Amharic translation - Africa Academy
Translated by Muhammad Zain Zahruddin. Published by Africa Academy
وَٱلَّيۡلِ إِذَا يَغۡشَىٰ
1. በሌሊቱ (ጨለማውን) በሚሸፍነው ጊዜ፤ (እምላለሁ)
وَٱلنَّهَارِ إِذَا تَجَلَّىٰ
2. በቀኑም በተገለጸ ጊዜ፤
وَمَا خَلَقَ ٱلذَّكَرَ وَٱلۡأُنثَىٰٓ
3. ወንድንና ሴትን በፈጠረዉም (አምላክ) እምላለሁ::
إِنَّ سَعۡيَكُمۡ لَشَتَّىٰ
4. ስራችሁ በእርግጥ የተለያየ ነው።
فَأَمَّا مَنۡ أَعۡطَىٰ وَٱتَّقَىٰ
5. ያ! የሰጠና ጌታውንም የፈራማ፤
وَصَدَّقَ بِٱلۡحُسۡنَىٰ
6. በመልካሚቱ እምነትም ያረጋገጠ ሰው
فَسَنُيَسِّرُهُۥ لِلۡيُسۡرَىٰ
7. ለገሪቱ እናገራዋለን።
وَأَمَّا مَنۢ بَخِلَ وَٱسۡتَغۡنَىٰ
8. ያ! የሰሰተ በራሱም የተብቃቃ፤
وَكَذَّبَ بِٱلۡحُسۡنَىٰ
9. በመልካሚቱም ያስተባበለውማ
فَسَنُيَسِّرُهُۥ لِلۡعُسۡرَىٰ
10. ለክፋት እናዘጋጀዋለን።
وَمَا يُغۡنِي عَنۡهُ مَالُهُۥٓ إِذَا تَرَدَّىٰٓ
11. ገሀነም በወደቀ ጊዜ ያ! ገንዘቡ ከእርሱ ምንም አይጠቅመዉም።
إِنَّ عَلَيۡنَا لَلۡهُدَىٰ
12. ቅኑን መንገድ መግለጽ በእኛ ላይ አለብን።
وَإِنَّ لَنَا لَلۡأٓخِرَةَ وَٱلۡأُولَىٰ
13. መጨረሻይቱም መጀመሪያይቱም ዓለም የእኛው ነው።
فَأَنذَرۡتُكُمۡ نَارٗا تَلَظَّىٰ
14. የምትንቀለቀል እሳት አስጠነቀቅኳችሁ።
لَا يَصۡلَىٰهَآ إِلَّا ٱلۡأَشۡقَى
15. ከጠማማ በስተቀር የማይገባባትን
ٱلَّذِي كَذَّبَ وَتَوَلَّىٰ
16. ያ ያስተባበለና ከትዕዛዝም የሸሸ እድለ ቢስ (ነው የሚገባባት)።
وَسَيُجَنَّبُهَا ٱلۡأَتۡقَى
17. አላህን በጣም ፈሪ የሆነ በእርግጥ ይርቃታል::
ٱلَّذِي يُؤۡتِي مَالَهُۥ يَتَزَكَّىٰ
18. ያ (ከወንጀል) የሚጥራራ ሲሆን ገንዘቡን የሚለግስ፤
وَمَا لِأَحَدٍ عِندَهُۥ مِن نِّعۡمَةٖ تُجۡزَىٰٓ
19. ለአንድም ሰው በእርሱ ዘንድ ተመላሽ የሚሆን ውለታ ሳይኖርበት።
إِلَّا ٱبۡتِغَآءَ وَجۡهِ رَبِّهِ ٱلۡأَعۡلَىٰ
20. የታላቁን ጌታውን የአላህን ውዴታ በመፈለግ ብቻ (ይህንን የሰራ) ሲቀር።
وَلَسَوۡفَ يَرۡضَىٰ
21. እርሱማ ወደ ፊት (በሚሰጠው) በእርግጥ ይደሰታል።
مشاركة عبر