Amharic translation - Africa Academy
Translated by Muhammad Zain Zahruddin. Published by Africa Academy
لَآ أُقۡسِمُ بِهَٰذَا ٱلۡبَلَدِ
1. በዚህ ሀገር (በመካ) እምላለሁ
وَأَنتَ حِلُّۢ بِهَٰذَا ٱلۡبَلَدِ
2.(መልዕክተኛችን ሙሐመድ ሆይ!) አንተ በዚህ አገር ሰፋሪ ስትሆን።
وَوَالِدٖ وَمَا وَلَدَ
3.በወላጂና በወለዳቸውም (በአደምና በዘሮቹ) ሁሉ (እምላለሁ)።
لَقَدۡ خَلَقۡنَا ٱلۡإِنسَٰنَ فِي كَبَدٍ
4. ሰውን ሁሉ በእርግጥ በልፋት ውስጥ ሆኖ ፈጠርነው::
أَيَحۡسَبُ أَن لَّن يَقۡدِرَ عَلَيۡهِ أَحَدٞ
5. በእርሱ ላይ አንድም አካል የማይችል መሆኑን ይጠረጥራልን?
يَقُولُ أَهۡلَكۡتُ مَالٗا لُّبَدًا
6. "ብዙን ገንዘብ አጠፋሁ" ይላል፤
أَيَحۡسَبُ أَن لَّمۡ يَرَهُۥٓ أَحَدٌ
7. አንድም ያላየው መሆኑን ያስባልን?
أَلَمۡ نَجۡعَل لَّهُۥ عَيۡنَيۡنِ
8. ለእርሱ ሁለት አይኖችን አላደረግንለትንምን?
وَلِسَانٗا وَشَفَتَيۡنِ
9. አንድ ምላስንና ሁለት ከንፈሮችንም፤
وَهَدَيۡنَٰهُ ٱلنَّجۡدَيۡنِ
10.ሁለትን መንገዶችስ አልመራነዉምን?
فَلَا ٱقۡتَحَمَ ٱلۡعَقَبَةَ
11.ዐቀበቱን አልወጣም።
وَمَآ أَدۡرَىٰكَ مَا ٱلۡعَقَبَةُ
12.ዐቀበቱን መውጣት ምን እንደሆነ ምን አሳወቀህ?
فَكُّ رَقَبَةٍ
13.ያ ጫንቃን መልቀቅ ነው። [1]
أَوۡ إِطۡعَٰمٞ فِي يَوۡمٖ ذِي مَسۡغَبَةٖ
14. ወይም የረሀብ ባለቤት በሆነ ቀን (ረሀብተኛን) ማብላት፤
يَتِيمٗا ذَا مَقۡرَبَةٍ
15. የዝምድና ባለቤት የሆነን የቲም፤
أَوۡ مِسۡكِينٗا ذَا مَتۡرَبَةٖ
16.ወይም የአፈር ባለቤት የሆነን (ችግረኛ) ማብላት ነው።
ثُمَّ كَانَ مِنَ ٱلَّذِينَ ءَامَنُواْ وَتَوَاصَوۡاْ بِٱلصَّبۡرِ وَتَوَاصَوۡاْ بِٱلۡمَرۡحَمَةِ
17.ከዚያም ከእነዚያ በአላህ ካመኑትና በመታገስ ላይ አደራ ከተባባሉት ሰዎች ጋር መሆን ነው።
أُوْلَٰٓئِكَ أَصۡحَٰبُ ٱلۡمَيۡمَنَةِ
18. እነዚያ (ይህንን የፈጸሙ) የቀኝ ጓዶች ናቸው።
وَٱلَّذِينَ كَفَرُواْ بِـَٔايَٰتِنَا هُمۡ أَصۡحَٰبُ ٱلۡمَشۡـَٔمَةِ
19. እነዚያ በአናቅጻችን የካዱ ሁሉ እነርሱ የግራ ጓዶች ናቸው።
عَلَيۡهِمۡ نَارٞ مُّؤۡصَدَةُۢ
20. ለእነርሱ የምትዘጋባቸው እሳትም አለች።
مشاركة عبر