪ ሆና ሳለ።
إِنَّ هَٰذَا لَفِي ٱلصُّحُفِ ٱلۡأُولَىٰ
18. ይህ በቀደምቶቹም መጻሕፍት ውስጥ ያለ ነው።
صُحُفِ إِبۡرَٰهِيمَ وَمُوسَىٰ
19. በኢብራሂምና በሙሳ መጽሐፍት ውስጥ የሰፈረ እውነታ ነው።
مشاركة عبر