Header Include

Amharic translation - Africa Academy

Translated by Muhammad Zain Zahruddin. Published by Africa Academy

QR Code https://quran.islamcontent.com/aa/amharic_zain

يَٰٓأَيُّهَا ٱلۡمُدَّثِّرُ

1. አንተ (ልብስ) ደራቢው ሆይ!

1. አንተ (ልብስ) ደራቢው ሆይ!

قُمۡ فَأَنذِرۡ

2. ተነሳና (ህዝቦችህን) አስጠንቅቅ።

2. ተነሳና (ህዝቦችህን) አስጠንቅቅ።

وَرَبَّكَ فَكَبِّرۡ

3. ጌታህንም አክብር::

3. ጌታህንም አክብር::

وَثِيَابَكَ فَطَهِّرۡ

4. ልብስህንም አጥራ::

4. ልብስህንም አጥራ::

وَٱلرُّجۡزَ فَٱهۡجُرۡ

5. ጣዖትንም ራቅ::

5. ጣዖትንም ራቅ::

وَلَا تَمۡنُن تَسۡتَكۡثِرُ

6. ማብዛትንም የምትፈልግ ሆነህ አትለግስ::

6. ማብዛትንም የምትፈልግ ሆነህ አትለግስ::

وَلِرَبِّكَ فَٱصۡبِرۡ

7. (ብዙ ዒባዳን ከመስራት አትድከም):: ለጌታህም (ትዕዘዛዝ) ታገስ።

7. (ብዙ ዒባዳን ከመስራት አትድከም):: ለጌታህም (ትዕዘዛዝ) ታገስ።

فَإِذَا نُقِرَ فِي ٱلنَّاقُورِ

8. በቀንዱም በተነፋ ጊዜ፤

8. በቀንዱም በተነፋ ጊዜ፤

فَذَٰلِكَ يَوۡمَئِذٖ يَوۡمٌ عَسِيرٌ

9. ይህን ጊዜ ያ ቀን አስቸጋሪ ቀን ነው።

9. ይህን ጊዜ ያ ቀን አስቸጋሪ ቀን ነው።

عَلَى ٱلۡكَٰفِرِينَ غَيۡرُ يَسِيرٖ

10. (በተለይ) በከሓዲያን ላይ ገር ያልሆነ ቀን ነው።

10. (በተለይ) በከሓዲያን ላይ ገር ያልሆነ ቀን ነው።

ذَرۡنِي وَمَنۡ خَلَقۡتُ وَحِيدٗا

11. (መልዕክተኛችን ሙሐመድ ሆይ!) በብቸኝነት ከፈጠርኩት ጋር ተወኝ።

11. (መልዕክተኛችን ሙሐመድ ሆይ!) በብቸኝነት ከፈጠርኩት ጋር ተወኝ።

وَجَعَلۡتُ لَهُۥ مَالٗا مَّمۡدُودٗا

12. ለእርሱም የተዘረጋን ገንዘብ (በዓይነቱ) አደረግኩለት።

12. ለእርሱም የተዘረጋን ገንዘብ (በዓይነቱ) አደረግኩለት።

وَبَنِينَ شُهُودٗا

13. በየአደባባዩ ተገኝ የሆኑ ወንዶች ልጆችንም ሰጠሁት።

13. በየአደባባዩ ተገኝ የሆኑ ወንዶች ልጆችንም ሰጠሁት።

وَمَهَّدتُّ لَهُۥ تَمۡهِيدٗا

14. ለእርሱም ኑሮውን መዘርጋትን ዘረጋሁለት፤

14. ለእርሱም ኑሮውን መዘርጋትን ዘረጋሁለት፤

ثُمَّ يَطۡمَعُ أَنۡ أَزِيدَ

15. ከዚያ ልጨምርለት ይከጅላል::

15. ከዚያ ልጨምርለት ይከጅላል::

كَلَّآۖ إِنَّهُۥ كَانَ لِأٓيَٰتِنَا عَنِيدٗا

16. ሰው ይከልከል! እርሱ ለአናቅጻችን በእርግጥ ተቃዋሚ ነበርና።

16. ሰው ይከልከል! እርሱ ለአናቅጻችን በእርግጥ ተቃዋሚ ነበርና።

سَأُرۡهِقُهُۥ صَعُودًا

17. በእርግጥ (ገሀነም ውስጥ) ችግርን አስገድደዋለሁ።

17. በእርግጥ (ገሀነም ውስጥ) ችግርን አስገድደዋለሁ።

إِنَّهُۥ فَكَّرَ وَقَدَّرَ

18. እርሱ (በቁርኣን ጉዳይ) አሰበ፤ ገመተም።

18. እርሱ (በቁርኣን ጉዳይ) አሰበ፤ ገመተም።

فَقُتِلَ كَيۡفَ قَدَّرَ

19. እናም ተረገመ:: እንዴት ገመተ!

19. እናም ተረገመ:: እንዴት ገመተ!

ثُمَّ قُتِلَ كَيۡفَ قَدَّرَ

20. ከዚያ ተረገመ። እንዴትስ ገመተ!

20. ከዚያ ተረገመ። እንዴትስ ገመተ!

ثُمَّ نَظَرَ

21. ከዚያም እንደገና (በቁርኣን ጉዳይ) ተመለከተ።

21. ከዚያም እንደገና (በቁርኣን ጉዳይ) ተመለከተ።

ثُمَّ عَبَسَ وَبَسَرَ

22. ከዚያ ፊቱን አጨፈገገ አኮማተረም::

22. ከዚያ ፊቱን አጨፈገገ አኮማተረም::

ثُمَّ أَدۡبَرَ وَٱسۡتَكۡبَرَ

23. ከዚያ (በአላህ ከማመን) ዞረ:: ኮራም::

23. ከዚያ (በአላህ ከማመን) ዞረ:: ኮራም::

فَقَالَ إِنۡ هَٰذَآ إِلَّا سِحۡرٞ يُؤۡثَرُ

24. «ይህ ከሌላ (ሰው) የሚቀዳ ድግምት እንጂ ሌላ አይደለም።

24. «ይህ ከሌላ (ሰው) የሚቀዳ ድግምት እንጂ ሌላ አይደለም።

إِنۡ هَٰذَآ إِلَّا قَوۡلُ ٱلۡبَشَرِ

25. «ይህ የሰው ቃል እንጂ ሌላ አይደለም» አለ::

25. «ይህ የሰው ቃል እንጂ ሌላ አይደለም» አለ::

سَأُصۡلِيهِ سَقَرَ

26. ሰቀር (በተባለ የገሀነም ዋሻ ውስጥ) በእርግጥ አስገባዋለሁ::

26. ሰቀር (በተባለ የገሀነም ዋሻ ውስጥ) በእርግጥ አስገባዋለሁ::

وَمَآ أَدۡرَىٰكَ مَا سَقَرُ

27. (መልዕክተኛችን ሙሐመድ ሆይ!) ሰቀር ምን እንደሆነ ምን አሳወቀህ?

27. (መልዕክተኛችን ሙሐመድ ሆይ!) ሰቀር ምን እንደሆነ ምን አሳወቀህ?

لَا تُبۡقِي وَلَا تَذَرُ

28. (ያገኘችውን ሁሉ) አታስቀርም:: አትተዉምም::

28. (ያገኘችውን ሁሉ) አታስቀርም:: አትተዉምም::

لَوَّاحَةٞ لِّلۡبَشَرِ

29. የሰዎችን ቆዳ በጣም አክሳይ ናት።

29. የሰዎችን ቆዳ በጣም አክሳይ ናት።

عَلَيۡهَا تِسۡعَةَ عَشَرَ

30. በእርሷም ላይ አስራ ዘጠኝ (ዘበኞች) አሉባት::

30. በእርሷም ላይ አስራ ዘጠኝ (ዘበኞች) አሉባት::

وَمَا جَعَلۡنَآ أَصۡحَٰبَ ٱلنَّارِ إِلَّا مَلَٰٓئِكَةٗۖ وَمَا جَعَلۡنَا عِدَّتَهُمۡ إِلَّا فِتۡنَةٗ لِّلَّذِينَ كَفَرُواْ لِيَسۡتَيۡقِنَ ٱلَّذِينَ أُوتُواْ ٱلۡكِتَٰبَ وَيَزۡدَادَ ٱلَّذِينَ ءَامَنُوٓاْ إِيمَٰنٗا وَلَا يَرۡتَابَ ٱلَّذِينَ أُوتُواْ ٱلۡكِتَٰبَ وَٱلۡمُؤۡمِنُونَ وَلِيَقُولَ ٱلَّذِينَ فِي قُلُوبِهِم مَّرَضٞ وَٱلۡكَٰفِرُونَ مَاذَآ أَرَادَ ٱللَّهُ بِهَٰذَا مَثَلٗاۚ كَذَٰلِكَ يُضِلُّ ٱللَّهُ مَن يَشَآءُ وَيَهۡدِي مَن يَشَآءُۚ وَمَا يَعۡلَمُ جُنُودَ رَبِّكَ إِلَّا هُوَۚ وَمَا هِيَ إِلَّا ذِكۡرَىٰ لِلۡبَشَرِ

31. የእሳትን ዘበኞች መላዕክት እንጂ ሌላ አላደረግንም:: ቁጥራቸውንም ለእነዚያ በአላህ ለካዱት ሰዎች መፈተኛ እንጂ ለሌላ አላደረግንም:: እነዚያ መጽሐፍን የተሰጡት ሰዎች እንዲያረጋግጡ፤ እነዚያም በትክክል ያመኑት እምነትን እንዲጨምሩ፤ እነዚያም መጽሐፍን የተሰጡትና ምዕመናኖቹ እንዳይጠራጠሩ፤ እነዚያም በልቦቻቸው ውስጥ በሽታ ያለባቸው አስመሳዮችና ከሓዲያን «አላህ በዚህ (ቁጥር) ምን ምሳሌ ሽቷል?» እንዲሉ እንጂ (አላደረግንም):: ልክ እንደዚሁ አላህ የሚፈልገውን ያጠማል:: የሚፈልገውንም ያቀናል:: (መልዕክተኛችን ሙሐመድ ሆይ!) የጌታህንም ሰራዊት ልክ ከእርሱ በስተቀር ማንም አያውቅም:: የሰቀር እሳት ለሰዎች መገሰጫ እንጂ ሌላ አይደለም::

31. የእሳትን ዘበኞች መላዕክት እንጂ ሌላ አላደረግንም:: ቁጥራቸውንም ለእነዚያ በአላህ ለካዱት ሰዎች መፈተኛ እንጂ ለሌላ አላደረግንም:: እነዚያ መጽሐፍን የተሰጡት ሰዎች እንዲያረጋግጡ፤ እነዚያም በትክክል ያመኑት እምነትን እንዲጨምሩ፤ እነዚያም መጽሐፍን የተሰጡትና ምዕመናኖቹ እንዳይጠራጠሩ፤ እነዚያም በልቦቻቸው ውስጥ በሽታ ያለባቸው አስመሳዮችና ከሓዲያን «አላህ በዚህ (ቁጥር) ምን ምሳሌ ሽቷል?» እንዲሉ እንጂ (አላደረግንም):: ልክ እንደዚሁ አላህ የሚፈልገውን ያጠማል:: የሚፈልገውንም ያቀናል:: (መልዕክተኛችን ሙሐመድ ሆይ!) የጌታህንም ሰራዊት ልክ ከእርሱ በስተቀር ማንም አያውቅም:: የሰቀር እሳት ለሰዎች መገሰጫ እንጂ ሌላ አይደለም::

كَلَّا وَٱلۡقَمَرِ

32. (ከክህደት) ይከልከሉ:: በጨረቃ (እምላለሁ)፤

32. (ከክህደት) ይከልከሉ:: በጨረቃ (እምላለሁ)፤

وَٱلَّيۡلِ إِذۡ أَدۡبَرَ

33. በሌሊቱም በሄደ ጊዜ፤

33. በሌሊቱም በሄደ ጊዜ፤

وَٱلصُّبۡحِ إِذَآ أَسۡفَرَ

34. በንጋቱም ባበራ ጊዜ እምላለሁ።

34. በንጋቱም ባበራ ጊዜ እምላለሁ።

إِنَّهَا لَإِحۡدَى ٱلۡكُبَرِ

35. (ሰቀር) ከታላላቆች አደጋዎች አንዱ፤

35. (ሰቀር) ከታላላቆች አደጋዎች አንዱ፤

نَذِيرٗا لِّلۡبَشَرِ

36. ለሰዎች አስፈራሪ ናት።

36. ለሰዎች አስፈራሪ ናት።

لِمَن شَآءَ مِنكُمۡ أَن يَتَقَدَّمَ أَوۡ يَتَأَخَّرَ

37. ከናንተ መካከል ወደ በጎ ነገር መቅደምን ወይም ወደ ኋላ መቅረትን ለፈለገ (ሰው) ሁሉ፤

37. ከናንተ መካከል ወደ በጎ ነገር መቅደምን ወይም ወደ ኋላ መቅረትን ለፈለገ (ሰው) ሁሉ፤

كُلُّ نَفۡسِۭ بِمَا كَسَبَتۡ رَهِينَةٌ

38. ነፍስ ሁሉ በሰራችው ስራ ተያዥ ናት::

38. ነፍስ ሁሉ በሰራችው ስራ ተያዥ ናት::

إِلَّآ أَصۡحَٰبَ ٱلۡيَمِينِ

39. እነዚያ መዝገባቸውን በቀኝ እጃቸው የሚሰጡት ብቻ ሲቀሩ::

39. እነዚያ መዝገባቸውን በቀኝ እጃቸው የሚሰጡት ብቻ ሲቀሩ::

فِي جَنَّٰتٖ يَتَسَآءَلُونَ

40. (እነርሱማ) በገነቶች ውስጥ ሁነው እርስ በራሳቸው ይጠያየቃሉ::

40. (እነርሱማ) በገነቶች ውስጥ ሁነው እርስ በራሳቸው ይጠያየቃሉ::

عَنِ ٱلۡمُجۡرِمِينَ

41. ከአመጸኞች ሁኔታ (ይጠያየቃሉ)

41. ከአመጸኞች ሁኔታ (ይጠያየቃሉ)

مَا سَلَكَكُمۡ فِي سَقَرَ

42. (ከዚያ ለእነርሱ እንዲህ ይሏቸዋል።) «በሰቀር ውስጥ ምን አገባችሁ?»

42. (ከዚያ ለእነርሱ እንዲህ ይሏቸዋል።) «በሰቀር ውስጥ ምን አገባችሁ?»

قَالُواْ لَمۡ نَكُ مِنَ ٱلۡمُصَلِّينَ

43. «ከሰጋጆች አልነበርንም።

43. «ከሰጋጆች አልነበርንም።

وَلَمۡ نَكُ نُطۡعِمُ ٱلۡمِسۡكِينَ

44. «ለድሆችም የምናበላም አልነበርንም።

44. «ለድሆችም የምናበላም አልነበርንም።

وَكُنَّا نَخُوضُ مَعَ ٱلۡخَآئِضِينَ

45. «ከዘባራቂዎችም ጋር እንዘባርቅ ነበር።

45. «ከዘባራቂዎችም ጋር እንዘባርቅ ነበር።

وَكُنَّا نُكَذِّبُ بِيَوۡمِ ٱلدِّينِ

46. «በፍርዱ ቀንም እናስተባብል ነበር፤

46. «በፍርዱ ቀንም እናስተባብል ነበር፤

حَتَّىٰٓ أَتَىٰنَا ٱلۡيَقِينُ

47. «እርግጠኛው ነገር ሞት እስከመጣብን ድረስ።» ይላሉ

47. «እርግጠኛው ነገር ሞት እስከመጣብን ድረስ።» ይላሉ

فَمَا تَنفَعُهُمۡ شَفَٰعَةُ ٱلشَّٰفِعِينَ

48. እናም በዚያ ቀን የአማላጆች (ሁሉ) ምልጃ አትጠቅማቸዉም።

48. እናም በዚያ ቀን የአማላጆች (ሁሉ) ምልጃ አትጠቅማቸዉም።

فَمَا لَهُمۡ عَنِ ٱلتَّذۡكِرَةِ مُعۡرِضِينَ

49. ከ(ቁርኣን) ከግሳጼም የሚያፈገፍጉበት ምን ምክኒያት አላቸው?

49. ከ(ቁርኣን) ከግሳጼም የሚያፈገፍጉበት ምን ምክኒያት አላቸው?

كَأَنَّهُمۡ حُمُرٞ مُّسۡتَنفِرَةٞ

50. እነርሱ ልክ ደንባሪዎች የሜዳ አህዩች ይመስላሉ::

50. እነርሱ ልክ ደንባሪዎች የሜዳ አህዩች ይመስላሉ::

فَرَّتۡ مِن قَسۡوَرَةِۭ

51. ከአንበሳ የሸሹ

51. ከአንበሳ የሸሹ

بَلۡ يُرِيدُ كُلُّ ٱمۡرِيٕٖ مِّنۡهُمۡ أَن يُؤۡتَىٰ صُحُفٗا مُّنَشَّرَةٗ

52. ይልቁንም ከእነርሱ መካከል ለእያንዳንዱ ሰው የተዘረጉ ጹሑፎችን በእጁ እንዲሰጥ ይፈልጋል::

52. ይልቁንም ከእነርሱ መካከል ለእያንዳንዱ ሰው የተዘረጉ ጹሑፎችን በእጁ እንዲሰጥ ይፈልጋል::

كَلَّاۖ بَل لَّا يَخَافُونَ ٱلۡأٓخِرَةَ

53. ከዚህ መሰል ተግባራቸው ይከልከሉ:: ይልቁንም የመጨረሻይቱን ዓለም ቅጣት አይፈሩም::

53. ከዚህ መሰል ተግባራቸው ይከልከሉ:: ይልቁንም የመጨረሻይቱን ዓለም ቅጣት አይፈሩም::

كَلَّآ إِنَّهُۥ تَذۡكِرَةٞ

54. ይከልከሉ፤እርሱ(ቁርአን) መገሰጫ ነው።

54. ይከልከሉ፤እርሱ(ቁርአን) መገሰጫ ነው።

فَمَن شَآءَ ذَكَرَهُۥ

55. ስለዚህ የፈለገ ሰው ቁርኣንን ይገሰጽበታል::

55. ስለዚህ የፈለገ ሰው ቁርኣንን ይገሰጽበታል::

وَمَا يَذۡكُرُونَ إِلَّآ أَن يَشَآءَ ٱللَّهُۚ هُوَ أَهۡلُ ٱلتَّقۡوَىٰ وَأَهۡلُ ٱلۡمَغۡفِرَةِ

56. ሆኖም (ሰዎች) አላህ ካልፈለገ በስተቀር አይገሰጹም:: አላህ የመፈራት ባለቤት ነው:: (ለፈሩትም) የምህረት ባለቤት ነው::

56. ሆኖም (ሰዎች) አላህ ካልፈለገ በስተቀር አይገሰጹም:: አላህ የመፈራት ባለቤት ነው:: (ለፈሩትም) የምህረት ባለቤት ነው::
Footer Include