Header Include

Terjemahan Berbahasa Amhar

Terjemahan makna Al-Qur`ān Al-Karīm ke bahasa Amhar oleh Muhammad Sadiq dan Muhammad Al-Sani Habib. Sudah dikoreksi di bawah pengawasan Markaz Ruwād Terjemah. Teks terjemahan asli masih bisa ditampilkan untuk diberi masukan, evaluasi dan pengembangan.

QR Code https://quran.islamcontent.com/id/amharic_sadiq

إِذَا ٱلسَّمَآءُ ٱنفَطَرَتۡ

ሰማይ በተሰነጠቀች ጊዜ፤

ሰማይ በተሰነጠቀች ጊዜ፤

وَإِذَا ٱلۡكَوَاكِبُ ٱنتَثَرَتۡ

ከዋክብትም ተበታትነው በወደቁ ጊዜ፤

ከዋክብትም ተበታትነው በወደቁ ጊዜ፤

وَإِذَا ٱلۡبِحَارُ فُجِّرَتۡ

ባሕሮችም በተከፈቱና በተደበላለቁ ጊዜ፤

ባሕሮችም በተከፈቱና በተደበላለቁ ጊዜ፤

وَإِذَا ٱلۡقُبُورُ بُعۡثِرَتۡ

መቃብሮችም በተገለባበጡና (ሙታን) በተነሱ ጊዜ፤

መቃብሮችም በተገለባበጡና (ሙታን) በተነሱ ጊዜ፤

عَلِمَتۡ نَفۡسٞ مَّا قَدَّمَتۡ وَأَخَّرَتۡ

ማንኛይቱም ነፍስ ያስቀደመችውንና ያቆየችውን ታውቃለች፡፡

ማንኛይቱም ነፍስ ያስቀደመችውንና ያቆየችውን ታውቃለች፡፡

يَٰٓأَيُّهَا ٱلۡإِنسَٰنُ مَا غَرَّكَ بِرَبِّكَ ٱلۡكَرِيمِ

አንተ ሰው ሆይ! በቸሩ ጌታህ ምን አታለለህ?

አንተ ሰው ሆይ! በቸሩ ጌታህ ምን አታለለህ?

ٱلَّذِي خَلَقَكَ فَسَوَّىٰكَ فَعَدَلَكَ

በዚያ በፈጠረህ አካለ ሙሉም ባደረገህ ባስተካከለህም፡፡

በዚያ በፈጠረህ አካለ ሙሉም ባደረገህ ባስተካከለህም፡፡

فِيٓ أَيِّ صُورَةٖ مَّا شَآءَ رَكَّبَكَ

በማንኛውም በሻው ቅርፅ በገጣጠመህ (ጌታህ ምን አታለለህ)፡፡

በማንኛውም በሻው ቅርፅ በገጣጠመህ (ጌታህ ምን አታለለህ)፡፡

كَلَّا بَلۡ تُكَذِّبُونَ بِٱلدِّينِ

ተከልከሉ፤ በእውነቱ በፍርዱ ቀን ታስተባብላላችሁ፡፡

ተከልከሉ፤ በእውነቱ በፍርዱ ቀን ታስተባብላላችሁ፡፡

وَإِنَّ عَلَيۡكُمۡ لَحَٰفِظِينَ

በእናንተ ላይ ተጠባባቂዎች ያሉባችሁ፤ ስትኾኑ፤

በእናንተ ላይ ተጠባባቂዎች ያሉባችሁ፤ ስትኾኑ፤

كِرَامٗا كَٰتِبِينَ

የተከበሩ ጸሐፊዎች የኾኑ፤ (ተጠባባቂዎች)፡፡

የተከበሩ ጸሐፊዎች የኾኑ፤ (ተጠባባቂዎች)፡፡

يَعۡلَمُونَ مَا تَفۡعَلُونَ

የምትሠሩትን ሁሉ የሚያውቁ፡፡

የምትሠሩትን ሁሉ የሚያውቁ፡፡

إِنَّ ٱلۡأَبۡرَارَ لَفِي نَعِيمٖ

እውነተኞቹ ምእምናን በእርግጥ በገነት ውስጥ ናቸው፡፡

እውነተኞቹ ምእምናን በእርግጥ በገነት ውስጥ ናቸው፡፡

وَإِنَّ ٱلۡفُجَّارَ لَفِي جَحِيمٖ

ከሓዲዎቹም በእርግጥ በገሀነም ውስጥ ናቸው፡፡

ከሓዲዎቹም በእርግጥ በገሀነም ውስጥ ናቸው፡፡

يَصۡلَوۡنَهَا يَوۡمَ ٱلدِّينِ

በፍርዱ ቀን ይገቧታል፡፡

በፍርዱ ቀን ይገቧታል፡፡

وَمَا هُمۡ عَنۡهَا بِغَآئِبِينَ

እነርሱም ከርሷ ራቂዎች አይደሉም፡፡

እነርሱም ከርሷ ራቂዎች አይደሉም፡፡

وَمَآ أَدۡرَىٰكَ مَا يَوۡمُ ٱلدِّينِ

የፍርድ ቀን ምን እንደኾነ ምን አሳወቀህ?

የፍርድ ቀን ምን እንደኾነ ምን አሳወቀህ?

ثُمَّ مَآ أَدۡرَىٰكَ مَا يَوۡمُ ٱلدِّينِ

ከዚያም የፍርዱ ቀን ምን እንደኾነ ምን አሳወቀህ?

ከዚያም የፍርዱ ቀን ምን እንደኾነ ምን አሳወቀህ?

يَوۡمَ لَا تَمۡلِكُ نَفۡسٞ لِّنَفۡسٖ شَيۡـٔٗاۖ وَٱلۡأَمۡرُ يَوۡمَئِذٖ لِّلَّهِ

(እርሱ) ማንኛይቱም ነፍስ ለሌላይቱ ነፍስ ምንም ማድረግን የማትችልበት ቀን ነው፡፡ ነገሩም ሁሉ በዚያ ቀን ለአላህ ብቻ ነው፡፡

(እርሱ) ማንኛይቱም ነፍስ ለሌላይቱ ነፍስ ምንም ማድረግን የማትችልበት ቀን ነው፡፡ ነገሩም ሁሉ በዚያ ቀን ለአላህ ብቻ ነው፡፡
Footer Include