Header Include

Amharic translation - Africa Academy

Translated by Muhammad Zain Zahruddin. Published by Africa Academy

QR Code https://quran.islamcontent.com/ro/amharic_zain

عَبَسَ وَتَوَلَّىٰٓ

1. ፊቱን አጨፈገገ፤ ዞረም፤

1. ፊቱን አጨፈገገ፤ ዞረም፤

أَن جَآءَهُ ٱلۡأَعۡمَىٰ

2. ዓይነስውሩ ወደ እርሱ ስለመጣ።

2. ዓይነስውሩ ወደ እርሱ ስለመጣ።

وَمَا يُدۡرِيكَ لَعَلَّهُۥ يَزَّكَّىٰٓ

3. (መልዕክተኛችን ሙሐመድ ሆይ!) ምን ያሳውቅሃል? ምን አልባትም (ይህ አይነስውር ሰው ካንተ በሚሰማው ምክር ከኃጢአቶቹ) ሊጥራራ ይከጀላል::

3. (መልዕክተኛችን ሙሐመድ ሆይ!) ምን ያሳውቅሃል? ምን አልባትም (ይህ አይነስውር ሰው ካንተ በሚሰማው ምክር ከኃጢአቶቹ) ሊጥራራ ይከጀላል::

أَوۡ يَذَّكَّرُ فَتَنفَعَهُ ٱلذِّكۡرَىٰٓ

4. ወይም ሊገሰጽና ግሳጼይቱም ልትጠቅመው ይከጀላል::

4. ወይም ሊገሰጽና ግሳጼይቱም ልትጠቅመው ይከጀላል::

أَمَّا مَنِ ٱسۡتَغۡنَىٰ

5. ያ! ከአላህ የተብቃቃውን ሰውማ፤

5. ያ! ከአላህ የተብቃቃውን ሰውማ፤

فَأَنتَ لَهُۥ تَصَدَّىٰ

6. አንተ ለእርሱ ትዘጋጃለህ።

6. አንተ ለእርሱ ትዘጋጃለህ።

وَمَا عَلَيۡكَ أَلَّا يَزَّكَّىٰ

7. ባይጥራራ (ባያምን)፤ ባንተ ላይ ምንም የሌለብህ ስትሆን፤

7. ባይጥራራ (ባያምን)፤ ባንተ ላይ ምንም የሌለብህ ስትሆን፤

وَأَمَّا مَن جَآءَكَ يَسۡعَىٰ

8. ያ! እየገሰገሰ የመጣህ ሰውማ፤

8. ያ! እየገሰገሰ የመጣህ ሰውማ፤

وَهُوَ يَخۡشَىٰ

9. እርሱ አላህን የሚፈራ ሲሆን፤

9. እርሱ አላህን የሚፈራ ሲሆን፤

فَأَنتَ عَنۡهُ تَلَهَّىٰ

10. አንተ ከእርሱ ትዘናጋለህ::

10. አንተ ከእርሱ ትዘናጋለህ::

كَلَّآ إِنَّهَا تَذۡكِرَةٞ

11. ተከልከል፤ (ቁርኣን) ማስገንዘቢያ ነው::

11. ተከልከል፤ (ቁርኣን) ማስገንዘቢያ ነው::

فَمَن شَآءَ ذَكَرَهُۥ

12. የፈለገ ሰው ሁሉ (ቁርኣኑን) ያስታውሰዋል::

12. የፈለገ ሰው ሁሉ (ቁርኣኑን) ያስታውሰዋል::

فِي صُحُفٖ مُّكَرَّمَةٖ

13. በተከበሩት ጹሑፎች ውስጥ ነው::

13. በተከበሩት ጹሑፎች ውስጥ ነው::

مَّرۡفُوعَةٖ مُّطَهَّرَةِۭ

14. ከፍ በተደረገች፤ ንጹህም በተደረገች (ጹሑፍ ውስጥ ነው)።

14. ከፍ በተደረገች፤ ንጹህም በተደረገች (ጹሑፍ ውስጥ ነው)።

بِأَيۡدِي سَفَرَةٖ

15. በጸሐፊዎች መላዕክት እጆች (ንጹህ የተደረገ)::

15. በጸሐፊዎች መላዕክት እጆች (ንጹህ የተደረገ)::

كِرَامِۭ بَرَرَةٖ

16. የተከበሩና ታዛዦች በሆኑት ጸሐፊዎች (እጆች)፤

16. የተከበሩና ታዛዦች በሆኑት ጸሐፊዎች (እጆች)፤

قُتِلَ ٱلۡإِنسَٰنُ مَآ أَكۡفَرَهُۥ

17. ሰው ተረገመ። ምን ከሓዲ አደረገው?

17. ሰው ተረገመ። ምን ከሓዲ አደረገው?

مِنۡ أَيِّ شَيۡءٍ خَلَقَهُۥ

18. (ጌታው) ከምን ነገር ፈጠረው?

18. (ጌታው) ከምን ነገር ፈጠረው?

مِن نُّطۡفَةٍ خَلَقَهُۥ فَقَدَّرَهُۥ

19. (አያስብምን?) ከፍትወት ጠብታ ፈጠረው፤ መጠነዉም::

19. (አያስብምን?) ከፍትወት ጠብታ ፈጠረው፤ መጠነዉም::

ثُمَّ ٱلسَّبِيلَ يَسَّرَهُۥ

20. ከዚያም (መውጫ) መንገዱን አገራው::

20. ከዚያም (መውጫ) መንገዱን አገራው::

ثُمَّ أَمَاتَهُۥ فَأَقۡبَرَهُۥ

21. ከዚያም ገደለው:: እንዲቀበርም አደረገው፤

21. ከዚያም ገደለው:: እንዲቀበርም አደረገው፤

ثُمَّ إِذَا شَآءَ أَنشَرَهُۥ

22. ከዚያ ማንሳቱን በፈለገ ጊዜ ያስነሳዋል::

22. ከዚያ ማንሳቱን በፈለገ ጊዜ ያስነሳዋል::

كَلَّا لَمَّا يَقۡضِ مَآ أَمَرَهُۥ

23. በእውነት ያንን ጌታው ያዘዘውን ገና አልፈጸመም::

23. በእውነት ያንን ጌታው ያዘዘውን ገና አልፈጸመም::

فَلۡيَنظُرِ ٱلۡإِنسَٰنُ إِلَىٰ طَعَامِهِۦٓ

24. ሰው ወደ ምግቡ ይመልከት፤

24. ሰው ወደ ምግቡ ይመልከት፤

أَنَّا صَبَبۡنَا ٱلۡمَآءَ صَبّٗا

25. እኛ ውሃን ማንቧቧትን ያንቧቧን መሆናችንን፤

25. እኛ ውሃን ማንቧቧትን ያንቧቧን መሆናችንን፤

ثُمَّ شَقَقۡنَا ٱلۡأَرۡضَ شَقّٗا

26. ከዚያ ምድርን በደካማ ቡቃያ መሰንጠቅን የሰነጠቅን፤

26. ከዚያ ምድርን በደካማ ቡቃያ መሰንጠቅን የሰነጠቅን፤

فَأَنۢبَتۡنَا فِيهَا حَبّٗا

27. በውስጧም እህልን ያበቀልን

27. በውስጧም እህልን ያበቀልን

وَعِنَبٗا وَقَضۡبٗا

28. ወይንም እርጥብ ሳርንም፤

28. ወይንም እርጥብ ሳርንም፤

وَزَيۡتُونٗا وَنَخۡلٗا

29. የዘይት ወይራንም ዘንባባንም፤

29. የዘይት ወይራንም ዘንባባንም፤

وَحَدَآئِقَ غُلۡبٗا

30. ጭፍቆች አትክልቶችንም፤

30. ጭፍቆች አትክልቶችንም፤

وَفَٰكِهَةٗ وَأَبّٗا

31. ፍራፍሬንና፤ ገለባንም (ያበቀልን መሆናችንን ይመልከት)።

31. ፍራፍሬንና፤ ገለባንም (ያበቀልን መሆናችንን ይመልከት)።

مَّتَٰعٗا لَّكُمۡ وَلِأَنۡعَٰمِكُمۡ

32. ለእናንተም ለእንሰሶቻችሁም መጠቀሚያ ይሆን ዘንድ (ይህን ሰራን)::

32. ለእናንተም ለእንሰሶቻችሁም መጠቀሚያ ይሆን ዘንድ (ይህን ሰራን)::

فَإِذَا جَآءَتِ ٱلصَّآخَّةُ

33. አደንቋሪይቱ (መከራ) በመጣች ጊዜ፤

33. አደንቋሪይቱ (መከራ) በመጣች ጊዜ፤

يَوۡمَ يَفِرُّ ٱلۡمَرۡءُ مِنۡ أَخِيهِ

34. ሰው ከወንድሙ በሚሸሽበት ቀን፤

34. ሰው ከወንድሙ በሚሸሽበት ቀን፤

وَأُمِّهِۦ وَأَبِيهِ

35. ከእናቱም፤ ከአባቱም፤ (በሚሸሽበት ቀን)

35. ከእናቱም፤ ከአባቱም፤ (በሚሸሽበት ቀን)

وَصَٰحِبَتِهِۦ وَبَنِيهِ

36. ከሚስቱና ከልጁም፤ (በሚሸሽበት ቀን)

36. ከሚስቱና ከልጁም፤ (በሚሸሽበት ቀን)

لِكُلِّ ٱمۡرِيٕٖ مِّنۡهُمۡ يَوۡمَئِذٖ شَأۡنٞ يُغۡنِيهِ

37. ከእነርሱ ለየሰው ሁሉ በዚያ ቀን ከሌላው የሚያብቃቃው ሁኔታ አለው::

37. ከእነርሱ ለየሰው ሁሉ በዚያ ቀን ከሌላው የሚያብቃቃው ሁኔታ አለው::

وُجُوهٞ يَوۡمَئِذٖ مُّسۡفِرَةٞ

38. ፊቶች በዚያ ቀን አብሪዎች፤

38. ፊቶች በዚያ ቀን አብሪዎች፤

ضَاحِكَةٞ مُّسۡتَبۡشِرَةٞ

39. ሳቂዎችና ተደሳቾች ናቸው::

39. ሳቂዎችና ተደሳቾች ናቸው::

وَوُجُوهٞ يَوۡمَئِذٍ عَلَيۡهَا غَبَرَةٞ

40. ፊቶች ደግሞ በዚያ ቀን በላያቸው ላይ ትብያ አለባቸው።

40. ፊቶች ደግሞ በዚያ ቀን በላያቸው ላይ ትብያ አለባቸው።

تَرۡهَقُهَا قَتَرَةٌ

41. ጥቁረት ትሸፍናቸዋለች፤

41. ጥቁረት ትሸፍናቸዋለች፤

أُوْلَٰٓئِكَ هُمُ ٱلۡكَفَرَةُ ٱلۡفَجَرَةُ

42. እነዚያ እነርሱ በአላህ ከሓዲያን እና በትዕዛዙ ላይ አመጸኞቹ ናቸው።

42. እነዚያ እነርሱ በአላህ ከሓዲያን እና በትዕዛዙ ላይ አመጸኞቹ ናቸው።
Footer Include