Header Include

Amharic translation - Africa Academy

Translated by Muhammad Zain Zahruddin. Published by Africa Academy

QR Code https://quran.islamcontent.com/aa/amharic_zain

حمٓ

1. ሓ፤ ሚይም፤

1. ሓ፤ ሚይም፤

وَٱلۡكِتَٰبِ ٱلۡمُبِينِ

2. ሁሉን ነገር አብራሪ በሆነው መጽሐፍ እንምላለን::

2. ሁሉን ነገር አብራሪ በሆነው መጽሐፍ እንምላለን::

إِنَّآ أَنزَلۡنَٰهُ فِي لَيۡلَةٖ مُّبَٰرَكَةٍۚ إِنَّا كُنَّا مُنذِرِينَ

3. እኛ ቁርኣኑን በዚያች በተባረከችው ሌሊት ውስጥ አወረድነው:: እኛ አስፈራሪዎች ነበርንና::

3. እኛ ቁርኣኑን በዚያች በተባረከችው ሌሊት ውስጥ አወረድነው:: እኛ አስፈራሪዎች ነበርንና::

فِيهَا يُفۡرَقُ كُلُّ أَمۡرٍ حَكِيمٍ

4. በውስጧ የተወሰነው ነገር ሁሉ ይለያል::

4. በውስጧ የተወሰነው ነገር ሁሉ ይለያል::

أَمۡرٗا مِّنۡ عِندِنَآۚ إِنَّا كُنَّا مُرۡسِلِينَ

5. ከእኛ ዘንድ የሆነ ትዕዛዝ ሲሆን አወረድነው:: እኛ መልዕክተኞችን ላኪዎች ነበርንና::

5. ከእኛ ዘንድ የሆነ ትዕዛዝ ሲሆን አወረድነው:: እኛ መልዕክተኞችን ላኪዎች ነበርንና::

رَحۡمَةٗ مِّن رَّبِّكَۚ إِنَّهُۥ هُوَ ٱلسَّمِيعُ ٱلۡعَلِيمُ

6. (መልዕክተኞች) ከጌታህ በሆነው ችሮታ (ተላኩ)። እነሆ እርሱ(አላህ) የሚባለዉን ሁሉ ሰሚና ሁሉን አዋቂ ነውና::

6. (መልዕክተኞች) ከጌታህ በሆነው ችሮታ (ተላኩ)። እነሆ እርሱ(አላህ) የሚባለዉን ሁሉ ሰሚና ሁሉን አዋቂ ነውና::

رَبِّ ٱلسَّمَٰوَٰتِ وَٱلۡأَرۡضِ وَمَا بَيۡنَهُمَآۖ إِن كُنتُم مُّوقِنِينَ

7. የሰማያት፤ የምድር እና በመካከላቸው ያሉ ነገሮች ሁሉ ጌታ ከሆነው (ተላኩ)። የምታረጋግጡ እንደሆናችሁ (ነገሩ እንዳልነው መሆኑን እወቁ)::

7. የሰማያት፤ የምድር እና በመካከላቸው ያሉ ነገሮች ሁሉ ጌታ ከሆነው (ተላኩ)። የምታረጋግጡ እንደሆናችሁ (ነገሩ እንዳልነው መሆኑን እወቁ)::

لَآ إِلَٰهَ إِلَّا هُوَ يُحۡيِۦ وَيُمِيتُۖ رَبُّكُمۡ وَرَبُّ ءَابَآئِكُمُ ٱلۡأَوَّلِينَ

8. ከእርሱም ሌላ አምላክ የለም። ህያው ያደርጋል። ህይወትም ይነሳል። ጌታችሁ የመጀመሪያዎቹ አባቶቻችሁም ጌታ ነው::

8. ከእርሱም ሌላ አምላክ የለም። ህያው ያደርጋል። ህይወትም ይነሳል። ጌታችሁ የመጀመሪያዎቹ አባቶቻችሁም ጌታ ነው::

بَلۡ هُمۡ فِي شَكّٖ يَلۡعَبُونَ

9. በእውነቱ እነርሱ የሚጫወቱ ሲሆኑ በመጠራጠር ውስጥ ናቸው::

9. በእውነቱ እነርሱ የሚጫወቱ ሲሆኑ በመጠራጠር ውስጥ ናቸው::

فَٱرۡتَقِبۡ يَوۡمَ تَأۡتِي ٱلسَّمَآءُ بِدُخَانٖ مُّبِينٖ

10. (መልዕክተኛችን ሙሐመድ ሆይ!) ( ሰዎችን) የሚሸፍን በሆነ ግልጽ ጭስ ሰማይ የምትመጣበትን ቀን ተጠባበቅ::

10. (መልዕክተኛችን ሙሐመድ ሆይ!) ( ሰዎችን) የሚሸፍን በሆነ ግልጽ ጭስ ሰማይ የምትመጣበትን ቀን ተጠባበቅ::

يَغۡشَى ٱلنَّاسَۖ هَٰذَا عَذَابٌ أَلِيمٞ

11.ሰዎችን ይሸፍናል ይህ አሳማሚ ቅጣት ነው::

11.ሰዎችን ይሸፍናል ይህ አሳማሚ ቅጣት ነው::

رَّبَّنَا ٱكۡشِفۡ عَنَّا ٱلۡعَذَابَ إِنَّا مُؤۡمِنُونَ

12. ጌታችን ሆይ! ክእኛ ላይ ቅጣቱን ግለጥልን:: እኛ ትክክለኛ አማኞች ነንና (ይላሉ::)

12. ጌታችን ሆይ! ክእኛ ላይ ቅጣቱን ግለጥልን:: እኛ ትክክለኛ አማኞች ነንና (ይላሉ::)

أَنَّىٰ لَهُمُ ٱلذِّكۡرَىٰ وَقَدۡ جَآءَهُمۡ رَسُولٞ مُّبِينٞ

13. አስረጂ መልዕክተኛ የመጣላቸው እና በአላህ የካዱ ሲሆኑ (ቅጣቱ በወረደ ጊዜ) ለእነርሱ መገሰጽ እንዴት ይኖራቸዋል?

13. አስረጂ መልዕክተኛ የመጣላቸው እና በአላህ የካዱ ሲሆኑ (ቅጣቱ በወረደ ጊዜ) ለእነርሱ መገሰጽ እንዴት ይኖራቸዋል?

ثُمَّ تَوَلَّوۡاْ عَنۡهُ وَقَالُواْ مُعَلَّمٞ مَّجۡنُونٌ

14. ከዚያም «ከሰው የተስተማረ እብድ ነው» ያሉ ሲሆኑ ከእርሱ ዞሩ።

14. ከዚያም «ከሰው የተስተማረ እብድ ነው» ያሉ ሲሆኑ ከእርሱ ዞሩ።

إِنَّا كَاشِفُواْ ٱلۡعَذَابِ قَلِيلًاۚ إِنَّكُمۡ عَآئِدُونَ

15. እኛ ቅጣትን ለጥቂት ጊዜ ገላጮች ነን። እናንተ ግን ወደ ክህደታችሁ በእርግጥ አንደገና ተመላሾች ናችሁ::

15. እኛ ቅጣትን ለጥቂት ጊዜ ገላጮች ነን። እናንተ ግን ወደ ክህደታችሁ በእርግጥ አንደገና ተመላሾች ናችሁ::

يَوۡمَ نَبۡطِشُ ٱلۡبَطۡشَةَ ٱلۡكُبۡرَىٰٓ إِنَّا مُنتَقِمُونَ

16. ታላቂቱን ብርቱ አያያዝ በምንይዝበት ቀን እኛ ተበቃዮች ነን።

16. ታላቂቱን ብርቱ አያያዝ በምንይዝበት ቀን እኛ ተበቃዮች ነን።

۞ وَلَقَدۡ فَتَنَّا قَبۡلَهُمۡ قَوۡمَ فِرۡعَوۡنَ وَجَآءَهُمۡ رَسُولٞ كَرِيمٌ

17. ከእነርሱ በፊት የፈርዖንን ህዝቦች በእርግጥ ሞከርን:: ክቡር መልዕክተኛም መጣላቸው::

17. ከእነርሱ በፊት የፈርዖንን ህዝቦች በእርግጥ ሞከርን:: ክቡር መልዕክተኛም መጣላቸው::

أَنۡ أَدُّوٓاْ إِلَيَّ عِبَادَ ٱللَّهِۖ إِنِّي لَكُمۡ رَسُولٌ أَمِينٞ

18. «የአላህን ባሮች ወደ እኔ አድርሱ (ለኔ ስጡኝ):: እኔ ለእናንተ ታማኝ መልዕክተኛ ነኝና።

18. «የአላህን ባሮች ወደ እኔ አድርሱ (ለኔ ስጡኝ):: እኔ ለእናንተ ታማኝ መልዕክተኛ ነኝና።

وَأَن لَّا تَعۡلُواْ عَلَى ٱللَّهِۖ إِنِّيٓ ءَاتِيكُم بِسُلۡطَٰنٖ مُّبِينٖ

19. «በአላህም ላይ ላትኮሩ። እኔ ግልጽ የሆነን አስረጂ ያመጣሁላችሁ ነኝና በማለት መጣላቸው።

19. «በአላህም ላይ ላትኮሩ። እኔ ግልጽ የሆነን አስረጂ ያመጣሁላችሁ ነኝና በማለት መጣላቸው።

وَإِنِّي عُذۡتُ بِرَبِّي وَرَبِّكُمۡ أَن تَرۡجُمُونِ

20. «እኔ እንዳትወግሩኝ በጌታዬና በጌታችሁ ተጠብቂያለሁ።

20. «እኔ እንዳትወግሩኝ በጌታዬና በጌታችሁ ተጠብቂያለሁ።

وَإِن لَّمۡ تُؤۡمِنُواْ لِي فَٱعۡتَزِلُونِ

21. «በእኔም ባታምኑ ራቁኝ። ተውኝ።» አለ::

21. «በእኔም ባታምኑ ራቁኝ። ተውኝ።» አለ::

فَدَعَا رَبَّهُۥٓ أَنَّ هَٰٓؤُلَآءِ قَوۡمٞ مُّجۡرِمُونَ

22. «ቀጥሎም እነዚህ አመጸኞች ህዝቦች ናቸው (አጥፋቸው)።» ሲል ጌታውን ለመነ።

22. «ቀጥሎም እነዚህ አመጸኞች ህዝቦች ናቸው (አጥፋቸው)።» ሲል ጌታውን ለመነ።

فَأَسۡرِ بِعِبَادِي لَيۡلًا إِنَّكُم مُّتَّبَعُونَ

23. (ጌታዉም አለ) «ባሮቼንም ይዘህ በሌሊት ሂድ። እናንተ የሚከተሉዋችሁ ናችሁና።

23. (ጌታዉም አለ) «ባሮቼንም ይዘህ በሌሊት ሂድ። እናንተ የሚከተሉዋችሁ ናችሁና።

وَٱتۡرُكِ ٱلۡبَحۡرَ رَهۡوًاۖ إِنَّهُمۡ جُندٞ مُّغۡرَقُونَ

24. «ባህሩንም የተከፈተ ሆኖ ተወው፤ እነርሱ የሚሰምጡ ሰራዊት ናቸውና» አለው።

24. «ባህሩንም የተከፈተ ሆኖ ተወው፤ እነርሱ የሚሰምጡ ሰራዊት ናቸውና» አለው።

كَمۡ تَرَكُواْ مِن جَنَّٰتٖ وَعُيُونٖ

25. ከአትክልቶችና ከምንጮች ብዙ ነገሮችን ትተው ሄዱ።

25. ከአትክልቶችና ከምንጮች ብዙ ነገሮችን ትተው ሄዱ።

وَزُرُوعٖ وَمَقَامٖ كَرِيمٖ

26. ከአዝመራዎችም ከመልካም መቀመጫም

26. ከአዝመራዎችም ከመልካም መቀመጫም

وَنَعۡمَةٖ كَانُواْ فِيهَا فَٰكِهِينَ

27. በእርሷ ተደሳቾች ከነበሩባትም ድሎት (ብዙን ነገር ትተው ሞቱ)።

27. በእርሷ ተደሳቾች ከነበሩባትም ድሎት (ብዙን ነገር ትተው ሞቱ)።

كَذَٰلِكَۖ وَأَوۡرَثۡنَٰهَا قَوۡمًا ءَاخَرِينَ

28. ነገሩ ልክ እንደዚህ ሆነ፤ ለሌሎች ህዝቦች አወረስናትም።

28. ነገሩ ልክ እንደዚህ ሆነ፤ ለሌሎች ህዝቦች አወረስናትም።

فَمَا بَكَتۡ عَلَيۡهِمُ ٱلسَّمَآءُ وَٱلۡأَرۡضُ وَمَا كَانُواْ مُنظَرِينَ

29. ሰማይና ምድር በእነርሱ ላይ አላለቀሱም:: የሚቆዩም አልነበሩም::

29. ሰማይና ምድር በእነርሱ ላይ አላለቀሱም:: የሚቆዩም አልነበሩም::

وَلَقَدۡ نَجَّيۡنَا بَنِيٓ إِسۡرَٰٓءِيلَ مِنَ ٱلۡعَذَابِ ٱلۡمُهِينِ

30. የኢስራኢል ልጆችን ከዚያ አዋራጅ ከሆነው ስቃይ በእርግጥ አዳንናቸው::

30. የኢስራኢል ልጆችን ከዚያ አዋራጅ ከሆነው ስቃይ በእርግጥ አዳንናቸው::

مِن فِرۡعَوۡنَۚ إِنَّهُۥ كَانَ عَالِيٗا مِّنَ ٱلۡمُسۡرِفِينَ

31. ከፈርዖን እርሱ (ፈርዖውን) የኮራ ከወሰን አላፊዎችም አንዱ ነበርና::

31. ከፈርዖን እርሱ (ፈርዖውን) የኮራ ከወሰን አላፊዎችም አንዱ ነበርና::

وَلَقَدِ ٱخۡتَرۡنَٰهُمۡ عَلَىٰ عِلۡمٍ عَلَى ٱلۡعَٰلَمِينَ

32. ከማወቅም ጋር ከዓለም ህዝቦች መካከል በእርግጥ መረጥናቸው::

32. ከማወቅም ጋር ከዓለም ህዝቦች መካከል በእርግጥ መረጥናቸው::

وَءَاتَيۡنَٰهُم مِّنَ ٱلۡأٓيَٰتِ مَا فِيهِ بَلَٰٓؤٞاْ مُّبِينٌ

33. ከተአምራቶችም በውስጡ ግልጽ የሆነ ፈተና ያለበትን ሰጠናቸው::

33. ከተአምራቶችም በውስጡ ግልጽ የሆነ ፈተና ያለበትን ሰጠናቸው::

إِنَّ هَٰٓؤُلَآءِ لَيَقُولُونَ

34. እነዚህ (የመካ ካሓዲያን) በእርግጥ ይላሉ:

34. እነዚህ (የመካ ካሓዲያን) በእርግጥ ይላሉ:

إِنۡ هِيَ إِلَّا مَوۡتَتُنَا ٱلۡأُولَىٰ وَمَا نَحۡنُ بِمُنشَرِينَ

35. «እርሷ የፊተኛይቱ ሞታችን እንጅ (ሌላ) አይደለችም። እኛም የምንቀሰቀስ አይደለንም።

35. «እርሷ የፊተኛይቱ ሞታችን እንጅ (ሌላ) አይደለችም። እኛም የምንቀሰቀስ አይደለንም።

فَأۡتُواْ بِـَٔابَآئِنَآ إِن كُنتُمۡ صَٰدِقِينَ

36. «እውነተኞችም እንደሆናችሁ አባቶቻችንን እስቲ አምጡልን።» (ይላሉ)

36. «እውነተኞችም እንደሆናችሁ አባቶቻችንን እስቲ አምጡልን።» (ይላሉ)

أَهُمۡ خَيۡرٌ أَمۡ قَوۡمُ تُبَّعٖ وَٱلَّذِينَ مِن قَبۡلِهِمۡ أَهۡلَكۡنَٰهُمۡۚ إِنَّهُمۡ كَانُواْ مُجۡرِمِينَ

37. እነርሱ በላጮች ናቸውን? ወይስ የቱበዕ ህዝቦችና እነዚያ ከእነርሱ በፊት የነበሩት? እነርሱን አጠፋናቸው። እነርሱ አመጸኞች ነበሩ።

37. እነርሱ በላጮች ናቸውን? ወይስ የቱበዕ ህዝቦችና እነዚያ ከእነርሱ በፊት የነበሩት? እነርሱን አጠፋናቸው። እነርሱ አመጸኞች ነበሩ።

وَمَا خَلَقۡنَا ٱلسَّمَٰوَٰتِ وَٱلۡأَرۡضَ وَمَا بَيۡنَهُمَا لَٰعِبِينَ

38. ሰማያትና ምድርን በሁለቱ መካከል ያለውንም ሁሉ ቀላጆች ሆነን አልፈጠርንም::

38. ሰማያትና ምድርን በሁለቱ መካከል ያለውንም ሁሉ ቀላጆች ሆነን አልፈጠርንም::

مَا خَلَقۡنَٰهُمَآ إِلَّا بِٱلۡحَقِّ وَلَٰكِنَّ أَكۡثَرَهُمۡ لَا يَعۡلَمُونَ

39. ሁለቱንም በቁምነገር እንጂ አልፈጠርናቸዉም:: ግን አብዛሀኞቻቸው አያውቀዉም::

39. ሁለቱንም በቁምነገር እንጂ አልፈጠርናቸዉም:: ግን አብዛሀኞቻቸው አያውቀዉም::

إِنَّ يَوۡمَ ٱلۡفَصۡلِ مِيقَٰتُهُمۡ أَجۡمَعِينَ

40. የመለያው ቀን ለሁሉም ቀጠሯቸው ነው::

40. የመለያው ቀን ለሁሉም ቀጠሯቸው ነው::

يَوۡمَ لَا يُغۡنِي مَوۡلًى عَن مَّوۡلٗى شَيۡـٔٗا وَلَا هُمۡ يُنصَرُونَ

41. ዘመድ ከዘመዱ ምንንም የማይጠቅምበት እነርሱም የማይረዱበት ቀን ነው::

41. ዘመድ ከዘመዱ ምንንም የማይጠቅምበት እነርሱም የማይረዱበት ቀን ነው::

إِلَّا مَن رَّحِمَ ٱللَّهُۚ إِنَّهُۥ هُوَ ٱلۡعَزِيزُ ٱلرَّحِيمُ

42. አላህ ያዘነለትና ያመነ ብቻ ሲቀር:: (እርሱ ይረዳል) እርሱ (አላህ) ሁሉን አሸናፊና አዛኝ ነውና::

42. አላህ ያዘነለትና ያመነ ብቻ ሲቀር:: (እርሱ ይረዳል) እርሱ (አላህ) ሁሉን አሸናፊና አዛኝ ነውና::

إِنَّ شَجَرَتَ ٱلزَّقُّومِ

43. የዘቁም ዛፍ

43. የዘቁም ዛፍ

طَعَامُ ٱلۡأَثِيمِ

44. የኃጢአተኞች ምግብ ናት::

44. የኃጢአተኞች ምግብ ናት::

كَٱلۡمُهۡلِ يَغۡلِي فِي ٱلۡبُطُونِ

45. እሱም ልክ እንደ ዘይት አተላ በሆዶች ውስጥ ይፈላል።

45. እሱም ልክ እንደ ዘይት አተላ በሆዶች ውስጥ ይፈላል።

كَغَلۡيِ ٱلۡحَمِيمِ

46. እንደገነፈለ ውሃ አፈላል የሚፈላ ነው::

46. እንደገነፈለ ውሃ አፈላል የሚፈላ ነው::

خُذُوهُ فَٱعۡتِلُوهُ إِلَىٰ سَوَآءِ ٱلۡجَحِيمِ

47. ያዙትና ወደ ገሀነም መካከል (ውስጥ) በሀይል ጎትቱት (ገፍትሩት)::

47. ያዙትና ወደ ገሀነም መካከል (ውስጥ) በሀይል ጎትቱት (ገፍትሩት)::

ثُمَّ صُبُّواْ فَوۡقَ رَأۡسِهِۦ مِنۡ عَذَابِ ٱلۡحَمِيمِ

48. ከዚያም በራሱ ላይ ከፈላ ውሃ ስቃይ አንቧቡበት::

48. ከዚያም በራሱ ላይ ከፈላ ውሃ ስቃይ አንቧቡበት::

ذُقۡ إِنَّكَ أَنتَ ٱلۡعَزِيزُ ٱلۡكَرِيمُ

49. (ይባላልም) «ቅመስ አንተ አሸናፊው፤ ክቡር የነበርክ ነህና።

49. (ይባላልም) «ቅመስ አንተ አሸናፊው፤ ክቡር የነበርክ ነህና።

إِنَّ هَٰذَا مَا كُنتُم بِهِۦ تَمۡتَرُونَ

50. «ይህ ያ በእርሱ ትጠራጠሩበት የነበራችሁት ነው» (ይባላሉ)::

50. «ይህ ያ በእርሱ ትጠራጠሩበት የነበራችሁት ነው» (ይባላሉ)::

إِنَّ ٱلۡمُتَّقِينَ فِي مَقَامٍ أَمِينٖ

51. ጥንቁቆች በእርግጥ በደህናማ መኖሪያ ውስጥ ናቸው::

51. ጥንቁቆች በእርግጥ በደህናማ መኖሪያ ውስጥ ናቸው::

فِي جَنَّٰتٖ وَعُيُونٖ

52. በአትክልቶችና በምንጮች ውስጥ ናቸው::

52. በአትክልቶችና በምንጮች ውስጥ ናቸው::

يَلۡبَسُونَ مِن سُندُسٖ وَإِسۡتَبۡرَقٖ مُّتَقَٰبِلِينَ

53. ፊት ለፊት የተቅጣጩ ሆነው ከስስ ሐርና ከወፍራም ሐር ይለብሳሉ::

53. ፊት ለፊት የተቅጣጩ ሆነው ከስስ ሐርና ከወፍራም ሐር ይለብሳሉ::

كَذَٰلِكَ وَزَوَّجۡنَٰهُم بِحُورٍ عِينٖ

54. ነገሩ ልክ እንደዚህ ነው። ዓይናማዎች የሆኑን ሴቶችም እናጠናዳቸዋለን::

54. ነገሩ ልክ እንደዚህ ነው። ዓይናማዎች የሆኑን ሴቶችም እናጠናዳቸዋለን::

يَدۡعُونَ فِيهَا بِكُلِّ فَٰكِهَةٍ ءَامِنِينَ

55. በእርሷ ውስጥም የተማመኑ ሆነው ከፍራፍሬ ሁሉ ያዛሉ::

55. በእርሷ ውስጥም የተማመኑ ሆነው ከፍራፍሬ ሁሉ ያዛሉ::

لَا يَذُوقُونَ فِيهَا ٱلۡمَوۡتَ إِلَّا ٱلۡمَوۡتَةَ ٱلۡأُولَىٰۖ وَوَقَىٰهُمۡ عَذَابَ ٱلۡجَحِيمِ

56. የፊተኛይቱን ሞት እንጂ ዳግመኛ በእርሷ ውስጥ ሞትን አይቀምሱም:: የገሀነምንም ቅጣት አላህ ጠብቋቸዋል።

56. የፊተኛይቱን ሞት እንጂ ዳግመኛ በእርሷ ውስጥ ሞትን አይቀምሱም:: የገሀነምንም ቅጣት አላህ ጠብቋቸዋል።

فَضۡلٗا مِّن رَّبِّكَۚ ذَٰلِكَ هُوَ ٱلۡفَوۡزُ ٱلۡعَظِيمُ

57. (መልዕክተኛችን ሙሐመድ ሆይ!) (ይህም ) ከጌታህ (አላህ) የሆነ ትሩፋት ሲሆን ይህም እርሱ ታላቁ እድል ነው::

57. (መልዕክተኛችን ሙሐመድ ሆይ!) (ይህም ) ከጌታህ (አላህ) የሆነ ትሩፋት ሲሆን ይህም እርሱ ታላቁ እድል ነው::

فَإِنَّمَا يَسَّرۡنَٰهُ بِلِسَانِكَ لَعَلَّهُمۡ يَتَذَكَّرُونَ

58. (መልዕክተኛችን ሙሐመድ ሆይ!) ቁርኣኑንም በቋንቋህ ያገራነው ህዝቦች ይገነዘቡት ዘንድ ብቻ ነው::

58. (መልዕክተኛችን ሙሐመድ ሆይ!) ቁርኣኑንም በቋንቋህ ያገራነው ህዝቦች ይገነዘቡት ዘንድ ብቻ ነው::

فَٱرۡتَقِبۡ إِنَّهُم مُّرۡتَقِبُونَ

59. ተጠባበቅ:: እነርሱም ተጠባባቂዎች ናቸውና::

59. ተጠባበቅ:: እነርሱም ተጠባባቂዎች ናቸውና::
Footer Include