Amharic translation - Africa Academy
Translated by Muhammad Zain Zahruddin. Published by Africa Academy
إِذَا ٱلسَّمَآءُ ٱنفَطَرَتۡ
1. ሰማይ በተሰነጠቀች ጊዜ፤
وَإِذَا ٱلۡكَوَاكِبُ ٱنتَثَرَتۡ
2. ከዋክብትም ተበታትነው በወደቁ ጊዜ፤
وَإِذَا ٱلۡبِحَارُ فُجِّرَتۡ
3. ባህሮችም በተከፈቱና በተደባለቁ ጊዜ፤
وَإِذَا ٱلۡقُبُورُ بُعۡثِرَتۡ
4. መቃብሮችም በተገለባበጡና ሙታን በተነሱ ጊዜ፤
عَلِمَتۡ نَفۡسٞ مَّا قَدَّمَتۡ وَأَخَّرَتۡ
5. (ያኔ) ማንኛይቱም ነፍስ ያስቀደመችውንና ያዘገየችውን ታውቃለች።
يَٰٓأَيُّهَا ٱلۡإِنسَٰنُ مَا غَرَّكَ بِرَبِّكَ ٱلۡكَرِيمِ
6. አንተ ሰው ሆይ! በቸሩ ጌታህ ምን አታለለህ?
ٱلَّذِي خَلَقَكَ فَسَوَّىٰكَ فَعَدَلَكَ
7. በዚያ በፈጠረህ፤ አካለ ሙሉም ባደረገህ፤ ባስተካከለህም፤
فِيٓ أَيِّ صُورَةٖ مَّا شَآءَ رَكَّبَكَ
8. በማንኛውም (እርሱ) በፈለገው ቅርጽ በገጣጠመህ ጌታህ ምን አታለለህ?
كَلَّا بَلۡ تُكَذِّبُونَ بِٱلدِّينِ
9 (ሰዎች ሆይ!) ተከልከሉ፤ በእውነት በፍርዱ ቀን ታስተባብላላችሁ።
وَإِنَّ عَلَيۡكُمۡ لَحَٰفِظِينَ
10. በእናንተ ላይ ጠባቂዎች ያሉባችሁ ስትሆኑ፤
كِرَامٗا كَٰتِبِينَ
11. የተከበሩ ጸሐፊዎች የሆኑ (ተጠባባቂዎች)፤
يَعۡلَمُونَ مَا تَفۡعَلُونَ
12. የምትሰሩትን (ሁሉ) ያውቃሉ፤
إِنَّ ٱلۡأَبۡرَارَ لَفِي نَعِيمٖ
13. (እውነተኞቹ) ደጋጎች በእርግጥም በገነት ውስጥ ናቸው።
وَإِنَّ ٱلۡفُجَّارَ لَفِي جَحِيمٖ
14.ከሓዲያንም በእርግጥ በገሀነም ውስጥ ናቸው::
يَصۡلَوۡنَهَا يَوۡمَ ٱلدِّينِ
15.በፍርዱ ቀን ይገቧታል::
وَمَا هُمۡ عَنۡهَا بِغَآئِبِينَ
16.እነርሱም (ምን ጊዜም) ከእርሷ ራቂዎች አይደሉም::
وَمَآ أَدۡرَىٰكَ مَا يَوۡمُ ٱلدِّينِ
17. (መልዕክተኛችን ሙሐመድ ሆይ!) የፍርዱ ቀን ምን እንደሆነ ምን አሳወቀህ?
ثُمَّ مَآ أَدۡرَىٰكَ مَا يَوۡمُ ٱلدِّينِ
18. ከዚያም የፍርዱ ቀን ምን እንደሆነ ምን አሳወቅህ?
يَوۡمَ لَا تَمۡلِكُ نَفۡسٞ لِّنَفۡسٖ شَيۡـٔٗاۖ وَٱلۡأَمۡرُ يَوۡمَئِذٖ لِّلَّهِ
19. (እርሱ) ማንኛይቱም ነፍስ ለሌላይቱ ነፍስ ምንም ማድረግ የማትችልበት ቀን ነው:: ነገሩም ሁሉ በዚያ ቀን ለአላህ ብቻ ነው::
مشاركة عبر