Header Include

Amharic translation - Africa Academy

Translated by Muhammad Zain Zahruddin. Published by Africa Academy

QR Code https://quran.islamcontent.com/aa/amharic_zain

سَأَلَ سَآئِلُۢ بِعَذَابٖ وَاقِعٖ

1. ወዳቂ (ተከሳች) ከሆነው ቅጣት ጠያቂ ጠየቀ::

1. ወዳቂ (ተከሳች) ከሆነው ቅጣት ጠያቂ ጠየቀ::

لِّلۡكَٰفِرِينَ لَيۡسَ لَهُۥ دَافِعٞ

2. ከሓዲያን ላይ (ወዳቂ ከሆነው) ለእርሱ መላሽ የለዉም።

2. ከሓዲያን ላይ (ወዳቂ ከሆነው) ለእርሱ መላሽ የለዉም።

مِّنَ ٱللَّهِ ذِي ٱلۡمَعَارِجِ

3. የ (ሰማያት) መሰላሎች ባለቤት ከሆነው አላህ (መላሽ የለዉም)::

3. የ (ሰማያት) መሰላሎች ባለቤት ከሆነው አላህ (መላሽ የለዉም)::

تَعۡرُجُ ٱلۡمَلَٰٓئِكَةُ وَٱلرُّوحُ إِلَيۡهِ فِي يَوۡمٖ كَانَ مِقۡدَارُهُۥ خَمۡسِينَ أَلۡفَ سَنَةٖ

4. መላዕክትና መንፈሱም ልኩ ሀምሳ ሺህ ዓመት በሆነ ቀን ውስጥ ወደ እርሱ (ይወጣሉ)::

4. መላዕክትና መንፈሱም ልኩ ሀምሳ ሺህ ዓመት በሆነ ቀን ውስጥ ወደ እርሱ (ይወጣሉ)::

فَٱصۡبِرۡ صَبۡرٗا جَمِيلًا

5. መልካምን ትዕግስት ታገስ::

5. መልካምን ትዕግስት ታገስ::

إِنَّهُمۡ يَرَوۡنَهُۥ بَعِيدٗا

6. እነርሱ ያንን ቀን ሩቅ አድርገው ያዩታል::

6. እነርሱ ያንን ቀን ሩቅ አድርገው ያዩታል::

وَنَرَىٰهُ قَرِيبٗا

7. እኛም ቅርብ ሆኖ እናየዋለን::

7. እኛም ቅርብ ሆኖ እናየዋለን::

يَوۡمَ تَكُونُ ٱلسَّمَآءُ كَٱلۡمُهۡلِ

8. ሰማይ እንደ ዘይት አተላ በምትሆንበት ቀን፤

8. ሰማይ እንደ ዘይት አተላ በምትሆንበት ቀን፤

وَتَكُونُ ٱلۡجِبَالُ كَٱلۡعِهۡنِ

9. ጋራዎችም በተለያዩ ቀለማት እንደ ተነከረ ሱፍ (ንፋስ) እንደበተነውና እንደሚያበረው በሚሆኑበት ቀን፤

9. ጋራዎችም በተለያዩ ቀለማት እንደ ተነከረ ሱፍ (ንፋስ) እንደበተነውና እንደሚያበረው በሚሆኑበት ቀን፤

وَلَا يَسۡـَٔلُ حَمِيمٌ حَمِيمٗا

10. ዘመድም ዘመድን በማይጠይቅበት ቀን መላሽ የለዉም::

10. ዘመድም ዘመድን በማይጠይቅበት ቀን መላሽ የለዉም::

يُبَصَّرُونَهُمۡۚ يَوَدُّ ٱلۡمُجۡرِمُ لَوۡ يَفۡتَدِي مِنۡ عَذَابِ يَوۡمِئِذِۭ بِبَنِيهِ

11. (ዘመዶቻቸውን) ያዩዋቸዋል፤ አመጸኛው ከዚያ ቀን ስቃይ (ነፍሱን) በልጆቹ ቤዛ ሊያደርግ ይመኛል::

11. (ዘመዶቻቸውን) ያዩዋቸዋል፤ አመጸኛው ከዚያ ቀን ስቃይ (ነፍሱን) በልጆቹ ቤዛ ሊያደርግ ይመኛል::

وَصَٰحِبَتِهِۦ وَأَخِيهِ

12. በሚስቱም በወንድሙም፤

12. በሚስቱም በወንድሙም፤

وَفَصِيلَتِهِ ٱلَّتِي تُـٔۡوِيهِ

13. በዚያች በምታስጠጋው ጎሳውም፤

13. በዚያች በምታስጠጋው ጎሳውም፤

وَمَن فِي ٱلۡأَرۡضِ جَمِيعٗا ثُمَّ يُنجِيهِ

14. በምድርም ላይ ባለው ሁሉ (ሊበዥ) ከዚያ ሊያድነው (ይመኛል)::

14. በምድርም ላይ ባለው ሁሉ (ሊበዥ) ከዚያ ሊያድነው (ይመኛል)::

كَلَّآۖ إِنَّهَا لَظَىٰ

15. ይተው፤እርሷ (እሳቲቱ) ነዲድ እሳት ናት።

15. ይተው፤እርሷ (እሳቲቱ) ነዲድ እሳት ናት።

نَزَّاعَةٗ لِّلشَّوَىٰ

16. የራስን ቅል ቆዳ የምትሞሽልቅ ስትሆን፤

16. የራስን ቅል ቆዳ የምትሞሽልቅ ስትሆን፤

تَدۡعُواْ مَنۡ أَدۡبَرَ وَتَوَلَّىٰ

17. (ከእምነት) የዞረንና የሸሸን ሰው (ወደ እርሷ) ትጠራለች::

17. (ከእምነት) የዞረንና የሸሸን ሰው (ወደ እርሷ) ትጠራለች::

وَجَمَعَ فَأَوۡعَىٰٓ

18. ገንዘብን የሰበሰበንና ዘካውን ሳይሰጥ የቆጠረንም (ትጠራለች)::

18. ገንዘብን የሰበሰበንና ዘካውን ሳይሰጥ የቆጠረንም (ትጠራለች)::

۞ إِنَّ ٱلۡإِنسَٰنَ خُلِقَ هَلُوعًا

19. ሰው ቅጠ ቢስ ሆኖ ተፈጠረ::

19. ሰው ቅጠ ቢስ ሆኖ ተፈጠረ::

إِذَا مَسَّهُ ٱلشَّرُّ جَزُوعٗا

20. ክፉ ነገር ባገኘው ጊዜ ብስጭተኛ፤

20. ክፉ ነገር ባገኘው ጊዜ ብስጭተኛ፤

وَإِذَا مَسَّهُ ٱلۡخَيۡرُ مَنُوعًا

21. መልካምም ነገር (ድሎት) ባገኘው ጊዜ ከልካይ ሆኖ ተፈጠረ::

21. መልካምም ነገር (ድሎት) ባገኘው ጊዜ ከልካይ ሆኖ ተፈጠረ::

إِلَّا ٱلۡمُصَلِّينَ

22. ሰጋጆች ብቻ ሲቀሩ::

22. ሰጋጆች ብቻ ሲቀሩ::

ٱلَّذِينَ هُمۡ عَلَىٰ صَلَاتِهِمۡ دَآئِمُونَ

23. እነዚያ እነርሱ በስግደታቸው ላይ ዘወታሪዎች የሆኑት::

23. እነዚያ እነርሱ በስግደታቸው ላይ ዘወታሪዎች የሆኑት::

وَٱلَّذِينَ فِيٓ أَمۡوَٰلِهِمۡ حَقّٞ مَّعۡلُومٞ

24. እነዚያም በገንዘቦቻቸው ላይ የታወቀ መብት ያለባቸው የሆኑት፤

24. እነዚያም በገንዘቦቻቸው ላይ የታወቀ መብት ያለባቸው የሆኑት፤

لِّلسَّآئِلِ وَٱلۡمَحۡرُومِ

25. ለለማኝ እና ከልመና ለሚቆጠብም መብት (ያለባቸው የሆኑ)፤

25. ለለማኝ እና ከልመና ለሚቆጠብም መብት (ያለባቸው የሆኑ)፤

وَٱلَّذِينَ يُصَدِّقُونَ بِيَوۡمِ ٱلدِّينِ

26. እነዚያም በፍርዱ ቀን እውነት የሚሉት የሚያረጋግጡ::

26. እነዚያም በፍርዱ ቀን እውነት የሚሉት የሚያረጋግጡ::

وَٱلَّذِينَ هُم مِّنۡ عَذَابِ رَبِّهِم مُّشۡفِقُونَ

27. እነዚያም እነርሱ ከጌታቸው ቅጣት ፈሪዎች የሆኑት::

27. እነዚያም እነርሱ ከጌታቸው ቅጣት ፈሪዎች የሆኑት::

إِنَّ عَذَابَ رَبِّهِمۡ غَيۡرُ مَأۡمُونٖ

28. የጌታቸው ቅጣት የማያስተማምን ነውና።

28. የጌታቸው ቅጣት የማያስተማምን ነውና።

وَٱلَّذِينَ هُمۡ لِفُرُوجِهِمۡ حَٰفِظُونَ

29. እነዚያም እነርሱ ብልቶቻቸውን ጠባቂዎች የሆኑት፤

29. እነዚያም እነርሱ ብልቶቻቸውን ጠባቂዎች የሆኑት፤

إِلَّا عَلَىٰٓ أَزۡوَٰجِهِمۡ أَوۡ مَا مَلَكَتۡ أَيۡمَٰنُهُمۡ فَإِنَّهُمۡ غَيۡرُ مَلُومِينَ

30. በሚስቶቻቸው ወይም እጆቻቸው በያዙዋቸው ባሮች ላይ ሲቀር:: እነርሱ በነዚህ የማይወቀሱ ናቸውና::

30. በሚስቶቻቸው ወይም እጆቻቸው በያዙዋቸው ባሮች ላይ ሲቀር:: እነርሱ በነዚህ የማይወቀሱ ናቸውና::

فَمَنِ ٱبۡتَغَىٰ وَرَآءَ ذَٰلِكَ فَأُوْلَٰٓئِكَ هُمُ ٱلۡعَادُونَ

31. ከዚያ ወዲያ የፈለገ እነዚያ እነርሱ ድንበር አላፊዎች ናቸው።

31. ከዚያ ወዲያ የፈለገ እነዚያ እነርሱ ድንበር አላፊዎች ናቸው።

وَٱلَّذِينَ هُمۡ لِأَمَٰنَٰتِهِمۡ وَعَهۡدِهِمۡ رَٰعُونَ

32. እነዚያም እነርሱ አደራዎቻቸውና ቃል ኪዳናቸውን ጠባቂዎች የሆኑት::

32. እነዚያም እነርሱ አደራዎቻቸውና ቃል ኪዳናቸውን ጠባቂዎች የሆኑት::

وَٱلَّذِينَ هُم بِشَهَٰدَٰتِهِمۡ قَآئِمُونَ

33. እነዚያም እነርሱ በምስክሮቻቸው ላይ ቀጥ ያሉት::

33. እነዚያም እነርሱ በምስክሮቻቸው ላይ ቀጥ ያሉት::

وَٱلَّذِينَ هُمۡ عَلَىٰ صَلَاتِهِمۡ يُحَافِظُونَ

34. እነዚያም እነርሱ በሶላቶቻቸው ላይ የሚጠባበቁት::

34. እነዚያም እነርሱ በሶላቶቻቸው ላይ የሚጠባበቁት::

أُوْلَٰٓئِكَ فِي جَنَّٰتٖ مُّكۡرَمُونَ

35. እነዚያ (ከዚህ በላይ የተወሱት ሁሉ) በገነቶች ውስጥ የሚከበሩ ናቸው::

35. እነዚያ (ከዚህ በላይ የተወሱት ሁሉ) በገነቶች ውስጥ የሚከበሩ ናቸው::

فَمَالِ ٱلَّذِينَ كَفَرُواْ قِبَلَكَ مُهۡطِعِينَ

36. እነዚያ (በአላህ) የካዱት ወደ አንተ በኩል አንገቶቻቸውን መዘው የሚያተኩሩት ምን አላቸው?

36. እነዚያ (በአላህ) የካዱት ወደ አንተ በኩል አንገቶቻቸውን መዘው የሚያተኩሩት ምን አላቸው?

عَنِ ٱلۡيَمِينِ وَعَنِ ٱلشِّمَالِ عِزِينَ

37. ከቀኝና ከግራ ክፍልፍል ቡድኖች ሲሆኑ፤

37. ከቀኝና ከግራ ክፍልፍል ቡድኖች ሲሆኑ፤

أَيَطۡمَعُ كُلُّ ٱمۡرِيٕٖ مِّنۡهُمۡ أَن يُدۡخَلَ جَنَّةَ نَعِيمٖ

38. ከእነርሱ እያንዳንዱ ሰው የጸጋይቱን ገነት መግባትን ይከጅላልን?

38. ከእነርሱ እያንዳንዱ ሰው የጸጋይቱን ገነት መግባትን ይከጅላልን?

كَلَّآۖ إِنَّا خَلَقۡنَٰهُم مِّمَّا يَعۡلَمُونَ

39. ይከልከል፤ በፍጹም እኛ ከሚያውቁት ነገር (ከፍተወት ጠብታ) ፈጠርናቸው::

39. ይከልከል፤ በፍጹም እኛ ከሚያውቁት ነገር (ከፍተወት ጠብታ) ፈጠርናቸው::

فَلَآ أُقۡسِمُ بِرَبِّ ٱلۡمَشَٰرِقِ وَٱلۡمَغَٰرِبِ إِنَّا لَقَٰدِرُونَ

40. (እናም ጉዳዩ ከሓዲያን እንደሚሉት አይደለም):: በምስራቆችና በምዕራቦች ጌታ እምላለሁ፤ እኛ በእርግጥ ቻዮች ነን::

40. (እናም ጉዳዩ ከሓዲያን እንደሚሉት አይደለም):: በምስራቆችና በምዕራቦች ጌታ እምላለሁ፤ እኛ በእርግጥ ቻዮች ነን::

عَلَىٰٓ أَن نُّبَدِّلَ خَيۡرٗا مِّنۡهُمۡ وَمَا نَحۡنُ بِمَسۡبُوقِينَ

41. ከእነርሱ የተሻለን በመለወጥ ላይ እኛም ተሸናፊዎች አይደለንም::

41. ከእነርሱ የተሻለን በመለወጥ ላይ እኛም ተሸናፊዎች አይደለንም::

فَذَرۡهُمۡ يَخُوضُواْ وَيَلۡعَبُواْ حَتَّىٰ يُلَٰقُواْ يَوۡمَهُمُ ٱلَّذِي يُوعَدُونَ

42. ያንንም የሚሰፈራሩበትን ቀናቸውን እስከሚያገኙ ድረስ ተዋቸው፤ በአሉባልታዎችም ዉስጥ ይዋኙ፤ ይጫወቱም።

42. ያንንም የሚሰፈራሩበትን ቀናቸውን እስከሚያገኙ ድረስ ተዋቸው፤ በአሉባልታዎችም ዉስጥ ይዋኙ፤ ይጫወቱም።

يَوۡمَ يَخۡرُجُونَ مِنَ ٱلۡأَجۡدَاثِ سِرَاعٗا كَأَنَّهُمۡ إِلَىٰ نُصُبٖ يُوفِضُونَ

43. ያ ቀን ወደ ጣዖት እንደሚሽቀዳደሙ ሆነው ከመቃብሮቻቸው ፈጥነው የሚወጡበትን ቀን ነው::

43. ያ ቀን ወደ ጣዖት እንደሚሽቀዳደሙ ሆነው ከመቃብሮቻቸው ፈጥነው የሚወጡበትን ቀን ነው::

خَٰشِعَةً أَبۡصَٰرُهُمۡ تَرۡهَقُهُمۡ ذِلَّةٞۚ ذَٰلِكَ ٱلۡيَوۡمُ ٱلَّذِي كَانُواْ يُوعَدُونَ

44. ዓይኖቻቸው ያፈሩ ሆነው፤ ውርደት ትሸፍናቸዋለች:: ይህ ቀን ያ ይስፈራሩበት የነበሩት ቀን ነው::

44. ዓይኖቻቸው ያፈሩ ሆነው፤ ውርደት ትሸፍናቸዋለች:: ይህ ቀን ያ ይስፈራሩበት የነበሩት ቀን ነው::
Footer Include