Header Include

Amharic translation - Africa Academy

Translated by Muhammad Zain Zahruddin. Published by Africa Academy

QR Code https://quran.islamcontent.com/ro/amharic_zain

سَبِّحِ ٱسۡمَ رَبِّكَ ٱلۡأَعۡلَى

1. (መልዕክተኛችን ሙሐመድ ሆይ!) የዚያን ከሁሉ በላይ የሆነውን ጌታህን ስም አጥራ (አሞግስ)።

1. (መልዕክተኛችን ሙሐመድ ሆይ!) የዚያን ከሁሉ በላይ የሆነውን ጌታህን ስም አጥራ (አሞግስ)።

ٱلَّذِي خَلَقَ فَسَوَّىٰ

2. ያ ሁሉን ነገር የፈጠረውንና ያስተካከለውን፤

2. ያ ሁሉን ነገር የፈጠረውንና ያስተካከለውን፤

وَٱلَّذِي قَدَّرَ فَهَدَىٰ

3. ያን የወሰነውን ነገርንም ሁሉ ለተፈጠረለት የመራውን፤

3. ያን የወሰነውን ነገርንም ሁሉ ለተፈጠረለት የመራውን፤

وَٱلَّذِيٓ أَخۡرَجَ ٱلۡمَرۡعَىٰ

4. ያም ግጦሽን ለምለም አርጎ ያወጣውን፤

4. ያም ግጦሽን ለምለም አርጎ ያወጣውን፤

فَجَعَلَهُۥ غُثَآءً أَحۡوَىٰ

5.(ከዚያ) ደረቅ ጥቁር ያደረገውንም (አምላክ ስም አሞግስ)፡፡

5.(ከዚያ) ደረቅ ጥቁር ያደረገውንም (አምላክ ስም አሞግስ)፡፡

سَنُقۡرِئُكَ فَلَا تَنسَىٰٓ

6. (መልዕክተኛችን ሙሐመድ ሆይ!) ቁርኣንን በእርግጥ እናስነብብሃለን፤ አትረሳምም፤

6. (መልዕክተኛችን ሙሐመድ ሆይ!) ቁርኣንን በእርግጥ እናስነብብሃለን፤ አትረሳምም፤

إِلَّا مَا شَآءَ ٱللَّهُۚ إِنَّهُۥ يَعۡلَمُ ٱلۡجَهۡرَ وَمَا يَخۡفَىٰ

7. አላህ ከፈለገው ነገር በስተቀር፤ እናም እርሱ ግልጹንም የሚሸሽገውንም ሁሉ ያውቃልና፤

7. አላህ ከፈለገው ነገር በስተቀር፤ እናም እርሱ ግልጹንም የሚሸሽገውንም ሁሉ ያውቃልና፤

وَنُيَسِّرُكَ لِلۡيُسۡرَىٰ

8. ለገሪቱም (ሕይወት እስላምን ትከተል ዘንድ) እናገራሃለን።

8. ለገሪቱም (ሕይወት እስላምን ትከተል ዘንድ) እናገራሃለን።

فَذَكِّرۡ إِن نَّفَعَتِ ٱلذِّكۡرَىٰ

9. (ሰዎችንም) ገስፅ፤ ግሳፄይቱ ብትጠቅም።

9. (ሰዎችንም) ገስፅ፤ ግሳፄይቱ ብትጠቅም።

سَيَذَّكَّرُ مَن يَخۡشَىٰ

10. (አላህን) የሚፈራ በእርግጥ ይገሰፃል።

10. (አላህን) የሚፈራ በእርግጥ ይገሰፃል።

وَيَتَجَنَّبُهَا ٱلۡأَشۡقَى

11. መናጢዉም ይርቃታል::

11. መናጢዉም ይርቃታል::

ٱلَّذِي يَصۡلَى ٱلنَّارَ ٱلۡكُبۡرَىٰ

12. ያ! ታላቂቱን እሳት የሚገባው፤

12. ያ! ታላቂቱን እሳት የሚገባው፤

ثُمَّ لَا يَمُوتُ فِيهَا وَلَا يَحۡيَىٰ

13. ከዚያም በእርሷ ውስጥ የማይሞትና ህያዉም የማይሆነው።

13. ከዚያም በእርሷ ውስጥ የማይሞትና ህያዉም የማይሆነው።

قَدۡ أَفۡلَحَ مَن تَزَكَّىٰ

14. (አላህን ከማመፅ) የተጥራራ ሰው በእርግጥ ዳነ፤

14. (አላህን ከማመፅ) የተጥራራ ሰው በእርግጥ ዳነ፤

وَذَكَرَ ٱسۡمَ رَبِّهِۦ فَصَلَّىٰ

15. የጌታውንም ስም ያወሳና የሰገደ::

15. የጌታውንም ስም ያወሳና የሰገደ::

بَلۡ تُؤۡثِرُونَ ٱلۡحَيَوٰةَ ٱلدُّنۡيَا

16. ይልቁንም ቅርቢቱን ሕይወት ታስቀድማላችሁ፤

16. ይልቁንም ቅርቢቱን ሕይወት ታስቀድማላችሁ፤

وَٱلۡأٓخِرَةُ خَيۡرٞ وَأَبۡقَىٰٓ

17. (ሰዎች ሆይ!) መጨረሻይቱ ሕይወት በላጭና፤ ዘወታሪ ሆና ሳለ።

17. (ሰዎች ሆይ!) መጨረሻይቱ ሕይወት በላጭና፤ ዘወታሪ ሆና ሳለ።

إِنَّ هَٰذَا لَفِي ٱلصُّحُفِ ٱلۡأُولَىٰ

18. ይህ በቀደምቶቹም መጻሕፍት ውስጥ ያለ ነው።

18. ይህ በቀደምቶቹም መጻሕፍት ውስጥ ያለ ነው።

صُحُفِ إِبۡرَٰهِيمَ وَمُوسَىٰ

19. በኢብራሂምና በሙሳ መጽሐፍት ውስጥ የሰፈረ እውነታ ነው።

19. በኢብራሂምና በሙሳ መጽሐፍት ውስጥ የሰፈረ እውነታ ነው።
Footer Include