Header Include

Amharic translation - Africa Academy

Translated by Muhammad Zain Zahruddin. Published by Africa Academy

QR Code https://quran.islamcontent.com/ro/amharic_zain

وَٱلصَّٰٓفَّٰتِ صَفّٗا

1. መሰለፍን በሚሰለፉት፤

1. መሰለፍን በሚሰለፉት፤

فَٱلزَّٰجِرَٰتِ زَجۡرٗا

2. (ደመና) መንዳትን በሚነዱት፤

2. (ደመና) መንዳትን በሚነዱት፤

فَٱلتَّٰلِيَٰتِ ذِكۡرًا

3. ቁርኣንንም በሚያነቡት እምላለሁ::

3. ቁርኣንንም በሚያነቡት እምላለሁ::

إِنَّ إِلَٰهَكُمۡ لَوَٰحِدٞ

4. አምላካችሁ በእርግጥ አንድ ብቻ ነው::

4. አምላካችሁ በእርግጥ አንድ ብቻ ነው::

رَّبُّ ٱلسَّمَٰوَٰتِ وَٱلۡأَرۡضِ وَمَا بَيۡنَهُمَا وَرَبُّ ٱلۡمَشَٰرِقِ

5. እርሱ ያ በሰማያትና በምድር በመካካለቸው ያለውም ፍጡር ሁሉ ጌታ ነው:: የምስራቆችም ጌታ ነው::

5. እርሱ ያ በሰማያትና በምድር በመካካለቸው ያለውም ፍጡር ሁሉ ጌታ ነው:: የምስራቆችም ጌታ ነው::

إِنَّا زَيَّنَّا ٱلسَّمَآءَ ٱلدُّنۡيَا بِزِينَةٍ ٱلۡكَوَاكِبِ

6. እኛ ቅርቢቱን ሰማይ በከዋክብት ጌጥ አጌጥናት (አስዋብናት)::

6. እኛ ቅርቢቱን ሰማይ በከዋክብት ጌጥ አጌጥናት (አስዋብናት)::

وَحِفۡظٗا مِّن كُلِّ شَيۡطَٰنٖ مَّارِدٖ

7. አመጸኛ ከሆነ ሰይጣንም ሁሉ መጠበቅን ጠበቅናት::

7. አመጸኛ ከሆነ ሰይጣንም ሁሉ መጠበቅን ጠበቅናት::

لَّا يَسَّمَّعُونَ إِلَى ٱلۡمَلَإِ ٱلۡأَعۡلَىٰ وَيُقۡذَفُونَ مِن كُلِّ جَانِبٖ

8. ወደ ላይኛው ሰራዊት አያደምጡም፤ ከየአቅጣጫውም ሁሉ ችቦ ይጣልባቸዋል፤ (ይቀጠቀጣሉ)።

8. ወደ ላይኛው ሰራዊት አያደምጡም፤ ከየአቅጣጫውም ሁሉ ችቦ ይጣልባቸዋል፤ (ይቀጠቀጣሉ)።

دُحُورٗاۖ وَلَهُمۡ عَذَابٞ وَاصِبٌ

9. የሚባረሩ ሲሆኑ (ይጣልባቸዋል)፤ ለእነርሱም ዘውታሪ ቅጣት አለባቸው::

9. የሚባረሩ ሲሆኑ (ይጣልባቸዋል)፤ ለእነርሱም ዘውታሪ ቅጣት አለባቸው::

إِلَّا مَنۡ خَطِفَ ٱلۡخَطۡفَةَ فَأَتۡبَعَهُۥ شِهَابٞ ثَاقِبٞ

10. ንጥቂያን የነጠቀ ወዲያውኑም አብሪ ኮከብ የተከተለው ሲቀር (እርሱ ይሰማዋል)::

10. ንጥቂያን የነጠቀ ወዲያውኑም አብሪ ኮከብ የተከተለው ሲቀር (እርሱ ይሰማዋል)::

فَٱسۡتَفۡتِهِمۡ أَهُمۡ أَشَدُّ خَلۡقًا أَم مَّنۡ خَلَقۡنَآۚ إِنَّا خَلَقۡنَٰهُم مِّن طِينٖ لَّازِبِۭ

11. (መልዕክተኛችን ሙሐመድ ሆይ!) ጠይቃቸውም፤ እነርሱ በአፈጣጠር ይበልጥ የበረቱ ናቸውን? ወይስ እኛ ከእነርሱ በፊት የፈጠረነው ፍጡር? እኛ ከሚጣበቅ ጭቃ ፈጠርናቸው::

11. (መልዕክተኛችን ሙሐመድ ሆይ!) ጠይቃቸውም፤ እነርሱ በአፈጣጠር ይበልጥ የበረቱ ናቸውን? ወይስ እኛ ከእነርሱ በፊት የፈጠረነው ፍጡር? እኛ ከሚጣበቅ ጭቃ ፈጠርናቸው::

بَلۡ عَجِبۡتَ وَيَسۡخَرُونَ

12. ይልቁንም ማስተባበላቸው አስደነቀህ፤ በመደነቅህም ይሳለቃሉ::

12. ይልቁንም ማስተባበላቸው አስደነቀህ፤ በመደነቅህም ይሳለቃሉ::

وَإِذَا ذُكِّرُواْ لَا يَذۡكُرُونَ

13. በተገሰጹም ጊዜ አይገሰጹም::

13. በተገሰጹም ጊዜ አይገሰጹም::

وَإِذَا رَأَوۡاْ ءَايَةٗ يَسۡتَسۡخِرُونَ

14. ተዓምርንም ባዩ ጊዜ ለመሳለቅ ይጣጣራሉ።

14. ተዓምርንም ባዩ ጊዜ ለመሳለቅ ይጣጣራሉ።

وَقَالُوٓاْ إِنۡ هَٰذَآ إِلَّا سِحۡرٞ مُّبِينٌ

15. አሉም: «ይህ ግልጽ ድግምት እንጂ ሌላ አይደለም።

15. አሉም: «ይህ ግልጽ ድግምት እንጂ ሌላ አይደለም።

أَءِذَا مِتۡنَا وَكُنَّا تُرَابٗا وَعِظَٰمًا أَءِنَّا لَمَبۡعُوثُونَ

16. «በሞትንና ዐፈርና አጥንቶችም በሆን ጊዜ የምንቀስቀስ ነን?

16. «በሞትንና ዐፈርና አጥንቶችም በሆን ጊዜ የምንቀስቀስ ነን?

أَوَءَابَآؤُنَا ٱلۡأَوَّلُونَ

17. «የቀድሞዎቹ አባቶቻችንም እንደዚሁ ይቀሰቀሳሉን?» (ይላሉ።)

17. «የቀድሞዎቹ አባቶቻችንም እንደዚሁ ይቀሰቀሳሉን?» (ይላሉ።)

قُلۡ نَعَمۡ وَأَنتُمۡ دَٰخِرُونَ

18. (መልዕክተኛችን ሙሐመድ ሆይ!) «አዎን! እናንተ ወራዶች ሆናችሁ (ትነሳላችሁ)።» በላቸው።

18. (መልዕክተኛችን ሙሐመድ ሆይ!) «አዎን! እናንተ ወራዶች ሆናችሁ (ትነሳላችሁ)።» በላቸው።

فَإِنَّمَا هِيَ زَجۡرَةٞ وَٰحِدَةٞ فَإِذَا هُمۡ يَنظُرُونَ

19. እርሷም አንዲት ጩኸት ብቻ ናት:: እነርሱም ወዲያውኑ ምን እንደሚፈጸምባቸው ያያሉ::

19. እርሷም አንዲት ጩኸት ብቻ ናት:: እነርሱም ወዲያውኑ ምን እንደሚፈጸምባቸው ያያሉ::

وَقَالُواْ يَٰوَيۡلَنَا هَٰذَا يَوۡمُ ٱلدِّينِ

20. «ዋ ጥፋታችን! ይህ የፍርዱ ቀን ነው።» (ይላሉም)

20. «ዋ ጥፋታችን! ይህ የፍርዱ ቀን ነው።» (ይላሉም)

هَٰذَا يَوۡمُ ٱلۡفَصۡلِ ٱلَّذِي كُنتُم بِهِۦ تُكَذِّبُونَ

21. «ይህ ያ በእርሱ ታስተባብሉት የነበራችት መለያው ቀን ነው።» ይባላሉ።

21. «ይህ ያ በእርሱ ታስተባብሉት የነበራችት መለያው ቀን ነው።» ይባላሉ።

۞ ٱحۡشُرُواْ ٱلَّذِينَ ظَلَمُواْ وَأَزۡوَٰجَهُمۡ وَمَا كَانُواْ يَعۡبُدُونَ

22. (ለመላዕክቶችም) «እነዚያን ነፍሶቻቸውን የበደሉትን ሰዎች ጓደኞቻቸውንም ከአላህ ሌላ ይገዟቸው የነበሩትንም ጣዖታት በአንድ ሰብስቡ።

22. (ለመላዕክቶችም) «እነዚያን ነፍሶቻቸውን የበደሉትን ሰዎች ጓደኞቻቸውንም ከአላህ ሌላ ይገዟቸው የነበሩትንም ጣዖታት በአንድ ሰብስቡ።

مِن دُونِ ٱللَّهِ فَٱهۡدُوهُمۡ إِلَىٰ صِرَٰطِ ٱلۡجَحِيمِ

23. ከአላህ ውጭ (ይገዟቸው የነበሩትን ሰብስቡ)። ከዚያም ወደ ገሀነም መንገድ ምሯቸው።

23. ከአላህ ውጭ (ይገዟቸው የነበሩትን ሰብስቡ)። ከዚያም ወደ ገሀነም መንገድ ምሯቸው።

وَقِفُوهُمۡۖ إِنَّهُم مَّسۡـُٔولُونَ

24. «እነርሱ ተጠያቂዎች ናቸውና አቁሟቸዉም።» (ይባላል።)

24. «እነርሱ ተጠያቂዎች ናቸውና አቁሟቸዉም።» (ይባላል።)

مَا لَكُمۡ لَا تَنَاصَرُونَ

25. ለነርሱም «ምን ሆናችሁ ነው የማትረዳዱት?» ይባላሉ።

25. ለነርሱም «ምን ሆናችሁ ነው የማትረዳዱት?» ይባላሉ።

بَلۡ هُمُ ٱلۡيَوۡمَ مُسۡتَسۡلِمُونَ

26. በእርግጥ እነርሱ ዛሬ እጃቸውን የሰጡ ማምለጫ የሌላቸው ወራዳዎች ናቸው::

26. በእርግጥ እነርሱ ዛሬ እጃቸውን የሰጡ ማምለጫ የሌላቸው ወራዳዎች ናቸው::

وَأَقۡبَلَ بَعۡضُهُمۡ عَلَىٰ بَعۡضٖ يَتَسَآءَلُونَ

27. እርስ በራሳቸውም የሚወቃቀሱም ሆነው ይመጣሉ።

27. እርስ በራሳቸውም የሚወቃቀሱም ሆነው ይመጣሉ።

قَالُوٓاْ إِنَّكُمۡ كُنتُمۡ تَأۡتُونَنَا عَنِ ٱلۡيَمِينِ

28. (ተከታዮቹ ለአስከታዮቻቸው) «እናንተ በጉልበት ትመጡብን ነበር» ይላሉ።

28. (ተከታዮቹ ለአስከታዮቻቸው) «እናንተ በጉልበት ትመጡብን ነበር» ይላሉ።

قَالُواْ بَل لَّمۡ تَكُونُواْ مُؤۡمِنِينَ

29. (አስከታዮቹም) ይላሉ፡- «አይደለም ፈጽሞ አማኞች አልነበራችሁም።

29. (አስከታዮቹም) ይላሉ፡- «አይደለም ፈጽሞ አማኞች አልነበራችሁም።

وَمَا كَانَ لَنَا عَلَيۡكُم مِّن سُلۡطَٰنِۭۖ بَلۡ كُنتُمۡ قَوۡمٗا طَٰغِينَ

30. «ለእኛም በናንተ ላይ ምንም ስልጣን አልነበረንም። በእርግጥ እናንተ ጠማሞች ህዝቦች ነበራችሁና ነው እንጂ።

30. «ለእኛም በናንተ ላይ ምንም ስልጣን አልነበረንም። በእርግጥ እናንተ ጠማሞች ህዝቦች ነበራችሁና ነው እንጂ።

فَحَقَّ عَلَيۡنَا قَوۡلُ رَبِّنَآۖ إِنَّا لَذَآئِقُونَ

31. «በእኛም ላይ የጌታችን ቃል የተረጋገጠብንና ሁላችንም ቅጣቱን ቀማሽ ነን።

31. «በእኛም ላይ የጌታችን ቃል የተረጋገጠብንና ሁላችንም ቅጣቱን ቀማሽ ነን።

فَأَغۡوَيۡنَٰكُمۡ إِنَّا كُنَّا غَٰوِينَ

32. «እኛ ጠማሞች ስለ ነበርን ወደ ጥመት ጠራናችሁም።» ይላሉ።

32. «እኛ ጠማሞች ስለ ነበርን ወደ ጥመት ጠራናችሁም።» ይላሉ።

فَإِنَّهُمۡ يَوۡمَئِذٖ فِي ٱلۡعَذَابِ مُشۡتَرِكُونَ

33. ስለዚህ እነርሱ በዚያ ቀን በቅጣቱ ተጋሪዎች ናቸው::

33. ስለዚህ እነርሱ በዚያ ቀን በቅጣቱ ተጋሪዎች ናቸው::

إِنَّا كَذَٰلِكَ نَفۡعَلُ بِٱلۡمُجۡرِمِينَ

34. እኛ በአመጸኞች ሁሉ እንደዚሁ እንሰራለን።

34. እኛ በአመጸኞች ሁሉ እንደዚሁ እንሰራለን።

إِنَّهُمۡ كَانُوٓاْ إِذَا قِيلَ لَهُمۡ لَآ إِلَٰهَ إِلَّا ٱللَّهُ يَسۡتَكۡبِرُونَ

35. እነርሱ «ከአላህ ሌላ ትክክለኛ አምላክ የለም» በተባሉ ጊዜ ይኮሩ ነበሩ።

35. እነርሱ «ከአላህ ሌላ ትክክለኛ አምላክ የለም» በተባሉ ጊዜ ይኮሩ ነበሩ።

وَيَقُولُونَ أَئِنَّا لَتَارِكُوٓاْ ءَالِهَتِنَا لِشَاعِرٖ مَّجۡنُونِۭ

36. «እኛ ለዕብድ ባለቅኔ ብለን አማልክቶቻችንን የምንተው ነን እንዴ?» ይሉ ነበር።

36. «እኛ ለዕብድ ባለቅኔ ብለን አማልክቶቻችንን የምንተው ነን እንዴ?» ይሉ ነበር።

بَلۡ جَآءَ بِٱلۡحَقِّ وَصَدَّقَ ٱلۡمُرۡسَلِينَ

37. አይደለም እውነቱን ሃይማኖት አመጣ፤ መልዕክተኞቹንም እውነተኝነታቸውን አረጋገጠ።

37. አይደለም እውነቱን ሃይማኖት አመጣ፤ መልዕክተኞቹንም እውነተኝነታቸውን አረጋገጠ።

إِنَّكُمۡ لَذَآئِقُواْ ٱلۡعَذَابِ ٱلۡأَلِيمِ

38. እናንተ አሳማሚውን ቅጣት እርግጥ ቀማሾች ናችሁ::

38. እናንተ አሳማሚውን ቅጣት እርግጥ ቀማሾች ናችሁ::

وَمَا تُجۡزَوۡنَ إِلَّا مَا كُنتُمۡ تَعۡمَلُونَ

39. ትሰሩትም የነበራችሁትን እንጂ ሌላን አትመነዱም::

39. ትሰሩትም የነበራችሁትን እንጂ ሌላን አትመነዱም::

إِلَّا عِبَادَ ٱللَّهِ ٱلۡمُخۡلَصِينَ

40. ግን ምርጥ የሆኑት የአላህ ባሮች ቅጣትን አይቀምሱም::

40. ግን ምርጥ የሆኑት የአላህ ባሮች ቅጣትን አይቀምሱም::

أُوْلَٰٓئِكَ لَهُمۡ رِزۡقٞ مَّعۡلُومٞ

41. እነዚያ ለእነርሱ የታወቀ ሲሳይ አለላቸው::

41. እነዚያ ለእነርሱ የታወቀ ሲሳይ አለላቸው::

فَوَٰكِهُ وَهُم مُّكۡرَمُونَ

42. ፍራፋሬዎች (አሉላቸው) እነርሱም የተከበሩ ናቸው::

42. ፍራፋሬዎች (አሉላቸው) እነርሱም የተከበሩ ናቸው::

فِي جَنَّٰتِ ٱلنَّعِيمِ

43. በድሎት ገነቶች ውስጥ::

43. በድሎት ገነቶች ውስጥ::

عَلَىٰ سُرُرٖ مُّتَقَٰبِلِينَ

44. ፊት ለፊት የሚተያዩ ሲሆኑ በአልጋዎች ላይ ይንፈላሰሳሉ::

44. ፊት ለፊት የሚተያዩ ሲሆኑ በአልጋዎች ላይ ይንፈላሰሳሉ::

يُطَافُ عَلَيۡهِم بِكَأۡسٖ مِّن مَّعِينِۭ

45. ከሚመነጭ ወይን ጠጅ በያዙ ብርጭቆ በእነርሱ ላይ ይዞርባቸዋል::

45. ከሚመነጭ ወይን ጠጅ በያዙ ብርጭቆ በእነርሱ ላይ ይዞርባቸዋል::

بَيۡضَآءَ لَذَّةٖ لِّلشَّٰرِبِينَ

46. ነጭ ለጠጪዎች ጣፋጭ ከሆነች፤

46. ነጭ ለጠጪዎች ጣፋጭ ከሆነች፤

لَا فِيهَا غَوۡلٞ وَلَا هُمۡ عَنۡهَا يُنزَفُونَ

47. በእርሷ ውስጥም የራስ ምታት የለባትም:: እነርሱም ከእርሷ የሚሰክሩ አይደሉም::

47. በእርሷ ውስጥም የራስ ምታት የለባትም:: እነርሱም ከእርሷ የሚሰክሩ አይደሉም::

وَعِندَهُمۡ قَٰصِرَٰتُ ٱلطَّرۡفِ عِينٞ

48. እነርሱ ዘንድ ዓይናቸውን በባሎቻቸው ላይ ብቻ አሳጣሪዎች የሆኑ ዓይናማ ሴቶች አሉ::

48. እነርሱ ዘንድ ዓይናቸውን በባሎቻቸው ላይ ብቻ አሳጣሪዎች የሆኑ ዓይናማ ሴቶች አሉ::

كَأَنَّهُنَّ بَيۡضٞ مَّكۡنُونٞ

49. እነርሱ ልክ የተሸፈነ (የሰጎን) እንቁላል ይመስላሉ::

49. እነርሱ ልክ የተሸፈነ (የሰጎን) እንቁላል ይመስላሉ::

فَأَقۡبَلَ بَعۡضُهُمۡ عَلَىٰ بَعۡضٖ يَتَسَآءَلُونَ

50. የሚጠያያቁም ሆነው ከፊላቸው ወደ ከፊሉ ይመጣሉ::

50. የሚጠያያቁም ሆነው ከፊላቸው ወደ ከፊሉ ይመጣሉ::

قَالَ قَآئِلٞ مِّنۡهُمۡ إِنِّي كَانَ لِي قَرِينٞ

51. ከእነርሱ የሆነ ተናጋሪ (እንዲህ) ይላል: «እኔ ጓደኛ ነበረኝ።

51. ከእነርሱ የሆነ ተናጋሪ (እንዲህ) ይላል: «እኔ ጓደኛ ነበረኝ።

يَقُولُ أَءِنَّكَ لَمِنَ ٱلۡمُصَدِّقِينَ

52. (እንዲህ) የሚል: ‹በእርግጥ አንተ ከሚያምኑት ነህን?

52. (እንዲህ) የሚል: ‹በእርግጥ አንተ ከሚያምኑት ነህን?

أَءِذَا مِتۡنَا وَكُنَّا تُرَابٗا وَعِظَٰمًا أَءِنَّا لَمَدِينُونَ

53. ‹በሞትንና ዐፈር አጥንቶችም በሆነ ጊዜ እኛ በእርግጥ እኛ እንመረመራለን?› የሚልም።

53. ‹በሞትንና ዐፈር አጥንቶችም በሆነ ጊዜ እኛ በእርግጥ እኛ እንመረመራለን?› የሚልም።

قَالَ هَلۡ أَنتُم مُّطَّلِعُونَ

54. እናንተ ተመልካቾች ናችሁን? ይላል::

54. እናንተ ተመልካቾች ናችሁን? ይላል::

فَٱطَّلَعَ فَرَءَاهُ فِي سَوَآءِ ٱلۡجَحِيمِ

55. ይመለከታልም በገሀነም መካከልም ጓደኛውን ያየዋል::

55. ይመለከታልም በገሀነም መካከልም ጓደኛውን ያየዋል::

قَالَ تَٱللَّهِ إِن كِدتَّ لَتُرۡدِينِ

56. ይላል «በአላህ እምላለሁ በእርግጥ ልታጠፋኝ ቀርበህ ነበር።

56. ይላል «በአላህ እምላለሁ በእርግጥ ልታጠፋኝ ቀርበህ ነበር።

وَلَوۡلَا نِعۡمَةُ رَبِّي لَكُنتُ مِنَ ٱلۡمُحۡضَرِينَ

57. «የጌታየም ጸጋ ባልነበረ ኖሮ ወደ እሳት ከሚቀርቡት እሆን ነበር።» (ይላል)

57. «የጌታየም ጸጋ ባልነበረ ኖሮ ወደ እሳት ከሚቀርቡት እሆን ነበር።» (ይላል)

أَفَمَا نَحۡنُ بِمَيِّتِينَ

58. (የገነት ሰዎች ይላሉ)፡ «እኛ የምንሞት ሰዎች አይደለንምን?»

58. (የገነት ሰዎች ይላሉ)፡ «እኛ የምንሞት ሰዎች አይደለንምን?»

إِلَّا مَوۡتَتَنَا ٱلۡأُولَىٰ وَمَا نَحۡنُ بِمُعَذَّبِينَ

59. «የመጀመሪያይቱ መሞታችን ብቻ ስትቀር እኛም የምንቀጣ አይደለንም» ይላሉ።

59. «የመጀመሪያይቱ መሞታችን ብቻ ስትቀር እኛም የምንቀጣ አይደለንም» ይላሉ።

إِنَّ هَٰذَا لَهُوَ ٱلۡفَوۡزُ ٱلۡعَظِيمُ

60.ይህ ለገነት ሰዎች የተወሳው እርሱ በእርግጥ ታላቅ እድል ነው::

60.ይህ ለገነት ሰዎች የተወሳው እርሱ በእርግጥ ታላቅ እድል ነው::

لِمِثۡلِ هَٰذَا فَلۡيَعۡمَلِ ٱلۡعَٰمِلُونَ

61. ለዚህ ብጤ ሰሪዎች ሁሉ ይስሩ::

61. ለዚህ ብጤ ሰሪዎች ሁሉ ይስሩ::

أَذَٰلِكَ خَيۡرٞ نُّزُلًا أَمۡ شَجَرَةُ ٱلزَّقُّومِ

62. በመስተንግዶነት ይህ ይበልጣልን? ወይስ የዘቁም ዛፍ?

62. በመስተንግዶነት ይህ ይበልጣልን? ወይስ የዘቁም ዛፍ?

إِنَّا جَعَلۡنَٰهَا فِتۡنَةٗ لِّلظَّٰلِمِينَ

63. እኛ ለበዳዮች ፈተና አድርገናታል።

63. እኛ ለበዳዮች ፈተና አድርገናታል።

إِنَّهَا شَجَرَةٞ تَخۡرُجُ فِيٓ أَصۡلِ ٱلۡجَحِيمِ

64. እርሷ ከገሀነም አዘቅት ውስጥ የምትወጣ ዛፍ ናት፤

64. እርሷ ከገሀነም አዘቅት ውስጥ የምትወጣ ዛፍ ናት፤

طَلۡعُهَا كَأَنَّهُۥ رُءُوسُ ٱلشَّيَٰطِينِ

65. እንቡጧ ልክ የሰይጣናት ራሶች ይመስላል::

65. እንቡጧ ልክ የሰይጣናት ራሶች ይመስላል::

فَإِنَّهُمۡ لَأٓكِلُونَ مِنۡهَا فَمَالِـُٔونَ مِنۡهَا ٱلۡبُطُونَ

66. እነርሱ ከእርሷ በይዎች ናቸው:: ሆዶችንም ከእርሷ ሞይዎች ናቸው::

66. እነርሱ ከእርሷ በይዎች ናቸው:: ሆዶችንም ከእርሷ ሞይዎች ናቸው::

ثُمَّ إِنَّ لَهُمۡ عَلَيۡهَا لَشَوۡبٗا مِّنۡ حَمِيمٖ

67. ከዚያ ለእነርሱ በእርሷ ላይ ከተኳሳ ውሃ ቅልቅልን መጠጥ አላቸው።

67. ከዚያ ለእነርሱ በእርሷ ላይ ከተኳሳ ውሃ ቅልቅልን መጠጥ አላቸው።

ثُمَّ إِنَّ مَرۡجِعَهُمۡ لَإِلَى ٱلۡجَحِيمِ

68. ከዚያም መመለሻቸው ወደ ተጋጋመች እሳት ነው::

68. ከዚያም መመለሻቸው ወደ ተጋጋመች እሳት ነው::

إِنَّهُمۡ أَلۡفَوۡاْ ءَابَآءَهُمۡ ضَآلِّينَ

69. እነርሱ አባቶቻቸውን የተሳሳቱ ሆነው አግኝተዋል።

69. እነርሱ አባቶቻቸውን የተሳሳቱ ሆነው አግኝተዋል።

فَهُمۡ عَلَىٰٓ ءَاثَٰرِهِمۡ يُهۡرَعُونَ

70. እነርሱም በፈለጎቻቸው ላይ ይገሰግሳሉና።

70. እነርሱም በፈለጎቻቸው ላይ ይገሰግሳሉና።

وَلَقَدۡ ضَلَّ قَبۡلَهُمۡ أَكۡثَرُ ٱلۡأَوَّلِينَ

71. ከእነርሱም በፊት የነበሩት የቀድሞዎቹ ህዝቦች አብዛሀኞቻቸው በእርግጥ ተሳስተዋል::

71. ከእነርሱም በፊት የነበሩት የቀድሞዎቹ ህዝቦች አብዛሀኞቻቸው በእርግጥ ተሳስተዋል::

وَلَقَدۡ أَرۡسَلۡنَا فِيهِم مُّنذِرِينَ

72. በውስጣቸዉም አስፈራሪዎችን በእርግጥ ልከናል::

72. በውስጣቸዉም አስፈራሪዎችን በእርግጥ ልከናል::

فَٱنظُرۡ كَيۡفَ كَانَ عَٰقِبَةُ ٱلۡمُنذَرِينَ

73. (መልዕክተኛችን ሙሐመድ ሆይ!) የተስፈራሪዎቹም መጨረሻ እንዴት እንደነበረ ተመልከት!

73. (መልዕክተኛችን ሙሐመድ ሆይ!) የተስፈራሪዎቹም መጨረሻ እንዴት እንደነበረ ተመልከት!

إِلَّا عِبَادَ ٱللَّهِ ٱلۡمُخۡلَصِينَ

74. ምርጥ የሆኑት የአላህ ባሮች ብቻ ሲቀሩ::

74. ምርጥ የሆኑት የአላህ ባሮች ብቻ ሲቀሩ::

وَلَقَدۡ نَادَىٰنَا نُوحٞ فَلَنِعۡمَ ٱلۡمُجِيبُونَ

75. ኑህም በእርግጥ ጠራን:: ምንኛ ያማርን ምላሽ ሰጪ ነን?

75. ኑህም በእርግጥ ጠራን:: ምንኛ ያማርን ምላሽ ሰጪ ነን?

وَنَجَّيۡنَٰهُ وَأَهۡلَهُۥ مِنَ ٱلۡكَرۡبِ ٱلۡعَظِيمِ

76. እርሱንም ቤተሰቦቹንም ከከባድ ጭንቅ አዳንን::

76. እርሱንም ቤተሰቦቹንም ከከባድ ጭንቅ አዳንን::

وَجَعَلۡنَا ذُرِّيَّتَهُۥ هُمُ ٱلۡبَاقِينَ

77. ዘሮቹንም እነርሱን ብቻ ቀሪዎች አደረግን::

77. ዘሮቹንም እነርሱን ብቻ ቀሪዎች አደረግን::

وَتَرَكۡنَا عَلَيۡهِ فِي ٱلۡأٓخِرِينَ

78. በእርሱም ላይ በኋለኞቹ ህዝቦች ውስጥ መልካምን ዝና ተውን::

78. በእርሱም ላይ በኋለኞቹ ህዝቦች ውስጥ መልካምን ዝና ተውን::

سَلَٰمٌ عَلَىٰ نُوحٖ فِي ٱلۡعَٰلَمِينَ

79. «በዓለማት ውስጥ ሰላም በኑህ ላይ ይሁን።»

79. «በዓለማት ውስጥ ሰላም በኑህ ላይ ይሁን።»

إِنَّا كَذَٰلِكَ نَجۡزِي ٱلۡمُحۡسِنِينَ

80. እኛ ልክ እንደዚሁ መልካም ሰሪዎችን እንመነዳለን::

80. እኛ ልክ እንደዚሁ መልካም ሰሪዎችን እንመነዳለን::

إِنَّهُۥ مِنۡ عِبَادِنَا ٱلۡمُؤۡمِنِينَ

81. እርሱ ከአማኞች ባሮቻችን ነውና::

81. እርሱ ከአማኞች ባሮቻችን ነውና::

ثُمَّ أَغۡرَقۡنَا ٱلۡأٓخَرِينَ

82. ከዚያም ሌሎችን አሰመጥን::

82. ከዚያም ሌሎችን አሰመጥን::

۞ وَإِنَّ مِن شِيعَتِهِۦ لَإِبۡرَٰهِيمَ

83. (መልዕክተኛችን ሙሐመድ ሆይ! ) ኢብራሂምም በእርግጥ ከወገኖቹ አንዱ ነው።

83. (መልዕክተኛችን ሙሐመድ ሆይ! ) ኢብራሂምም በእርግጥ ከወገኖቹ አንዱ ነው።

إِذۡ جَآءَ رَبَّهُۥ بِقَلۡبٖ سَلِيمٍ

84. ወደ ጌታው በቅን ልብ በመጣ ጊዜ የሆነውን (አስታውስ)::

84. ወደ ጌታው በቅን ልብ በመጣ ጊዜ የሆነውን (አስታውስ)::

إِذۡ قَالَ لِأَبِيهِ وَقَوۡمِهِۦ مَاذَا تَعۡبُدُونَ

85. ለአባቱና ለህዝቦቹ ባለ ጊዜ: «ምንን ትገዛላችሁ?

85. ለአባቱና ለህዝቦቹ ባለ ጊዜ: «ምንን ትገዛላችሁ?

أَئِفۡكًا ءَالِهَةٗ دُونَ ٱللَّهِ تُرِيدُونَ

86. «ለቅጥፈት ብላችሁ ከአላህ ሌላ አማልክትን ትሻላችሁን?

86. «ለቅጥፈት ብላችሁ ከአላህ ሌላ አማልክትን ትሻላችሁን?

فَمَا ظَنُّكُم بِرَبِّ ٱلۡعَٰلَمِينَ

87. «በዓለማቱ ጌታስ ሀሳባችሁ ምንድ ነው?።»

87. «በዓለማቱ ጌታስ ሀሳባችሁ ምንድ ነው?።»

فَنَظَرَ نَظۡرَةٗ فِي ٱلنُّجُومِ

88. በከዋክብት መመልከትን ተመለከተ::

88. በከዋክብት መመልከትን ተመለከተ::

فَقَالَ إِنِّي سَقِيمٞ

89. እኔ «በሽተኛ ነኝ» አለ።

89. እኔ «በሽተኛ ነኝ» አለ።

فَتَوَلَّوۡاْ عَنۡهُ مُدۡبِرِينَ

90. እነርሱም ከእርሱ የሸሹ ሆነው ሄዱ።

90. እነርሱም ከእርሱ የሸሹ ሆነው ሄዱ።

فَرَاغَ إِلَىٰٓ ءَالِهَتِهِمۡ فَقَالَ أَلَا تَأۡكُلُونَ

91. ከዚያ እሱ ወደ አማልዕክቶቻቸው ተዘነበለ፤ (እንዲህ) አለም፡- «አትበሉም እንዴ?

91. ከዚያ እሱ ወደ አማልዕክቶቻቸው ተዘነበለ፤ (እንዲህ) አለም፡- «አትበሉም እንዴ?

مَا لَكُمۡ لَا تَنطِقُونَ

92. «ምንም የማትናገሩበትስ ምን ምክኒያት አላችሁ?»

92. «ምንም የማትናገሩበትስ ምን ምክኒያት አላችሁ?»

فَرَاغَ عَلَيۡهِمۡ ضَرۡبَۢا بِٱلۡيَمِينِ

93. በቀኝ (እጁ) የሚመታቸዉም ሆኖ በእነርሱ ላይ በድብቅ ተዘነበለ::

93. በቀኝ (እጁ) የሚመታቸዉም ሆኖ በእነርሱ ላይ በድብቅ ተዘነበለ::

فَأَقۡبَلُوٓاْ إِلَيۡهِ يَزِفُّونَ

94. ወደ እርሱም ሰዎቹ እየሮጡ መጡ።

94. ወደ እርሱም ሰዎቹ እየሮጡ መጡ።

قَالَ أَتَعۡبُدُونَ مَا تَنۡحِتُونَ

95. አለ: «የምትጠርቡትን ትገዛላችሁን?

95. አለ: «የምትጠርቡትን ትገዛላችሁን?

وَٱللَّهُ خَلَقَكُمۡ وَمَا تَعۡمَلُونَ

96. «አላህ እናንተንም ሆነ የምትሰሩትን ሁሉ የፈጠረ ሲሆን» አላቸው።

96. «አላህ እናንተንም ሆነ የምትሰሩትን ሁሉ የፈጠረ ሲሆን» አላቸው።

قَالُواْ ٱبۡنُواْ لَهُۥ بُنۡيَٰنٗا فَأَلۡقُوهُ فِي ٱلۡجَحِيمِ

97. «ለእርሱም ግንብን ገንቡ በእሳት ነበልባል ውስጥ ጣሉትም።» አሉ።

97. «ለእርሱም ግንብን ገንቡ በእሳት ነበልባል ውስጥ ጣሉትም።» አሉ።

فَأَرَادُواْ بِهِۦ كَيۡدٗا فَجَعَلۡنَٰهُمُ ٱلۡأَسۡفَلِينَ

98. ለእርሱ ተንኮልን አስቡ ወራዶችም አደረግናቸው።

98. ለእርሱ ተንኮልን አስቡ ወራዶችም አደረግናቸው።

وَقَالَ إِنِّي ذَاهِبٌ إِلَىٰ رَبِّي سَيَهۡدِينِ

99. አለም፡- «እኔ ወደ ጌታየ ሂያጅ ነኝ፤ በእርግጥ ይመራኛልና።

99. አለም፡- «እኔ ወደ ጌታየ ሂያጅ ነኝ፤ በእርግጥ ይመራኛልና።

رَبِّ هَبۡ لِي مِنَ ٱلصَّٰلِحِينَ

100. «ጌታየ ሆይ! ከመልካሞቹ የሆነን (ልጅ) ስጠኝ።»

100. «ጌታየ ሆይ! ከመልካሞቹ የሆነን (ልጅ) ስጠኝ።»

فَبَشَّرۡنَٰهُ بِغُلَٰمٍ حَلِيمٖ

101. ታጋሽም በሆነ ልጅም አበሰርነው።

101. ታጋሽም በሆነ ልጅም አበሰርነው።

فَلَمَّا بَلَغَ مَعَهُ ٱلسَّعۡيَ قَالَ يَٰبُنَيَّ إِنِّيٓ أَرَىٰ فِي ٱلۡمَنَامِ أَنِّيٓ أَذۡبَحُكَ فَٱنظُرۡ مَاذَا تَرَىٰۚ قَالَ يَٰٓأَبَتِ ٱفۡعَلۡ مَا تُؤۡمَرُۖ سَتَجِدُنِيٓ إِن شَآءَ ٱللَّهُ مِنَ ٱلصَّٰبِرِينَ

102. ከእርሱ ጋርም (ለስራ) በደረሰ ጊዜ «ልጄ ሆይ! እኔ በህልሜ እኔ የማርድህ ሆኜ አያለሁ፤ ተመልከትም፤ ምን ትላለህ?» አለው። «አባቴ ሆይ! የታዘዝከውን ስራ፤ አላህ ቢሻ ከታጋሾች ሆኜ ታገኘኛለህ።» አለ።

102. ከእርሱ ጋርም (ለስራ) በደረሰ ጊዜ «ልጄ ሆይ! እኔ በህልሜ እኔ የማርድህ ሆኜ አያለሁ፤ ተመልከትም፤ ምን ትላለህ?» አለው። «አባቴ ሆይ! የታዘዝከውን ስራ፤ አላህ ቢሻ ከታጋሾች ሆኜ ታገኘኛለህ።» አለ።

فَلَمَّآ أَسۡلَمَا وَتَلَّهُۥ لِلۡجَبِينِ

103. ሁለቱም ትዕዛዙን በተቀበሉና በግንባሩም ጎን ላይ በጣለው ጊዜ (የሆነው ሆነ)::

103. ሁለቱም ትዕዛዙን በተቀበሉና በግንባሩም ጎን ላይ በጣለው ጊዜ (የሆነው ሆነ)::

وَنَٰدَيۡنَٰهُ أَن يَٰٓإِبۡرَٰهِيمُ

104. ጠራነዉም: «ኢብራሂም ሆይ!

104. ጠራነዉም: «ኢብራሂም ሆይ!

قَدۡ صَدَّقۡتَ ٱلرُّءۡيَآۚ إِنَّا كَذَٰلِكَ نَجۡزِي ٱلۡمُحۡسِنِينَ

105. «ራዕዩን በርግጥ እውን አደረግክ።» እኛ ልክ እንደዚሁ መልካም ሰሪዎችን እንመነዳለን።

105. «ራዕዩን በርግጥ እውን አደረግክ።» እኛ ልክ እንደዚሁ መልካም ሰሪዎችን እንመነዳለን።

إِنَّ هَٰذَا لَهُوَ ٱلۡبَلَٰٓؤُاْ ٱلۡمُبِينُ

106. ይህ እርሱ በእውነት ግልጽ ፈተና ነው::

106. ይህ እርሱ በእውነት ግልጽ ፈተና ነው::

وَفَدَيۡنَٰهُ بِذِبۡحٍ عَظِيمٖ

107. በታላቅ እርድም መስዕዋት ቤዛ አደረግንለት።

107. በታላቅ እርድም መስዕዋት ቤዛ አደረግንለት።

وَتَرَكۡنَا عَلَيۡهِ فِي ٱلۡأٓخِرِينَ

108. በእርሱም ላይ በኋለኞቹ ህዝቦች ውስጥ መልካም ዝናን አስቀረንለት::

108. በእርሱም ላይ በኋለኞቹ ህዝቦች ውስጥ መልካም ዝናን አስቀረንለት::

سَلَٰمٌ عَلَىٰٓ إِبۡرَٰهِيمَ

109. ሰላም በኢብራሂም ላይ ይሁን::

109. ሰላም በኢብራሂም ላይ ይሁን::

كَذَٰلِكَ نَجۡزِي ٱلۡمُحۡسِنِينَ

110. ልክ እንደዚሁ መልካም ሰሪዎችን ሁሉ እንመነዳለን::

110. ልክ እንደዚሁ መልካም ሰሪዎችን ሁሉ እንመነዳለን::

إِنَّهُۥ مِنۡ عِبَادِنَا ٱلۡمُؤۡمِنِينَ

111. እርሱ በእርግጥ ካመኑት ባሮቻችን ነው::

111. እርሱ በእርግጥ ካመኑት ባሮቻችን ነው::

وَبَشَّرۡنَٰهُ بِإِسۡحَٰقَ نَبِيّٗا مِّنَ ٱلصَّٰلِحِينَ

112. በኢስሐቅም አበሰርነው። ከመልካሞች የሆነ ነብይ ሲሆን::

112. በኢስሐቅም አበሰርነው። ከመልካሞች የሆነ ነብይ ሲሆን::

وَبَٰرَكۡنَا عَلَيۡهِ وَعَلَىٰٓ إِسۡحَٰقَۚ وَمِن ذُرِّيَّتِهِمَا مُحۡسِنٞ وَظَالِمٞ لِّنَفۡسِهِۦ مُبِينٞ

113. በእርሱና በኢስሐቅ ላይም ባረክን። ከሁለቱም ዘሮች በጎ ሰሪ አለ:: ነፍሱን በግልጽ በዳይም አለ::

113. በእርሱና በኢስሐቅ ላይም ባረክን። ከሁለቱም ዘሮች በጎ ሰሪ አለ:: ነፍሱን በግልጽ በዳይም አለ::

وَلَقَدۡ مَنَنَّا عَلَىٰ مُوسَىٰ وَهَٰرُونَ

114. በሙሳና በሀሩን ላይ በእርግጥ ለገስን::

114. በሙሳና በሀሩን ላይ በእርግጥ ለገስን::

وَنَجَّيۡنَٰهُمَا وَقَوۡمَهُمَا مِنَ ٱلۡكَرۡبِ ٱلۡعَظِيمِ

115. እነርሱንም ሆነ ህዝቦቻቸውንም ከታላቅ ጭንቅ አዳንን::

115. እነርሱንም ሆነ ህዝቦቻቸውንም ከታላቅ ጭንቅ አዳንን::

وَنَصَرۡنَٰهُمۡ فَكَانُواْ هُمُ ٱلۡغَٰلِبِينَ

116. ረዳናቸውናም እነርሱ አሸናፊዎቹ ሆኑ::

116. ረዳናቸውናም እነርሱ አሸናፊዎቹ ሆኑ::

وَءَاتَيۡنَٰهُمَا ٱلۡكِتَٰبَ ٱلۡمُسۡتَبِينَ

117. በጣም የተብራራውንም መጽሐፍ ሰጠናቸው::

117. በጣም የተብራራውንም መጽሐፍ ሰጠናቸው::

وَهَدَيۡنَٰهُمَا ٱلصِّرَٰطَ ٱلۡمُسۡتَقِيمَ

118. ቀጥተኛውንም መንገድ መራናቸው::

118. ቀጥተኛውንም መንገድ መራናቸው::

وَتَرَكۡنَا عَلَيۡهِمَا فِي ٱلۡأٓخِرِينَ

119. በሁለቱም ላይ በኋለኞቹ ህዝቦች ውስጥ መልካምን ዝናን ተውንላቸው::

119. በሁለቱም ላይ በኋለኞቹ ህዝቦች ውስጥ መልካምን ዝናን ተውንላቸው::

سَلَٰمٌ عَلَىٰ مُوسَىٰ وَهَٰرُونَ

120. ሰላም በሙሳና በሀሩን ላይ ይሁን::

120. ሰላም በሙሳና በሀሩን ላይ ይሁን::

إِنَّا كَذَٰلِكَ نَجۡزِي ٱلۡمُحۡسِنِينَ

121. እኛ ልክ እንደዚሁ በጎ አድራጊዎችን ሁሉ እንመነዳለን::

121. እኛ ልክ እንደዚሁ በጎ አድራጊዎችን ሁሉ እንመነዳለን::

إِنَّهُمَا مِنۡ عِبَادِنَا ٱلۡمُؤۡمِنِينَ

122. ሁለቱም በትክክል በአላህ ካመኑት ባሮቻችን ናቸው::

122. ሁለቱም በትክክል በአላህ ካመኑት ባሮቻችን ናቸው::

وَإِنَّ إِلۡيَاسَ لَمِنَ ٱلۡمُرۡسَلِينَ

123. ኢልያስም በእርግጥ ከመልዕክተኞቹ ነው።

123. ኢልያስም በእርግጥ ከመልዕክተኞቹ ነው።

إِذۡ قَالَ لِقَوۡمِهِۦٓ أَلَا تَتَّقُونَ

124. ለህዝቦቹም ባለ ጊዜ (አስታውስ) «አላህን አትፈሩምን?

124. ለህዝቦቹም ባለ ጊዜ (አስታውስ) «አላህን አትፈሩምን?

أَتَدۡعُونَ بَعۡلٗا وَتَذَرُونَ أَحۡسَنَ ٱلۡخَٰلِقِينَ

125. «ስዕልን ትገዛላችሁ? ከስዓሊዎቹ ሁሉ ይበልጥ በጣም አሳማሪ የሆነዉም አምላክ ትተዋላችሁን?

125. «ስዕልን ትገዛላችሁ? ከስዓሊዎቹ ሁሉ ይበልጥ በጣም አሳማሪ የሆነዉም አምላክ ትተዋላችሁን?

ٱللَّهَ رَبَّكُمۡ وَرَبَّ ءَابَآئِكُمُ ٱلۡأَوَّلِينَ

126. «አላህ ጌታችሁና የቀድሞዎቹ አባቶቻችሁንም ጌታ ትተዋላችሁን?»

126. «አላህ ጌታችሁና የቀድሞዎቹ አባቶቻችሁንም ጌታ ትተዋላችሁን?»

فَكَذَّبُوهُ فَإِنَّهُمۡ لَمُحۡضَرُونَ

127. አስተባበሉትም ስለዚህ እነርሱ ለቅጣት የሚጣዱ ናቸው::

127. አስተባበሉትም ስለዚህ እነርሱ ለቅጣት የሚጣዱ ናቸው::

إِلَّا عِبَادَ ٱللَّهِ ٱلۡمُخۡلَصِينَ

128. ንጹህ የተደረጉት የአላህ ባሮች ብቻ ሲቀሩ::

128. ንጹህ የተደረጉት የአላህ ባሮች ብቻ ሲቀሩ::

وَتَرَكۡنَا عَلَيۡهِ فِي ٱلۡأٓخِرِينَ

129. በእነርሱ ላይም በኋለኞቹ ህዝቦች ውስጥ መልካም ዝናን ተውንለት::

129. በእነርሱ ላይም በኋለኞቹ ህዝቦች ውስጥ መልካም ዝናን ተውንለት::

سَلَٰمٌ عَلَىٰٓ إِلۡ يَاسِينَ

130. ሰላም በኢልያስ ላይ ይሁን፤

130. ሰላም በኢልያስ ላይ ይሁን፤

إِنَّا كَذَٰلِكَ نَجۡزِي ٱلۡمُحۡسِنِينَ

131. እኛ ልክ እንደዚሁ መልካም ሰሪዎችን እንመነዳለን::

131. እኛ ልክ እንደዚሁ መልካም ሰሪዎችን እንመነዳለን::

إِنَّهُۥ مِنۡ عِبَادِنَا ٱلۡمُؤۡمِنِينَ

132. እርሱ በእርግጥ ከምዕመናን ባሮቻችን ነው::

132. እርሱ በእርግጥ ከምዕመናን ባሮቻችን ነው::

وَإِنَّ لُوطٗا لَّمِنَ ٱلۡمُرۡسَلِينَ

133. ሉጥም በእርግጥ ከመልዕክተኞቹ ነው::

133. ሉጥም በእርግጥ ከመልዕክተኞቹ ነው::

إِذۡ نَجَّيۡنَٰهُ وَأَهۡلَهُۥٓ أَجۡمَعِينَ

134. እርሱንና ቤተሰቦቹን ሁሉንም በአዳናቸው ጊዜ (የሆነዉን አስታውስ)::

134. እርሱንና ቤተሰቦቹን ሁሉንም በአዳናቸው ጊዜ (የሆነዉን አስታውስ)::

إِلَّا عَجُوزٗا فِي ٱلۡغَٰبِرِينَ

135. በቅጣቱ ውስጥ ከቀሪዎቹ የሆነችው አሮጊት ብቻ ስትቀር::

135. በቅጣቱ ውስጥ ከቀሪዎቹ የሆነችው አሮጊት ብቻ ስትቀር::

ثُمَّ دَمَّرۡنَا ٱلۡأٓخَرِينَ

136. ከዚያም ሌሎቹን አጠፋን::

136. ከዚያም ሌሎቹን አጠፋን::

وَإِنَّكُمۡ لَتَمُرُّونَ عَلَيۡهِم مُّصۡبِحِينَ

137. (መኮች ሆይ)፤ እናንተም በእነርሱ መኖሪያዎች ላይ ያነጋችሁ ስትሆኑ ታልፋላችሁ።

137. (መኮች ሆይ)፤ እናንተም በእነርሱ መኖሪያዎች ላይ ያነጋችሁ ስትሆኑ ታልፋላችሁ።

وَبِٱلَّيۡلِۚ أَفَلَا تَعۡقِلُونَ

138. በሌሊትም ታልፋላችሁ:: ልብ አታደርጉምን?

138. በሌሊትም ታልፋላችሁ:: ልብ አታደርጉምን?

وَإِنَّ يُونُسَ لَمِنَ ٱلۡمُرۡسَلِينَ

139. ዩኑስም በእርግጥ ከመልዕክተኞቹ ነው።

139. ዩኑስም በእርግጥ ከመልዕክተኞቹ ነው።

إِذۡ أَبَقَ إِلَى ٱلۡفُلۡكِ ٱلۡمَشۡحُونِ

140. ወደ ተሞላው መርከብ በኮበለለ ጊዜ አስታውስ::

140. ወደ ተሞላው መርከብ በኮበለለ ጊዜ አስታውስ::

فَسَاهَمَ فَكَانَ مِنَ ٱلۡمُدۡحَضِينَ

141. እጣም ተጣጣለ፤ ከተሸነፉትም ሆነ::

141. እጣም ተጣጣለ፤ ከተሸነፉትም ሆነ::

فَٱلۡتَقَمَهُ ٱلۡحُوتُ وَهُوَ مُلِيمٞ

142. እርሱም ተወቃሽ ሲሆን ዐሳ ነባሪው ዋጠው::

142. እርሱም ተወቃሽ ሲሆን ዐሳ ነባሪው ዋጠው::

فَلَوۡلَآ أَنَّهُۥ كَانَ مِنَ ٱلۡمُسَبِّحِينَ

143. እርሱ ለጌታው ከአወዳሾቹ ባልሆነ ኖሮ

143. እርሱ ለጌታው ከአወዳሾቹ ባልሆነ ኖሮ

لَلَبِثَ فِي بَطۡنِهِۦٓ إِلَىٰ يَوۡمِ يُبۡعَثُونَ

144. እስከሚቀሰቀሱበት ቀን ድረስ በሆዱ ውስጥ በቆየ ነበር::

144. እስከሚቀሰቀሱበት ቀን ድረስ በሆዱ ውስጥ በቆየ ነበር::

۞ فَنَبَذۡنَٰهُ بِٱلۡعَرَآءِ وَهُوَ سَقِيمٞ

145. እርሱ በሽተኛ ሆኖ በቃይ በሌለው ባህር ዳርቻ ላይ ጣልነዉም::

145. እርሱ በሽተኛ ሆኖ በቃይ በሌለው ባህር ዳርቻ ላይ ጣልነዉም::

وَأَنۢبَتۡنَا عَلَيۡهِ شَجَرَةٗ مِّن يَقۡطِينٖ

146. በእርሱም ላይ በአጠገቡ ከቅል የሆነችን ዛፍ አበቀልን::

146. በእርሱም ላይ በአጠገቡ ከቅል የሆነችን ዛፍ አበቀልን::

وَأَرۡسَلۡنَٰهُ إِلَىٰ مِاْئَةِ أَلۡفٍ أَوۡ يَزِيدُونَ

147. ወደ መቶ ሺህ ሰዎችም ላክነው፤ ከቶውንም ይጨምራሉ::

147. ወደ መቶ ሺህ ሰዎችም ላክነው፤ ከቶውንም ይጨምራሉ::

فَـَٔامَنُواْ فَمَتَّعۡنَٰهُمۡ إِلَىٰ حِينٖ

148. አመኑም። እስከ ጊዜው ድረስም አጣቀምናቸው::

148. አመኑም። እስከ ጊዜው ድረስም አጣቀምናቸው::

فَٱسۡتَفۡتِهِمۡ أَلِرَبِّكَ ٱلۡبَنَاتُ وَلَهُمُ ٱلۡبَنُونَ

149. (መልዕክተኛችን ሙሐመድ ሆይ!) የመካን ሰዎች ጠይቃቸዉም: «ለጌታህ ሴት ልጆች ለእነርሱም ወንዶች ልጆች ይኖራሉን?

149. (መልዕክተኛችን ሙሐመድ ሆይ!) የመካን ሰዎች ጠይቃቸዉም: «ለጌታህ ሴት ልጆች ለእነርሱም ወንዶች ልጆች ይኖራሉን?

أَمۡ خَلَقۡنَا ٱلۡمَلَٰٓئِكَةَ إِنَٰثٗا وَهُمۡ شَٰهِدُونَ

150. «ወይስ እኛ እነርሱ የተጣዱ ሆነው መላዕክትን ሴቶች አድርገን ፈጠርን?»

150. «ወይስ እኛ እነርሱ የተጣዱ ሆነው መላዕክትን ሴቶች አድርገን ፈጠርን?»

أَلَآ إِنَّهُم مِّنۡ إِفۡكِهِمۡ لَيَقُولُونَ

151. አስተውሉ! እነርሱ ከቅጥፈታቸው የተነሳ ይላሉ:

151. አስተውሉ! እነርሱ ከቅጥፈታቸው የተነሳ ይላሉ:

وَلَدَ ٱللَّهُ وَإِنَّهُمۡ لَكَٰذِبُونَ

152.፡- «አላህ መላዕክትን ወለደ።» እነርሱም በእርግጥ ውሸታሞች ናቸው።

152.፡- «አላህ መላዕክትን ወለደ።» እነርሱም በእርግጥ ውሸታሞች ናቸው።

أَصۡطَفَى ٱلۡبَنَاتِ عَلَى ٱلۡبَنِينَ

153. በወንዶች ልጆች ላይ ይልቅ ሴቶችን ልጆች መረጠን?

153. በወንዶች ልጆች ላይ ይልቅ ሴቶችን ልጆች መረጠን?

مَا لَكُمۡ كَيۡفَ تَحۡكُمُونَ

154. ለእናንተ ምን አስረጂ አላችሁ? እንዴት ትፈርዳላችሁ!

154. ለእናንተ ምን አስረጂ አላችሁ? እንዴት ትፈርዳላችሁ!

أَفَلَا تَذَكَّرُونَ

155. አትገነዘቡምን?

155. አትገነዘቡምን?

أَمۡ لَكُمۡ سُلۡطَٰنٞ مُّبِينٞ

156. ወይስ ለእናንተ ግልጽ አስረጂ አላችሁን?

156. ወይስ ለእናንተ ግልጽ አስረጂ አላችሁን?

فَأۡتُواْ بِكِتَٰبِكُمۡ إِن كُنتُمۡ صَٰدِقِينَ

157. «እውነተኞች እንደሆናችሁ መጽሐፋችሁን አምጡ» በላቸው።

157. «እውነተኞች እንደሆናችሁ መጽሐፋችሁን አምጡ» በላቸው።

وَجَعَلُواْ بَيۡنَهُۥ وَبَيۡنَ ٱلۡجِنَّةِ نَسَبٗاۚ وَلَقَدۡ عَلِمَتِ ٱلۡجِنَّةُ إِنَّهُمۡ لَمُحۡضَرُونَ

158. በአላህና በአጋንንት መካከልም ዝምድናን አደረጉ:: አጋንንትም ሆኑ ይህን ባዩች በእሳት የሚጣዱ መሆናቸውን በእርግጥ አውቀዋል::

158. በአላህና በአጋንንት መካከልም ዝምድናን አደረጉ:: አጋንንትም ሆኑ ይህን ባዩች በእሳት የሚጣዱ መሆናቸውን በእርግጥ አውቀዋል::

سُبۡحَٰنَ ٱللَّهِ عَمَّا يَصِفُونَ

159. አላህ ከሚመጥኑት ሁሉ ጠራ::

159. አላህ ከሚመጥኑት ሁሉ ጠራ::

إِلَّا عِبَادَ ٱللَّهِ ٱلۡمُخۡلَصِينَ

160. ግን የተመረጡት የአላህ ባሮች በአላህ ላይ አይዋሹም::

160. ግን የተመረጡት የአላህ ባሮች በአላህ ላይ አይዋሹም::

فَإِنَّكُمۡ وَمَا تَعۡبُدُونَ

161. (ካሐዲያን ሆይ!) እናንተም የምትገዟቸዉም ሁሉ፤

161. (ካሐዲያን ሆይ!) እናንተም የምትገዟቸዉም ሁሉ፤

مَآ أَنتُمۡ عَلَيۡهِ بِفَٰتِنِينَ

162. በእርሱ በአላህ ላይ አንድንም አጥማሚዎች አይደላችሁም

162. በእርሱ በአላህ ላይ አንድንም አጥማሚዎች አይደላችሁም

إِلَّا مَنۡ هُوَ صَالِ ٱلۡجَحِيمِ

163. ያንን እርሱ ገሀነም ገቢ የሆነውን ቢሆን እንጂ (አጥማሚዎች አይደላችሁም)።

163. ያንን እርሱ ገሀነም ገቢ የሆነውን ቢሆን እንጂ (አጥማሚዎች አይደላችሁም)።

وَمَا مِنَّآ إِلَّا لَهُۥ مَقَامٞ مَّعۡلُومٞ

164. (መላእክቶችም አሉ)? «ከእኛ አንድም የለም፤ ለእርሱ የታወቀ ደረጃ ያለው ቢሆን እንጅ።

164. (መላእክቶችም አሉ)? «ከእኛ አንድም የለም፤ ለእርሱ የታወቀ ደረጃ ያለው ቢሆን እንጅ።

وَإِنَّا لَنَحۡنُ ٱلصَّآفُّونَ

165. «እኛም ጌታን ለመገዛት ተሰላፊዎቹ እኛ ነን።

165. «እኛም ጌታን ለመገዛት ተሰላፊዎቹ እኛ ነን።

وَإِنَّا لَنَحۡنُ ٱلۡمُسَبِّحُونَ

166. «እኛም አላህን አጥሪዎቹ እኛው ነን።»

166. «እኛም አላህን አጥሪዎቹ እኛው ነን።»

وَإِن كَانُواْ لَيَقُولُونَ

167. (መልዕክተኛችን ሙሐመድ ሆይ!) እነርሱ (ከሓዲያን) በእርግጥ ይሉ ነበር:

167. (መልዕክተኛችን ሙሐመድ ሆይ!) እነርሱ (ከሓዲያን) በእርግጥ ይሉ ነበር:

لَوۡ أَنَّ عِندَنَا ذِكۡرٗا مِّنَ ٱلۡأَوَّلِينَ

168. «ከቀድሞዎቹ መጽሐፍ ገሳጭ መጽሐፍ እኛ ዘንድ በነበረ ኖሮ

168. «ከቀድሞዎቹ መጽሐፍ ገሳጭ መጽሐፍ እኛ ዘንድ በነበረ ኖሮ

لَكُنَّا عِبَادَ ٱللَّهِ ٱلۡمُخۡلَصِينَ

169. «የአላህ ምርጦች ባሮች በሆን ነበር።»

169. «የአላህ ምርጦች ባሮች በሆን ነበር።»

فَكَفَرُواْ بِهِۦۖ فَسَوۡفَ يَعۡلَمُونَ

170. ግን ቁርኣኑ በመጣላቸው ጊዜ በእርሱ ላይ ካዱ። ወደ ፊትም በእርግጥ ያውቃሉ::

170. ግን ቁርኣኑ በመጣላቸው ጊዜ በእርሱ ላይ ካዱ። ወደ ፊትም በእርግጥ ያውቃሉ::

وَلَقَدۡ سَبَقَتۡ كَلِمَتُنَا لِعِبَادِنَا ٱلۡمُرۡسَلِينَ

171. የእርዳታ ቃላችንም መልዕክተኞች ለሆኑት ባሮቻችን በእውነት አልፋለች::

171. የእርዳታ ቃላችንም መልዕክተኞች ለሆኑት ባሮቻችን በእውነት አልፋለች::

إِنَّهُمۡ لَهُمُ ٱلۡمَنصُورُونَ

172. እነርሱ ተረጂዎቹ እነርሱ ብቻ ናቸው::

172. እነርሱ ተረጂዎቹ እነርሱ ብቻ ናቸው::

وَإِنَّ جُندَنَا لَهُمُ ٱلۡغَٰلِبُونَ

173. ሰራዊቶቻችንም በእርግጥ አሸናፊዎቹ እነርሱ ናቸው::

173. ሰራዊቶቻችንም በእርግጥ አሸናፊዎቹ እነርሱ ናቸው::

فَتَوَلَّ عَنۡهُمۡ حَتَّىٰ حِينٖ

174. (መልዕክተኛችን ሙሐመድ ሆይ!) ከእነርሱም ከመካ ከሓዲያን እስከ ጥቂት ጊዜ ድረስ ዙር ተዋቸው::

174. (መልዕክተኛችን ሙሐመድ ሆይ!) ከእነርሱም ከመካ ከሓዲያን እስከ ጥቂት ጊዜ ድረስ ዙር ተዋቸው::

وَأَبۡصِرۡهُمۡ فَسَوۡفَ يُبۡصِرُونَ

175. ተመልከታቸዉም ወደፊትም የሚደርስባቸውን ያያሉ::

175. ተመልከታቸዉም ወደፊትም የሚደርስባቸውን ያያሉ::

أَفَبِعَذَابِنَا يَسۡتَعۡجِلُونَ

176. በቅጣታችንም ያቻኩሉናልን?

176. በቅጣታችንም ያቻኩሉናልን?

فَإِذَا نَزَلَ بِسَاحَتِهِمۡ فَسَآءَ صَبَاحُ ٱلۡمُنذَرِينَ

177. በቀያቸዉም በወረደ ጊዜ የተስፈራሪዎቹ ንጋት ከፋ!

177. በቀያቸዉም በወረደ ጊዜ የተስፈራሪዎቹ ንጋት ከፋ!

وَتَوَلَّ عَنۡهُمۡ حَتَّىٰ حِينٖ

178. (መልዕክተኛችን ሙሐመድ ሆይ!) እነርሱን እስከ ጥቂት ጊዜ ድረስ ተዋቸው::

178. (መልዕክተኛችን ሙሐመድ ሆይ!) እነርሱን እስከ ጥቂት ጊዜ ድረስ ተዋቸው::

وَأَبۡصِرۡ فَسَوۡفَ يُبۡصِرُونَ

179. ተመልከትም በእርግጥም ያያሉ::

179. ተመልከትም በእርግጥም ያያሉ::

سُبۡحَٰنَ رَبِّكَ رَبِّ ٱلۡعِزَّةِ عَمَّا يَصِفُونَ

180. (መልዕክተኛችን ሙሐመድ ሆይ!) የማሸነፍ ጌታ የሆነው ጌታህ ከሚሉት ሁሉ ጠራ::

180. (መልዕክተኛችን ሙሐመድ ሆይ!) የማሸነፍ ጌታ የሆነው ጌታህ ከሚሉት ሁሉ ጠራ::

وَسَلَٰمٌ عَلَى ٱلۡمُرۡسَلِينَ

181. በመልዕክተኞቹም ላይ ሰላም ይሁን::

181. በመልዕክተኞቹም ላይ ሰላም ይሁን::

وَٱلۡحَمۡدُ لِلَّهِ رَبِّ ٱلۡعَٰلَمِينَ

182. ምስጋና ሁሉም ለዓለማት ጌታ ለሆነው ለአላህ ብቻ ይገባው::

182. ምስጋና ሁሉም ለዓለማት ጌታ ለሆነው ለአላህ ብቻ ይገባው::
Footer Include