Header Include

Amharic translation - Africa Academy

Translated by Muhammad Zain Zahruddin. Published by Africa Academy

QR Code https://quran.islamcontent.com/ro/amharic_zain

لَمۡ يَكُنِ ٱلَّذِينَ كَفَرُواْ مِنۡ أَهۡلِ ٱلۡكِتَٰبِ وَٱلۡمُشۡرِكِينَ مُنفَكِّينَ حَتَّىٰ تَأۡتِيَهُمُ ٱلۡبَيِّنَةُ

1. ከመጽሐፍ ባለቤቶችና ከአጋሪዎች እነዚያ በአላህ የካዱት ሰዎች ግልጽ አስረጂ እስኪመጣላቸው ድረስ (ከነበሩበት አቋም) ተወጋጆች አልነበሩም::

1. ከመጽሐፍ ባለቤቶችና ከአጋሪዎች እነዚያ በአላህ የካዱት ሰዎች ግልጽ አስረጂ እስኪመጣላቸው ድረስ (ከነበሩበት አቋም) ተወጋጆች አልነበሩም::

رَسُولٞ مِّنَ ٱللَّهِ يَتۡلُواْ صُحُفٗا مُّطَهَّرَةٗ

2. (አስረጂውም) የተጥራሩ (መጽሐፎችን) የሚያነብ ከአላህ የሆነ መልዕክተኛ ነው።

2. (አስረጂውም) የተጥራሩ (መጽሐፎችን) የሚያነብ ከአላህ የሆነ መልዕክተኛ ነው።

فِيهَا كُتُبٞ قَيِّمَةٞ

3. በውስጧም ቀጥተኛ የሆኑ ጹሁፎች ያሉባት የሆነችን (አስረጂ)፤

3. በውስጧም ቀጥተኛ የሆኑ ጹሁፎች ያሉባት የሆነችን (አስረጂ)፤

وَمَا تَفَرَّقَ ٱلَّذِينَ أُوتُواْ ٱلۡكِتَٰبَ إِلَّا مِنۢ بَعۡدِ مَا جَآءَتۡهُمُ ٱلۡبَيِّنَةُ

4. እነዚያ መጽሐፉን የተሰጡ ሰዎችም ግልጽ አስረጂ ከመጣላቸው በኋላ እንጂ አልተለያዩም::

4. እነዚያ መጽሐፉን የተሰጡ ሰዎችም ግልጽ አስረጂ ከመጣላቸው በኋላ እንጂ አልተለያዩም::

وَمَآ أُمِرُوٓاْ إِلَّا لِيَعۡبُدُواْ ٱللَّهَ مُخۡلِصِينَ لَهُ ٱلدِّينَ حُنَفَآءَ وَيُقِيمُواْ ٱلصَّلَوٰةَ وَيُؤۡتُواْ ٱلزَّكَوٰةَۚ وَذَٰلِكَ دِينُ ٱلۡقَيِّمَةِ

5. ሃይማኖትን ለአላህ ብቻ አጥሪዎችና ቀጥተኞች ሆነው አላህን ሊገዙት፤ ሶላትንም አስተካክለው ሊሰግዱ፤ ዘካንም በትክክል ሊሰጡ እንጂ ያልታዘዙ ሲሆን ተለያዩ:: የቀጥተኛይቱ ሃይማኖት ድንጋጌም ይሀው ነው።

5. ሃይማኖትን ለአላህ ብቻ አጥሪዎችና ቀጥተኞች ሆነው አላህን ሊገዙት፤ ሶላትንም አስተካክለው ሊሰግዱ፤ ዘካንም በትክክል ሊሰጡ እንጂ ያልታዘዙ ሲሆን ተለያዩ:: የቀጥተኛይቱ ሃይማኖት ድንጋጌም ይሀው ነው።

إِنَّ ٱلَّذِينَ كَفَرُواْ مِنۡ أَهۡلِ ٱلۡكِتَٰبِ وَٱلۡمُشۡرِكِينَ فِي نَارِ جَهَنَّمَ خَٰلِدِينَ فِيهَآۚ أُوْلَٰٓئِكَ هُمۡ شَرُّ ٱلۡبَرِيَّةِ

6. ከመጽሐፉ ባለቤቶችና ከአጋሪዎች እነዚያ የካዱት በውስጧ ዘውታሪዎች በሚሆኑባት የገሀነም እሳት ውስጥ ናቸው:: እነዚያ ከፍጥረቱ ሁሉ መጥፎዎቹ እነርሱ ናቸው::

6. ከመጽሐፉ ባለቤቶችና ከአጋሪዎች እነዚያ የካዱት በውስጧ ዘውታሪዎች በሚሆኑባት የገሀነም እሳት ውስጥ ናቸው:: እነዚያ ከፍጥረቱ ሁሉ መጥፎዎቹ እነርሱ ናቸው::

إِنَّ ٱلَّذِينَ ءَامَنُواْ وَعَمِلُواْ ٱلصَّٰلِحَٰتِ أُوْلَٰٓئِكَ هُمۡ خَيۡرُ ٱلۡبَرِيَّةِ

7. እነዚያ በትክክል አምነው በጎ ተግባራትንም የሰሩት እነዚያ ከፍጥረት ሁሉ በላጭ (ምርጦች) የሆኑት እነርሱ ናቸው።

7. እነዚያ በትክክል አምነው በጎ ተግባራትንም የሰሩት እነዚያ ከፍጥረት ሁሉ በላጭ (ምርጦች) የሆኑት እነርሱ ናቸው።

جَزَآؤُهُمۡ عِندَ رَبِّهِمۡ جَنَّٰتُ عَدۡنٖ تَجۡرِي مِن تَحۡتِهَا ٱلۡأَنۡهَٰرُ خَٰلِدِينَ فِيهَآ أَبَدٗاۖ رَّضِيَ ٱللَّهُ عَنۡهُمۡ وَرَضُواْ عَنۡهُۚ ذَٰلِكَ لِمَنۡ خَشِيَ رَبَّهُۥ

8. ምንዳቸውም በስሮቻቸው ወንዞች የሚፈሱባቸው ከጌታቸው ዘንድ የሚቸሯቸው የመኖሪያ ገነቶች ናቸው። በውስጣቸው ለዘልዓለም ዘወታሪዎች ሲሆኑ ይገቡባቸዋል:: አላህ ከእነርሱ ስራቸውን ወደደላቸው:: እነርሱም ከእርሱ ምንዳውን ወደዱ:: ይህ እድል ጌታውን ለፈራ ሁሉ ነው::

8. ምንዳቸውም በስሮቻቸው ወንዞች የሚፈሱባቸው ከጌታቸው ዘንድ የሚቸሯቸው የመኖሪያ ገነቶች ናቸው። በውስጣቸው ለዘልዓለም ዘወታሪዎች ሲሆኑ ይገቡባቸዋል:: አላህ ከእነርሱ ስራቸውን ወደደላቸው:: እነርሱም ከእርሱ ምንዳውን ወደዱ:: ይህ እድል ጌታውን ለፈራ ሁሉ ነው::
Footer Include