Header Include

Terjemahan Berbahasa Amhar

Terjemahan makna Al-Qur`ān Al-Karīm ke bahasa Amhar oleh Muhammad Sadiq dan Muhammad Al-Sani Habib. Sudah dikoreksi di bawah pengawasan Markaz Ruwād Terjemah. Teks terjemahan asli masih bisa ditampilkan untuk diberi masukan, evaluasi dan pengembangan.

QR Code https://quran.islamcontent.com/id/amharic_sadiq

وَٱلۡمُرۡسَلَٰتِ عُرۡفٗا

ተከታታይ ኾነው በተላኩት፣

ተከታታይ ኾነው በተላኩት፣

فَٱلۡعَٰصِفَٰتِ عَصۡفٗا

በኀይል መንፈስን ነፋሾች በኾኑትም፣

በኀይል መንፈስን ነፋሾች በኾኑትም፣

وَٱلنَّٰشِرَٰتِ نَشۡرٗا

መበተንን በታኞች በኾኑትም፤ (ነፋሶች)፣

መበተንን በታኞች በኾኑትም፤ (ነፋሶች)፣

فَٱلۡفَٰرِقَٰتِ فَرۡقٗا

መለየትን ለይዎች በኾኑትም፣

መለየትን ለይዎች በኾኑትም፣

فَٱلۡمُلۡقِيَٰتِ ذِكۡرًا

መገሠጫን (ወደ ነቢያት) ጣይዎች በኾኑትም፣

መገሠጫን (ወደ ነቢያት) ጣይዎች በኾኑትም፣

عُذۡرًا أَوۡ نُذۡرًا

ምክንያትን ለማስወገድ ወይም ለማስፈራራት (ጣይዎች በኾኑት መላእክት) እምላለሁ፡፡

ምክንያትን ለማስወገድ ወይም ለማስፈራራት (ጣይዎች በኾኑት መላእክት) እምላለሁ፡፡

إِنَّمَا تُوعَدُونَ لَوَٰقِعٞ

ያ የምትስፈራሩበት (ትንሣኤ) በእርግጥ ኋኝ ነው፡፡

ያ የምትስፈራሩበት (ትንሣኤ) በእርግጥ ኋኝ ነው፡፡

فَإِذَا ٱلنُّجُومُ طُمِسَتۡ

ከዋክብትም (ብርሃንዋ) በታበሰች ጊዜ፡፡

ከዋክብትም (ብርሃንዋ) በታበሰች ጊዜ፡፡

وَإِذَا ٱلسَّمَآءُ فُرِجَتۡ

ሰማይም በተከፈተች ጊዜ፡፡

ሰማይም በተከፈተች ጊዜ፡፡

وَإِذَا ٱلۡجِبَالُ نُسِفَتۡ

ጋራዎችም በተንኮተኮቱ ጊዜ፡፡

ጋራዎችም በተንኮተኮቱ ጊዜ፡፡

وَإِذَا ٱلرُّسُلُ أُقِّتَتۡ

መልክተኞቹም ወቅት በተደረገላቸው ጊዜ፡፡

መልክተኞቹም ወቅት በተደረገላቸው ጊዜ፡፡

لِأَيِّ يَوۡمٍ أُجِّلَتۡ

ለየትኛው ቀን ተቀጠሩ (የሚባል ሲኾን)፤

ለየትኛው ቀን ተቀጠሩ (የሚባል ሲኾን)፤

لِيَوۡمِ ٱلۡفَصۡلِ

ለመለያው ቀን (በተባለ ጊዜ፤ በፍጡሮች መካከል ይፈረዳል)፡፡

ለመለያው ቀን (በተባለ ጊዜ፤ በፍጡሮች መካከል ይፈረዳል)፡፡

وَمَآ أَدۡرَىٰكَ مَا يَوۡمُ ٱلۡفَصۡلِ

የመለያውም ቀን ምን እንደኾነ ምን አሳወቀህ?

የመለያውም ቀን ምን እንደኾነ ምን አሳወቀህ?

وَيۡلٞ يَوۡمَئِذٖ لِّلۡمُكَذِّبِينَ

ለአስተባባዮች በዚያ ቀን ወዮላቸው፡፡ {1}

{1} ይህ አንቀጽ በዚህ ምእራፍ ውስጥ 10 ግዜ ተደጋግሟል
ለአስተባባዮች በዚያ ቀን ወዮላቸው፡፡ {1}

أَلَمۡ نُهۡلِكِ ٱلۡأَوَّلِينَ

የፊተኞቹን (ሕዝቦች) አላጠፋንምን?

የፊተኞቹን (ሕዝቦች) አላጠፋንምን?

ثُمَّ نُتۡبِعُهُمُ ٱلۡأٓخِرِينَ

ከዚያም የኋለኞቹን እናስከትላቸዋለን፡፡

ከዚያም የኋለኞቹን እናስከትላቸዋለን፡፡

كَذَٰلِكَ نَفۡعَلُ بِٱلۡمُجۡرِمِينَ

በአመጸኞች ሁሉ እንደዚሁ እንሠራለን፡፡

በአመጸኞች ሁሉ እንደዚሁ እንሠራለን፡፡

وَيۡلٞ يَوۡمَئِذٖ لِّلۡمُكَذِّبِينَ

ለአስተባባዮች በዚያ ቀን ወዮላቸው፡፡

ለአስተባባዮች በዚያ ቀን ወዮላቸው፡፡

أَلَمۡ نَخۡلُقكُّم مِّن مَّآءٖ مَّهِينٖ

ከደካማ ውሃ አልፈጠርናችሁምን?

ከደካማ ውሃ አልፈጠርናችሁምን?

فَجَعَلۡنَٰهُ فِي قَرَارٖ مَّكِينٍ

በተጠበቀ መርጊያ ውስጥም (በማሕፀን) አደረግነው፡፡

በተጠበቀ መርጊያ ውስጥም (በማሕፀን) አደረግነው፡፡

إِلَىٰ قَدَرٖ مَّعۡلُومٖ

እስከ ታወቀ ልክ ድረስ፡፡

እስከ ታወቀ ልክ ድረስ፡፡

فَقَدَرۡنَا فَنِعۡمَ ٱلۡقَٰدِرُونَ

መጠንነውም፤ ምን ያማርንም መጣኞች ነን!

መጠንነውም፤ ምን ያማርንም መጣኞች ነን!

وَيۡلٞ يَوۡمَئِذٖ لِّلۡمُكَذِّبِينَ

ለአስተባባዮች በዚያ ቀን ወዮላቸው፡፡

ለአስተባባዮች በዚያ ቀን ወዮላቸው፡፡

أَلَمۡ نَجۡعَلِ ٱلۡأَرۡضَ كِفَاتًا

ምድርን ሰብሳቢ አላደረግናትምን?

ምድርን ሰብሳቢ አላደረግናትምን?

أَحۡيَآءٗ وَأَمۡوَٰتٗا

ሕያዋን ኾናችሁ ሙታንም ኾናችሁ፡፡

ሕያዋን ኾናችሁ ሙታንም ኾናችሁ፡፡

وَجَعَلۡنَا فِيهَا رَوَٰسِيَ شَٰمِخَٰتٖ وَأَسۡقَيۡنَٰكُم مَّآءٗ فُرَاتٗا

በውስጧም ከፍተኛዎችን ተራራዎች አደረግን፡፡ ጣፋጭ ውሃንም አጠጣናችሁ፡፡

በውስጧም ከፍተኛዎችን ተራራዎች አደረግን፡፡ ጣፋጭ ውሃንም አጠጣናችሁ፡፡

وَيۡلٞ يَوۡمَئِذٖ لِّلۡمُكَذِّبِينَ

ለአስተባባዮች በዚያ ቀን ወዮላቸው፡፡

ለአስተባባዮች በዚያ ቀን ወዮላቸው፡፡

ٱنطَلِقُوٓاْ إِلَىٰ مَا كُنتُم بِهِۦ تُكَذِّبُونَ

«ወደዚያ በእርሱ ታስተባብሉ ወደ ነበራችሁት (ቅጣት) አዝግሙ፡፡

«ወደዚያ በእርሱ ታስተባብሉ ወደ ነበራችሁት (ቅጣት) አዝግሙ፡፡

ٱنطَلِقُوٓاْ إِلَىٰ ظِلّٖ ذِي ثَلَٰثِ شُعَبٖ

«ባለ ሦስት ቅርንጫፎች ወደ ኾነው ጥላ አዝግሙ፤» (ይባላሉ)፡፡

«ባለ ሦስት ቅርንጫፎች ወደ ኾነው ጥላ አዝግሙ፤» (ይባላሉ)፡፡

لَّا ظَلِيلٖ وَلَا يُغۡنِي مِنَ ٱللَّهَبِ

አጠላይ ያልኾነ ከእሳቱም ላንቃ የማያድን ወደ ኾነው (አዝግሙ)፡፡

አጠላይ ያልኾነ ከእሳቱም ላንቃ የማያድን ወደ ኾነው (አዝግሙ)፡፡

إِنَّهَا تَرۡمِي بِشَرَرٖ كَٱلۡقَصۡرِ

እርሷ እንደ ታላላቅ ሕንጻ የኾኑን ቃንቄዎች ትወረውራለች፡፡

እርሷ እንደ ታላላቅ ሕንጻ የኾኑን ቃንቄዎች ትወረውራለች፡፡

كَأَنَّهُۥ جِمَٰلَتٞ صُفۡرٞ

(ቃንቄውም) ልክ ዳለቻዎች ግመሎችን ይመስላል፡፡

(ቃንቄውም) ልክ ዳለቻዎች ግመሎችን ይመስላል፡፡

وَيۡلٞ يَوۡمَئِذٖ لِّلۡمُكَذِّبِينَ

ለአስተባባዮች በዚያ ቀን ወዮላቸው፡፡

ለአስተባባዮች በዚያ ቀን ወዮላቸው፡፡

هَٰذَا يَوۡمُ لَا يَنطِقُونَ

ይህ የማይናገሩበት ቀን ነው፡፡

ይህ የማይናገሩበት ቀን ነው፡፡

وَلَا يُؤۡذَنُ لَهُمۡ فَيَعۡتَذِرُونَ

ይቅርታም ይጠይቁ ዘንድ፤ ለእነርሱ አይፈቀድላቸውም፡፡

ይቅርታም ይጠይቁ ዘንድ፤ ለእነርሱ አይፈቀድላቸውም፡፡

وَيۡلٞ يَوۡمَئِذٖ لِّلۡمُكَذِّبِينَ

ለአስተባባዮች በዚያ ቀን ወዮላቸው፡፡

ለአስተባባዮች በዚያ ቀን ወዮላቸው፡፡

هَٰذَا يَوۡمُ ٱلۡفَصۡلِۖ جَمَعۡنَٰكُمۡ وَٱلۡأَوَّلِينَ

ይህ መለያው ቀን ነው፡፡ እናንተንም የፊተኞቹንም ሰብሰብናችሁ፡፡

ይህ መለያው ቀን ነው፡፡ እናንተንም የፊተኞቹንም ሰብሰብናችሁ፡፡

فَإِن كَانَ لَكُمۡ كَيۡدٞ فَكِيدُونِ

ለናንተም (ለማምለጥ) ብልሃት እንዳላችሁ ተተናኮሉኝ፡፡

ለናንተም (ለማምለጥ) ብልሃት እንዳላችሁ ተተናኮሉኝ፡፡

وَيۡلٞ يَوۡمَئِذٖ لِّلۡمُكَذِّبِينَ

ላስተባባዮች በዚያ ቀን ወዮላቸው፡፡

ላስተባባዮች በዚያ ቀን ወዮላቸው፡፡

إِنَّ ٱلۡمُتَّقِينَ فِي ظِلَٰلٖ وَعُيُونٖ

ጥንቁቆቹ በጥላዎችና በምንጮች ውስጥ ናቸው፡፡

ጥንቁቆቹ በጥላዎችና በምንጮች ውስጥ ናቸው፡፡

وَفَوَٰكِهَ مِمَّا يَشۡتَهُونَ

ከሚከጅሉትም ሁሉ በፍራፍሬዎች ውስጥ ናቸው፡፡

ከሚከጅሉትም ሁሉ በፍራፍሬዎች ውስጥ ናቸው፡፡

كُلُواْ وَٱشۡرَبُواْ هَنِيٓـَٔۢا بِمَا كُنتُمۡ تَعۡمَلُونَ

«ትሠሩት በነበራችሁት ዋጋ የምትደሰቱ ኾናችሁ ብሉ፣ ጠጡም፤» (ይባላሉ)፡፡

«ትሠሩት በነበራችሁት ዋጋ የምትደሰቱ ኾናችሁ ብሉ፣ ጠጡም፤» (ይባላሉ)፡፡

إِنَّا كَذَٰلِكَ نَجۡزِي ٱلۡمُحۡسِنِينَ

እኛ እንደዚሁ መልካም ሠሪዎችን ሁሉ እንመነዳለን፡፡

እኛ እንደዚሁ መልካም ሠሪዎችን ሁሉ እንመነዳለን፡፡

وَيۡلٞ يَوۡمَئِذٖ لِّلۡمُكَذِّبِينَ

ለአስተባባዮች በዚያ ቀን ወዮላቸው፡፡

ለአስተባባዮች በዚያ ቀን ወዮላቸው፡፡

كُلُواْ وَتَمَتَّعُواْ قَلِيلًا إِنَّكُم مُّجۡرِمُونَ

ብሉ፤ ጥቂትንም (ጊዜ) ተጠቀሙ፡፡ እናንተ አመጸኞች ናችሁና፡፡

ብሉ፤ ጥቂትንም (ጊዜ) ተጠቀሙ፡፡ እናንተ አመጸኞች ናችሁና፡፡

وَيۡلٞ يَوۡمَئِذٖ لِّلۡمُكَذِّبِينَ

ለአስተባባዮች በዚያ ቀን ወዮላቸው፡፡

ለአስተባባዮች በዚያ ቀን ወዮላቸው፡፡

وَإِذَا قِيلَ لَهُمُ ٱرۡكَعُواْ لَا يَرۡكَعُونَ

«ለእነርሱ ስገዱም» በተባሉ ጊዜ አይሰግዱም፡፡

«ለእነርሱ ስገዱም» በተባሉ ጊዜ አይሰግዱም፡፡

وَيۡلٞ يَوۡمَئِذٖ لِّلۡمُكَذِّبِينَ

ለአስተባባዮች በዚያ ቀን ወዮላቸው፡፡

ለአስተባባዮች በዚያ ቀን ወዮላቸው፡፡

فَبِأَيِّ حَدِيثِۭ بَعۡدَهُۥ يُؤۡمِنُونَ

ከእርሱም ሌላ በየትኛው ንግግር ያምናሉ?

ከእርሱም ሌላ በየትኛው ንግግር ያምናሉ?
Footer Include