Header Include

Amharic translation - Africa Academy

Translated by Muhammad Zain Zahruddin. Published by Africa Academy

QR Code https://quran.islamcontent.com/ro/amharic_zain

وَٱلَّيۡلِ إِذَا يَغۡشَىٰ

1. በሌሊቱ (ጨለማውን) በሚሸፍነው ጊዜ፤ (እምላለሁ)

1. በሌሊቱ (ጨለማውን) በሚሸፍነው ጊዜ፤ (እምላለሁ)

وَٱلنَّهَارِ إِذَا تَجَلَّىٰ

2. በቀኑም በተገለጸ ጊዜ፤

2. በቀኑም በተገለጸ ጊዜ፤

وَمَا خَلَقَ ٱلذَّكَرَ وَٱلۡأُنثَىٰٓ

3. ወንድንና ሴትን በፈጠረዉም (አምላክ) እምላለሁ::

3. ወንድንና ሴትን በፈጠረዉም (አምላክ) እምላለሁ::

إِنَّ سَعۡيَكُمۡ لَشَتَّىٰ

4. ስራችሁ በእርግጥ የተለያየ ነው።

4. ስራችሁ በእርግጥ የተለያየ ነው።

فَأَمَّا مَنۡ أَعۡطَىٰ وَٱتَّقَىٰ

5. ያ! የሰጠና ጌታውንም የፈራማ፤

5. ያ! የሰጠና ጌታውንም የፈራማ፤

وَصَدَّقَ بِٱلۡحُسۡنَىٰ

6. በመልካሚቱ እምነትም ያረጋገጠ ሰው

6. በመልካሚቱ እምነትም ያረጋገጠ ሰው

فَسَنُيَسِّرُهُۥ لِلۡيُسۡرَىٰ

7. ለገሪቱ እናገራዋለን።

7. ለገሪቱ እናገራዋለን።

وَأَمَّا مَنۢ بَخِلَ وَٱسۡتَغۡنَىٰ

8. ያ! የሰሰተ በራሱም የተብቃቃ፤

8. ያ! የሰሰተ በራሱም የተብቃቃ፤

وَكَذَّبَ بِٱلۡحُسۡنَىٰ

9. በመልካሚቱም ያስተባበለውማ

9. በመልካሚቱም ያስተባበለውማ

فَسَنُيَسِّرُهُۥ لِلۡعُسۡرَىٰ

10. ለክፋት እናዘጋጀዋለን።

10. ለክፋት እናዘጋጀዋለን።

وَمَا يُغۡنِي عَنۡهُ مَالُهُۥٓ إِذَا تَرَدَّىٰٓ

11. ገሀነም በወደቀ ጊዜ ያ! ገንዘቡ ከእርሱ ምንም አይጠቅመዉም።

11. ገሀነም በወደቀ ጊዜ ያ! ገንዘቡ ከእርሱ ምንም አይጠቅመዉም።

إِنَّ عَلَيۡنَا لَلۡهُدَىٰ

12. ቅኑን መንገድ መግለጽ በእኛ ላይ አለብን።

12. ቅኑን መንገድ መግለጽ በእኛ ላይ አለብን።

وَإِنَّ لَنَا لَلۡأٓخِرَةَ وَٱلۡأُولَىٰ

13. መጨረሻይቱም መጀመሪያይቱም ዓለም የእኛው ነው።

13. መጨረሻይቱም መጀመሪያይቱም ዓለም የእኛው ነው።

فَأَنذَرۡتُكُمۡ نَارٗا تَلَظَّىٰ

14. የምትንቀለቀል እሳት አስጠነቀቅኳችሁ።

14. የምትንቀለቀል እሳት አስጠነቀቅኳችሁ።

لَا يَصۡلَىٰهَآ إِلَّا ٱلۡأَشۡقَى

15. ከጠማማ በስተቀር የማይገባባትን

15. ከጠማማ በስተቀር የማይገባባትን

ٱلَّذِي كَذَّبَ وَتَوَلَّىٰ

16. ያ ያስተባበለና ከትዕዛዝም የሸሸ እድለ ቢስ (ነው የሚገባባት)።

16. ያ ያስተባበለና ከትዕዛዝም የሸሸ እድለ ቢስ (ነው የሚገባባት)።

وَسَيُجَنَّبُهَا ٱلۡأَتۡقَى

17. አላህን በጣም ፈሪ የሆነ በእርግጥ ይርቃታል::

17. አላህን በጣም ፈሪ የሆነ በእርግጥ ይርቃታል::

ٱلَّذِي يُؤۡتِي مَالَهُۥ يَتَزَكَّىٰ

18. ያ (ከወንጀል) የሚጥራራ ሲሆን ገንዘቡን የሚለግስ፤

18. ያ (ከወንጀል) የሚጥራራ ሲሆን ገንዘቡን የሚለግስ፤

وَمَا لِأَحَدٍ عِندَهُۥ مِن نِّعۡمَةٖ تُجۡزَىٰٓ

19. ለአንድም ሰው በእርሱ ዘንድ ተመላሽ የሚሆን ውለታ ሳይኖርበት።

19. ለአንድም ሰው በእርሱ ዘንድ ተመላሽ የሚሆን ውለታ ሳይኖርበት።

إِلَّا ٱبۡتِغَآءَ وَجۡهِ رَبِّهِ ٱلۡأَعۡلَىٰ

20. የታላቁን ጌታውን የአላህን ውዴታ በመፈለግ ብቻ (ይህንን የሰራ) ሲቀር።

20. የታላቁን ጌታውን የአላህን ውዴታ በመፈለግ ብቻ (ይህንን የሰራ) ሲቀር።

وَلَسَوۡفَ يَرۡضَىٰ

21. እርሱማ ወደ ፊት (በሚሰጠው) በእርግጥ ይደሰታል።

21. እርሱማ ወደ ፊት (በሚሰጠው) በእርግጥ ይደሰታል።
Footer Include