Header Include

Amharic translation - Africa Academy

Translated by Muhammad Zain Zahruddin. Published by Africa Academy

QR Code https://quran.islamcontent.com/aa/amharic_zain

وَٱلسَّمَآءِ وَٱلطَّارِقِ

1. በሰማዩ እና ሌሊት በሚመጣውም እምላለሁ።

1. በሰማዩ እና ሌሊት በሚመጣውም እምላለሁ።

وَمَآ أَدۡرَىٰكَ مَا ٱلطَّارِقُ

2. (መልዕክተኛችን ሙሐመድ ሆይ!) የሌሊት መጪው ምን እንደሆነ ምን አሳወቀህ?

2. (መልዕክተኛችን ሙሐመድ ሆይ!) የሌሊት መጪው ምን እንደሆነ ምን አሳወቀህ?

ٱلنَّجۡمُ ٱلثَّاقِبُ

3. ጨለማውን ሰንጣቂ ኮከብ ነው::

3. ጨለማውን ሰንጣቂ ኮከብ ነው::

إِن كُلُّ نَفۡسٖ لَّمَّا عَلَيۡهَا حَافِظٞ

4. ነፍስ ሁሉ በእርሷ ላይ ጠባቂ ያለባት እንጂ ሌላ አይደለችም::

4. ነፍስ ሁሉ በእርሷ ላይ ጠባቂ ያለባት እንጂ ሌላ አይደለችም::

فَلۡيَنظُرِ ٱلۡإِنسَٰنُ مِمَّ خُلِقَ

5. የሰው ልጅ ከምን እንደተፈጠረ ይመልከት፤

5. የሰው ልጅ ከምን እንደተፈጠረ ይመልከት፤

خُلِقَ مِن مَّآءٖ دَافِقٖ

6. ከተስፈንጣሪ ውሃ (የዘር ፈሳሽ) ተፈጠረ::

6. ከተስፈንጣሪ ውሃ (የዘር ፈሳሽ) ተፈጠረ::

يَخۡرُجُ مِنۢ بَيۡنِ ٱلصُّلۡبِ وَٱلتَّرَآئِبِ

7. ከጀርባና ከእርግብግቢቶች መካከል የሚወጣ ከሆነ የዘር ፈሳሽ ውሃ (ተፈጠረ)።

7. ከጀርባና ከእርግብግቢቶች መካከል የሚወጣ ከሆነ የዘር ፈሳሽ ውሃ (ተፈጠረ)።

إِنَّهُۥ عَلَىٰ رَجۡعِهِۦ لَقَادِرٞ

8. አላህ እርሱን በመመለሱ ላይ በእርግጥ ቻይ ነው::

8. አላህ እርሱን በመመለሱ ላይ በእርግጥ ቻይ ነው::

يَوۡمَ تُبۡلَى ٱلسَّرَآئِرُ

9. ሚስጥሮች በሚገለጹበት ቀን፤

9. ሚስጥሮች በሚገለጹበት ቀን፤

فَمَا لَهُۥ مِن قُوَّةٖ وَلَا نَاصِرٖ

10. (ለሰው) ምንም ኃይልና ረዳት አይኖረዉም::

10. (ለሰው) ምንም ኃይልና ረዳት አይኖረዉም::

وَٱلسَّمَآءِ ذَاتِ ٱلرَّجۡعِ

11. የመመለስ ባለቤት (ዝናባማ) በሆነችው ሰማይ እምላለሁ::

11. የመመለስ ባለቤት (ዝናባማ) በሆነችው ሰማይ እምላለሁ::

وَٱلۡأَرۡضِ ذَاتِ ٱلصَّدۡعِ

12. (በበቃይ) የመሰንጠቅ ባለቤት በሆነችው ምድርም እምላለሁ::

12. (በበቃይ) የመሰንጠቅ ባለቤት በሆነችው ምድርም እምላለሁ::

إِنَّهُۥ لَقَوۡلٞ فَصۡلٞ

13. እርሱ (ቁርኣን)፤ (እውነትን ከውሸት) የሚለይ (የአላህ) ቃል ነው።

13. እርሱ (ቁርኣን)፤ (እውነትን ከውሸት) የሚለይ (የአላህ) ቃል ነው።

وَمَا هُوَ بِٱلۡهَزۡلِ

14. እርሱም ቀልድ አይደለም።

14. እርሱም ቀልድ አይደለም።

إِنَّهُمۡ يَكِيدُونَ كَيۡدٗا

15. እነርሱ በእርግጥ ተንኮልን ያሴራሉ (ይሸርባሉ)::

15. እነርሱ በእርግጥ ተንኮልን ያሴራሉ (ይሸርባሉ)::

وَأَكِيدُ كَيۡدٗا

16. እኔ ተንኮልንም እመልሳለሁ (አመክናለሁ)::

16. እኔ ተንኮልንም እመልሳለሁ (አመክናለሁ)::

فَمَهِّلِ ٱلۡكَٰفِرِينَ أَمۡهِلۡهُمۡ رُوَيۡدَۢا

17. (መልዕክተኛችን ሙሐመድ ሆይ!) ከሓዲያንን ቀን ሰጣቸው:: ጥቂትን ጊዜ አቆያቸው (ታገሳቸው)::

17. (መልዕክተኛችን ሙሐመድ ሆይ!) ከሓዲያንን ቀን ሰጣቸው:: ጥቂትን ጊዜ አቆያቸው (ታገሳቸው)::
Footer Include