Header Include

Amharic translation - Africa Academy

Translated by Muhammad Zain Zahruddin. Published by Africa Academy

QR Code https://quran.islamcontent.com/aa/amharic_zain

هَلۡ أَتَىٰكَ حَدِيثُ ٱلۡغَٰشِيَةِ

1. (መልዕክተኛችን ሙሐመድ ሆይ!) የሸፋኝቱ ትንሳኤ ወሬ መጣልህን?

1. (መልዕክተኛችን ሙሐመድ ሆይ!) የሸፋኝቱ ትንሳኤ ወሬ መጣልህን?

وُجُوهٞ يَوۡمَئِذٍ خَٰشِعَةٌ

2. በዚያ ቀን የከሓዲያን ፊቶች ተዋራጆች ናቸው::

2. በዚያ ቀን የከሓዲያን ፊቶች ተዋራጆች ናቸው::

عَامِلَةٞ نَّاصِبَةٞ

3. ሰሪዎች ለፊዎች ናቸው::

3. ሰሪዎች ለፊዎች ናቸው::

تَصۡلَىٰ نَارًا حَامِيَةٗ

4. የምታቃጥልን እሳት ይገባሉ::

4. የምታቃጥልን እሳት ይገባሉ::

تُسۡقَىٰ مِنۡ عَيۡنٍ ءَانِيَةٖ

5. በጣም ከፈላች ምንጭም ይጋታሉ::

5. በጣም ከፈላች ምንጭም ይጋታሉ::

لَّيۡسَ لَهُمۡ طَعَامٌ إِلَّا مِن ضَرِيعٖ

6. ዶሪዕ ከሚባል (እሾሃማ) ዛፍ እንጂ ሌላ ምግብ የላቸዉም::

6. ዶሪዕ ከሚባል (እሾሃማ) ዛፍ እንጂ ሌላ ምግብ የላቸዉም::

لَّا يُسۡمِنُ وَلَا يُغۡنِي مِن جُوعٖ

7. አካልን አያሰባ፤ ከረኃብም አያብቃቃ፤

7. አካልን አያሰባ፤ ከረኃብም አያብቃቃ፤

وُجُوهٞ يَوۡمَئِذٖ نَّاعِمَةٞ

8. (የአማንያን) ፊቶች በዚያ ቀን ተቀማጣዮች ናቸው::

8. (የአማንያን) ፊቶች በዚያ ቀን ተቀማጣዮች ናቸው::

لِّسَعۡيِهَا رَاضِيَةٞ

9. በስራቸውም ተደሳቾች ናቸው::

9. በስራቸውም ተደሳቾች ናቸው::

فِي جَنَّةٍ عَالِيَةٖ

10. በከፍተኛ ገነት ውስጥ ናቸው::

10. በከፍተኛ ገነት ውስጥ ናቸው::

لَّا تَسۡمَعُ فِيهَا لَٰغِيَةٗ

11. በውስጧ ውድቅን ነገር አይሰሙም::

11. በውስጧ ውድቅን ነገር አይሰሙም::

فِيهَا عَيۡنٞ جَارِيَةٞ

12. በውስጧ ፈሳሾች ምንጮች አሉ::

12. በውስጧ ፈሳሾች ምንጮች አሉ::

فِيهَا سُرُرٞ مَّرۡفُوعَةٞ

13. በውስጧ ከፍ የተደረጉ አልጋዎች አሉ::

13. በውስጧ ከፍ የተደረጉ አልጋዎች አሉ::

وَأَكۡوَابٞ مَّوۡضُوعَةٞ

14. በተርታ የተኖሩ ኩባያዎችም፤

14. በተርታ የተኖሩ ኩባያዎችም፤

وَنَمَارِقُ مَصۡفُوفَةٞ

15. የተደረደሩ መከዳዎችም፤

15. የተደረደሩ መከዳዎችም፤

وَزَرَابِيُّ مَبۡثُوثَةٌ

16. የተነጠፉ ስጋጃዎችም (አሉ)::

16. የተነጠፉ ስጋጃዎችም (አሉ)::

أَفَلَا يَنظُرُونَ إِلَى ٱلۡإِبِلِ كَيۡفَ خُلِقَتۡ

17. (ከሓዲያን) ግመል እንዴት እንደተፈጠረች አይመለከቱምን?

17. (ከሓዲያን) ግመል እንዴት እንደተፈጠረች አይመለከቱምን?

وَإِلَى ٱلسَّمَآءِ كَيۡفَ رُفِعَتۡ

18. ሰማይም እንዴት ከፍ እንደተደረገች!

18. ሰማይም እንዴት ከፍ እንደተደረገች!

وَإِلَى ٱلۡجِبَالِ كَيۡفَ نُصِبَتۡ

19. ተራራዎችም እንዴት እንደ ተቸከሉ!

19. ተራራዎችም እንዴት እንደ ተቸከሉ!

وَإِلَى ٱلۡأَرۡضِ كَيۡفَ سُطِحَتۡ

20. ምድርም እንዴት እንደተዘረጋች አይመለከቱምን?!

20. ምድርም እንዴት እንደተዘረጋች አይመለከቱምን?!

فَذَكِّرۡ إِنَّمَآ أَنتَ مُذَكِّرٞ

21. (መልዕክተኛችን ሙሐመድ ሆይ!) አስታውስም:: አንተ አስታዋሽ ብቻ ነህና::

21. (መልዕክተኛችን ሙሐመድ ሆይ!) አስታውስም:: አንተ አስታዋሽ ብቻ ነህና::

لَّسۡتَ عَلَيۡهِم بِمُصَيۡطِرٍ

22. በእነርሱ ላይ አስገዳጅ (ተሿሚ) አይደለህም፤

22. በእነርሱ ላይ አስገዳጅ (ተሿሚ) አይደለህም፤

إِلَّا مَن تَوَلَّىٰ وَكَفَرَ

23. ግን ከእውነት የዞረና የካደ፤

23. ግን ከእውነት የዞረና የካደ፤

فَيُعَذِّبُهُ ٱللَّهُ ٱلۡعَذَابَ ٱلۡأَكۡبَرَ

24. አላህም ከባዱን ቅጣት ይቀጣዋል።

24. አላህም ከባዱን ቅጣት ይቀጣዋል።

إِنَّ إِلَيۡنَآ إِيَابَهُمۡ

25. መመለሻቸው ወደ እኛ ብቻ ነው::

25. መመለሻቸው ወደ እኛ ብቻ ነው::

ثُمَّ إِنَّ عَلَيۡنَا حِسَابَهُم

26. ምርመራቸዉም በእኛ ላይ ብቻ ነው::

26. ምርመራቸዉም በእኛ ላይ ብቻ ነው::
Footer Include