Header Include

Amharic translation - Africa Academy

Translated by Muhammad Zain Zahruddin. Published by Africa Academy

QR Code https://quran.islamcontent.com/ro/amharic_zain

ٱلۡحَآقَّةُ

1. እውነትን አረጋጋጪቱ (ትንሳኤ)::

1. እውነትን አረጋጋጪቱ (ትንሳኤ)::

مَا ٱلۡحَآقَّةُ

2. አረጋጋጪቱ (እርሷ) ምንድን ናት!

2. አረጋጋጪቱ (እርሷ) ምንድን ናት!

وَمَآ أَدۡرَىٰكَ مَا ٱلۡحَآقَّةُ

3. (መልዕክተኛችን ሙሐመድ ሆይ!) አረጋግጪቱም ምን እንደሆነች ምን አሳወቀህ?

3. (መልዕክተኛችን ሙሐመድ ሆይ!) አረጋግጪቱም ምን እንደሆነች ምን አሳወቀህ?

كَذَّبَتۡ ثَمُودُ وَعَادُۢ بِٱلۡقَارِعَةِ

4. የሰሙድና የዓድ ህዝቦች በቆርቋሪይቱ (ትንሳኤ) ቀን አስተባበሉ::

4. የሰሙድና የዓድ ህዝቦች በቆርቋሪይቱ (ትንሳኤ) ቀን አስተባበሉ::

فَأَمَّا ثَمُودُ فَأُهۡلِكُواْ بِٱلطَّاغِيَةِ

5. የሰሙድ ህዝቦችማ ወሰን በሌላት ነፋስ ጩኸት ተጠፉ::

5. የሰሙድ ህዝቦችማ ወሰን በሌላት ነፋስ ጩኸት ተጠፉ::

وَأَمَّا عَادٞ فَأُهۡلِكُواْ بِرِيحٖ صَرۡصَرٍ عَاتِيَةٖ

6. የዓድ ህዝቦችማ በኃይል በምትንሻሻ ብርቱ ነፋስ ተጠፉ::

6. የዓድ ህዝቦችማ በኃይል በምትንሻሻ ብርቱ ነፋስ ተጠፉ::

سَخَّرَهَا عَلَيۡهِمۡ سَبۡعَ لَيَالٖ وَثَمَٰنِيَةَ أَيَّامٍ حُسُومٗاۖ فَتَرَى ٱلۡقَوۡمَ فِيهَا صَرۡعَىٰ كَأَنَّهُمۡ أَعۡجَازُ نَخۡلٍ خَاوِيَةٖ

7. ተከታታይ በሆነ ሰባት ሌሊቶችና ስምንት ቀናቶች ውስጥ በእነርሱ ላይ ለቀቃት:: ህዝቦችንም፤ በውስጧ የተጣሉ ሆነው ልክ ክፍት እደሆኑ የበሰበሱ የዘንባባ ግንዶች ታያቸዋለህ::

7. ተከታታይ በሆነ ሰባት ሌሊቶችና ስምንት ቀናቶች ውስጥ በእነርሱ ላይ ለቀቃት:: ህዝቦችንም፤ በውስጧ የተጣሉ ሆነው ልክ ክፍት እደሆኑ የበሰበሱ የዘንባባ ግንዶች ታያቸዋለህ::

فَهَلۡ تَرَىٰ لَهُم مِّنۢ بَاقِيَةٖ

8. ከእነርሱ መካከል ቀሪን ታያለህን?

8. ከእነርሱ መካከል ቀሪን ታያለህን?

وَجَآءَ فِرۡعَوۡنُ وَمَن قَبۡلَهُۥ وَٱلۡمُؤۡتَفِكَٰتُ بِٱلۡخَاطِئَةِ

9. ፈርዖን፤ ከበፊቱ የነበሩትን ሰዎችም፤ ተገልባጮችም (የሉጥ ሰዎች ከተሞች) ኃጢአት ፈጸሙ።

9. ፈርዖን፤ ከበፊቱ የነበሩትን ሰዎችም፤ ተገልባጮችም (የሉጥ ሰዎች ከተሞች) ኃጢአት ፈጸሙ።

فَعَصَوۡاْ رَسُولَ رَبِّهِمۡ فَأَخَذَهُمۡ أَخۡذَةٗ رَّابِيَةً

10. የጌታቸውንም መልዕክተኛ ትዕዛዝ ጣሱ፤ የበረታችንም ቅጣት ቀጣቸው::

10. የጌታቸውንም መልዕክተኛ ትዕዛዝ ጣሱ፤ የበረታችንም ቅጣት ቀጣቸው::

إِنَّا لَمَّا طَغَا ٱلۡمَآءُ حَمَلۡنَٰكُمۡ فِي ٱلۡجَارِيَةِ

11. እኛ ውሃው ባየለ ጊዜ በተንሳፋፊይቱ ታንኳ ውስጥ ጫንናችሁ::

11. እኛ ውሃው ባየለ ጊዜ በተንሳፋፊይቱ ታንኳ ውስጥ ጫንናችሁ::

لِنَجۡعَلَهَا لَكُمۡ تَذۡكِرَةٗ وَتَعِيَهَآ أُذُنٞ وَٰعِيَةٞ

12. ይህንም ያደረግነው ለእናንተ መገሰጫ ልናደርጋትና አጥኚ የሆነችም ጆሮ ታጠናት ዘንድ ነው::

12. ይህንም ያደረግነው ለእናንተ መገሰጫ ልናደርጋትና አጥኚ የሆነችም ጆሮ ታጠናት ዘንድ ነው::

فَإِذَا نُفِخَ فِي ٱلصُّورِ نَفۡخَةٞ وَٰحِدَةٞ

13. በቀንዱ አንዲት መነፋት በተነፋች ጊዜ::

13. በቀንዱ አንዲት መነፋት በተነፋች ጊዜ::

وَحُمِلَتِ ٱلۡأَرۡضُ وَٱلۡجِبَالُ فَدُكَّتَا دَكَّةٗ وَٰحِدَةٗ

14. ምድርና ጋራዎች (ከየስፍራቸው) በተነሱና አንዲትን መሰባበር በተሰባበሩ ጊዜ፤

14. ምድርና ጋራዎች (ከየስፍራቸው) በተነሱና አንዲትን መሰባበር በተሰባበሩ ጊዜ፤

فَيَوۡمَئِذٖ وَقَعَتِ ٱلۡوَاقِعَةُ

15. በዚያ ቀን (ትንሳኤ) ትከሰታለች::

15. በዚያ ቀን (ትንሳኤ) ትከሰታለች::

وَٱنشَقَّتِ ٱلسَّمَآءُ فَهِيَ يَوۡمَئِذٖ وَاهِيَةٞ

16. ሰማይም ትቀደዳለች:: በመሆኑም እርሷ በዚያ ቀን ደካማ ናት፤

16. ሰማይም ትቀደዳለች:: በመሆኑም እርሷ በዚያ ቀን ደካማ ናት፤

وَٱلۡمَلَكُ عَلَىٰٓ أَرۡجَآئِهَاۚ وَيَحۡمِلُ عَرۡشَ رَبِّكَ فَوۡقَهُمۡ يَوۡمَئِذٖ ثَمَٰنِيَةٞ

17. መላዕክትም በየጫፎቿ ላይ ይሆናሉ:: የጌታህንም ዓርሽ በዚያ ቀን ስምንት መላዕክት ከበላያቸው ይሸከማሉ::

17. መላዕክትም በየጫፎቿ ላይ ይሆናሉ:: የጌታህንም ዓርሽ በዚያ ቀን ስምንት መላዕክት ከበላያቸው ይሸከማሉ::

يَوۡمَئِذٖ تُعۡرَضُونَ لَا تَخۡفَىٰ مِنكُمۡ خَافِيَةٞ

18. በዚያ ቀን ከናንተ ተደባቂ (ነገሮች) የማይደበቁ ሲሆኑ ትቀረባላችሁ::

18. በዚያ ቀን ከናንተ ተደባቂ (ነገሮች) የማይደበቁ ሲሆኑ ትቀረባላችሁ::

فَأَمَّا مَنۡ أُوتِيَ كِتَٰبَهُۥ بِيَمِينِهِۦ فَيَقُولُ هَآؤُمُ ٱقۡرَءُواْ كِتَٰبِيَهۡ

19. ያ መጽሀፉን በቀኝ እጁ የተሰጠ ሰውማ (ለጓደኞቹ እንዲህ) ይላል: «እንኩ መጽሐፌን አንብቡ፤

19. ያ መጽሀፉን በቀኝ እጁ የተሰጠ ሰውማ (ለጓደኞቹ እንዲህ) ይላል: «እንኩ መጽሐፌን አንብቡ፤

إِنِّي ظَنَنتُ أَنِّي مُلَٰقٍ حِسَابِيَهۡ

20. «እኔ ምርመራየን የምገናኝ መሆኔን አረጋገጥኩ።» (ይላል)

20. «እኔ ምርመራየን የምገናኝ መሆኔን አረጋገጥኩ።» (ይላል)

فَهُوَ فِي عِيشَةٖ رَّاضِيَةٖ

21. እርሱም በተወደደች ኑሮ ውስጥ ይሆናል::

21. እርሱም በተወደደች ኑሮ ውስጥ ይሆናል::

فِي جَنَّةٍ عَالِيَةٖ

22. በከፍተኛይቱ ገነት ውስጥ፤

22. በከፍተኛይቱ ገነት ውስጥ፤

قُطُوفُهَا دَانِيَةٞ

23. ፍሬዎቿ ቅርቦች የሆኑ::

23. ፍሬዎቿ ቅርቦች የሆኑ::

كُلُواْ وَٱشۡرَبُواْ هَنِيٓـَٔۢا بِمَآ أَسۡلَفۡتُمۡ فِي ٱلۡأَيَّامِ ٱلۡخَالِيَةِ

24. በአለፉት ቀናት ውስጥ (በምድረ ዓለም) ባስቀደማችሁት ምክንያት ብሉ፤ ጠጡም ይባላሉ::

24. በአለፉት ቀናት ውስጥ (በምድረ ዓለም) ባስቀደማችሁት ምክንያት ብሉ፤ ጠጡም ይባላሉ::

وَأَمَّا مَنۡ أُوتِيَ كِتَٰبَهُۥ بِشِمَالِهِۦ فَيَقُولُ يَٰلَيۡتَنِي لَمۡ أُوتَ كِتَٰبِيَهۡ

25. ያ መጽሐፉን በግራው የተሰጠ ሰው ደግሞ (እንዲህ) ይላል: «ዋ ጥፋቴ ምነው መጽሐፌን ባልተሰጠሁ፤

25. ያ መጽሐፉን በግራው የተሰጠ ሰው ደግሞ (እንዲህ) ይላል: «ዋ ጥፋቴ ምነው መጽሐፌን ባልተሰጠሁ፤

وَلَمۡ أَدۡرِ مَا حِسَابِيَهۡ

26. «ምርመራዬም ምን እንደሆነ ባላወቅሁ፤

26. «ምርመራዬም ምን እንደሆነ ባላወቅሁ፤

يَٰلَيۡتَهَا كَانَتِ ٱلۡقَاضِيَةَ

27. «ሞት ምነው የህይወቴ የመጨረሻ ፍፃሜ በሆነች፤

27. «ሞት ምነው የህይወቴ የመጨረሻ ፍፃሜ በሆነች፤

مَآ أَغۡنَىٰ عَنِّي مَالِيَهۡۜ

28. «ገንዘቤ ከእኔ ምንንም አልጠቀመኝም፤

28. «ገንዘቤ ከእኔ ምንንም አልጠቀመኝም፤

هَلَكَ عَنِّي سُلۡطَٰنِيَهۡ

29. «ስልጣኔ ከእኔ ላይ ጠፋ» ይላል::

29. «ስልጣኔ ከእኔ ላይ ጠፋ» ይላል::

خُذُوهُ فَغُلُّوهُ

30. ያዙት ከዚያ እጁን ከአንገቱ ጋር እሰሩት፤

30. ያዙት ከዚያ እጁን ከአንገቱ ጋር እሰሩት፤

ثُمَّ ٱلۡجَحِيمَ صَلُّوهُ

31. ከዚያ በእሳት ውስጥ አስገቡት፤

31. ከዚያ በእሳት ውስጥ አስገቡት፤

ثُمَّ فِي سِلۡسِلَةٖ ذَرۡعُهَا سَبۡعُونَ ذِرَاعٗا فَٱسۡلُكُوهُ

32. ከዚም እርዝመቷ ሰባ ክንድ በሆነች ሰንሰለት ውስጥ አስገቡት።

32. ከዚም እርዝመቷ ሰባ ክንድ በሆነች ሰንሰለት ውስጥ አስገቡት።

إِنَّهُۥ كَانَ لَا يُؤۡمِنُ بِٱللَّهِ ٱلۡعَظِيمِ

33. እርሱ ታላቅ በሆነው አላህ አያምንም ነበርና፤

33. እርሱ ታላቅ በሆነው አላህ አያምንም ነበርና፤

وَلَا يَحُضُّ عَلَىٰ طَعَامِ ٱلۡمِسۡكِينِ

34. ድሆችንም በማብላት ላይ አያነሳሳም ነበርና::

34. ድሆችንም በማብላት ላይ አያነሳሳም ነበርና::

فَلَيۡسَ لَهُ ٱلۡيَوۡمَ هَٰهُنَا حَمِيمٞ

35. ለእርሱ ዛሬ እዚህ ቦታ ዘመድ ማንም የለዉም::

35. ለእርሱ ዛሬ እዚህ ቦታ ዘመድ ማንም የለዉም::

وَلَا طَعَامٌ إِلَّا مِنۡ غِسۡلِينٖ

36. ምግብም ከእሳት ሰዎች ቁስል እጣቢ እዥ በስተቀር የለዉም::

36. ምግብም ከእሳት ሰዎች ቁስል እጣቢ እዥ በስተቀር የለዉም::

لَّا يَأۡكُلُهُۥٓ إِلَّا ٱلۡخَٰطِـُٔونَ

37. ይህን ምግብ ኃጢአተኞች እንጂ ሌላ አይበላዉም ይባላል::

37. ይህን ምግብ ኃጢአተኞች እንጂ ሌላ አይበላዉም ይባላል::

فَلَآ أُقۡسِمُ بِمَا تُبۡصِرُونَ

38. በምታዩት ነገር ሁሉ እምላለሁ ::

38. በምታዩት ነገር ሁሉ እምላለሁ ::

وَمَا لَا تُبۡصِرُونَ

39. በማታዩትም ነገር ሁሉ እምላለሁ ::

39. በማታዩትም ነገር ሁሉ እምላለሁ ::

إِنَّهُۥ لَقَوۡلُ رَسُولٖ كَرِيمٖ

40. ቁርኣን የተከበረው መልዕክተኛ ቃል ነው።

40. ቁርኣን የተከበረው መልዕክተኛ ቃል ነው።

وَمَا هُوَ بِقَوۡلِ شَاعِرٖۚ قَلِيلٗا مَّا تُؤۡمِنُونَ

41. እርሱም የባለ ቅኔ ገጣሚ ቃል አይደለም:: ጥቂትን ብቻ ታምናላችሁ::

41. እርሱም የባለ ቅኔ ገጣሚ ቃል አይደለም:: ጥቂትን ብቻ ታምናላችሁ::

وَلَا بِقَوۡلِ كَاهِنٖۚ قَلِيلٗا مَّا تَذَكَّرُونَ

42. የጠንቋይም ቃል አይደለም:: ጥቂትን ብቻ ታስታውሳላችሁ::

42. የጠንቋይም ቃል አይደለም:: ጥቂትን ብቻ ታስታውሳላችሁ::

تَنزِيلٞ مِّن رَّبِّ ٱلۡعَٰلَمِينَ

43. ከዓለማት ጌታ የተወረደ ነው::

43. ከዓለማት ጌታ የተወረደ ነው::

وَلَوۡ تَقَوَّلَ عَلَيۡنَا بَعۡضَ ٱلۡأَقَاوِيلِ

44. በእኛ ላይም ከፊልን ቃላት እንኳን (ያላልነው) በቀጠፈ ኖሮ፤

44. በእኛ ላይም ከፊልን ቃላት እንኳን (ያላልነው) በቀጠፈ ኖሮ፤

لَأَخَذۡنَا مِنۡهُ بِٱلۡيَمِينِ

45. በኃይል በቀጣነው ነበር::

45. በኃይል በቀጣነው ነበር::

ثُمَّ لَقَطَعۡنَا مِنۡهُ ٱلۡوَتِينَ

46. ከዚያ ከእርሱ የልቡን ስር የተንጠላጠለበትን (ጅማት) በቆረጥን ነበር::

46. ከዚያ ከእርሱ የልቡን ስር የተንጠላጠለበትን (ጅማት) በቆረጥን ነበር::

فَمَا مِنكُم مِّنۡ أَحَدٍ عَنۡهُ حَٰجِزِينَ

47. ከናንተም ውስጥ ከእርሱ ላይ ከልካዮች ምንም አይኖሩም።

47. ከናንተም ውስጥ ከእርሱ ላይ ከልካዮች ምንም አይኖሩም።

وَإِنَّهُۥ لَتَذۡكِرَةٞ لِّلۡمُتَّقِينَ

48. እርሱ (ቁርኣን) ለጥንቅቆቹ ብቻ መገሰጫ ነው::

48. እርሱ (ቁርኣን) ለጥንቅቆቹ ብቻ መገሰጫ ነው::

وَإِنَّا لَنَعۡلَمُ أَنَّ مِنكُم مُّكَذِّبِينَ

49. እኛም ከናንተ ውስጥ አስተባባዩች መኖራቸውን በእርግጥ እናውቃለን::

49. እኛም ከናንተ ውስጥ አስተባባዩች መኖራቸውን በእርግጥ እናውቃለን::

وَإِنَّهُۥ لَحَسۡرَةٌ عَلَى ٱلۡكَٰفِرِينَ

50. እርሱ (ቁርኣንም) በከሓዲያን ላይ ጸጸት ነው::

50. እርሱ (ቁርኣንም) በከሓዲያን ላይ ጸጸት ነው::

وَإِنَّهُۥ لَحَقُّ ٱلۡيَقِينِ

51. እርሱም የተረጋገጠ እውነት ነው::

51. እርሱም የተረጋገጠ እውነት ነው::

فَسَبِّحۡ بِٱسۡمِ رَبِّكَ ٱلۡعَظِيمِ

52. እናም የታላቁን ጌታህን ስም (ታላቁን ጌታህን) አጥራው::

52. እናም የታላቁን ጌታህን ስም (ታላቁን ጌታህን) አጥራው::
Footer Include